Фильтр публикаций


የራሽያ ኢኮኖሚ 28,000 ማዕቀብ ተቋቁሞ እንዴት አደገ?

ኢኮኖሚው ለ3 ዓመት ጦርነት ውስጥ ሆኖ እጥፍ የGDP እና የፖለቲካ አጋርነት እድገት አስመዝግቧል!

የራሽያ ኢኮኖሚ ( ፑቲን) በጦርነት እና በማዕቀብ ውስጥ ሆኖ ኢኮኖሚን የማሳደግ ምሳሌ ሆነዋል!

ራሽያ ላለፉት 3 ዓመታት 28,000 ማዕቀብ ቢጣልባትም ኢኮኖሚዋ ማዕቀብ ከጣሉባት ሃገራት የተሻለ እድገት ማስመዝገቡን IMF እየመሰከረ ነው!

ጠለቅ አድርገን እንመልከተው.....https://youtu.be/wkH0Ln2QgVE


የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ 27 ባንኮች በተሳተፉበት ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላርን በ136 ብር ቢሸጥላቸውም ንግድ ባንኮቹ ከ3 ቀን በኋላ አብዛኞቹ የመሸጫ ዋጋ ለውጥ አላደረጉም!

የ10 ባንኮችን የተከታታይ 3 ቀናት የዶላር የመሸጫ ዋጋ ስንመለከት ያደረጉት ለውጥ የሚጠበቅ አይደለም!

ባንኮች ዶላር ከገዙበት በታች እየሸጡ ያሉበት ድራማ መነሻው ምንድን ነው?

ከጨረታው በኋላ እድል የተከፈተላቸው ባንኮች....

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ዶላር የሸጠው ገበያው ውስጥ ወርቅ ለመግዛት የበተነውን ብር ለመሰብሰብ ነው ወይስ ለወርቅ ሸመታ ብር አጥሮት ብር ለማግኘት?

በዝርዝር እንመልከተው.....https://youtu.be/LDONqlkHZMs


ብሄራዊ ባንክ ገበያውን አረጋጋለሁ ብሎ ብርን ለምን ከ8-10 ብር ድረስ ለማዳከም ወሰነ?

ብሔራዊ ባንክ በዛሬው የዶላር ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ 135.61 ብር ዋጋ መሸጡን አስታወቋል!

ከዛሬው የመደበኛ ባንኮች የምንዛሬ ተመን አንፃር ብር ከ8-10 ብር ተዳክሟል!

የዚህ ጨረታ ዋጋ መጋነን ምክንያት ምንድን ነው?

የብር መዳከም ከነገ ጀምሮ በገበያው ላይ የሚፈጥረው ተፅዕኖ ምን ሊሆን ይችላል?

ብሄራዊ ባንክ የምንዛሬው ዋጋው መጋነኑን ከተመለከተ በኋላ ጨረታውን ለምን አልሰረዘም?

በፍፁም የጨረታው ዋጋ ብርን በጣም ያዳክማል ብዬ አላሰብኩም ነበር! በዝርዝር እንመልከተው....https://youtu.be/Q0LmEXlEMdU


#ለመረጃ፡ ብሔራዊ ባንክ በዛሬው የዶላር ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ 135.61 ብር ዋጋ መሸጡን አስታወቀ።

ጥያቄው ንግድ ባንኮቹ ለውጪ ምንዛሬ ፈላጊው በስንት ሊሸጡ ነው?


የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የ60 ሚሊየን ዶላር ጨረታ አወጣ! የዶላር ጨረታው የዶላር ዋጋን ይወስናል?

የመጀመሪያው የዶላር ጨረታ ከኢኮኖሚ ለውጡ 10 ቀን በኋላ (ነሃሴ 1/2016) ነበር አንድ ዶላር 107.9 ብር ዋጋ ወጥቶለት የነበረው!

ከ6 ወር በኋላ 60 ሚሊየን ዶላር ለጨረታ ቀርቧል! በገበያው ምን አይነት ለውጥ ሊያመጣ ይችላል?

የመጀመሪያው ጨረታ የሚገመት ውጤት አልነበረውም!

ከአሁኑ ጨረታ የውጪ ምንዛሬ ገበያው ለውጥ ሊኖረው ይችላል...https://youtu.be/FUqXEb_oM2c


#ለመረጃ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ነገ የካቲት 18 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚያካሂድ አስታውቋል፡፡

ለጨረታ የሚቀርበው የውጭ ምንዛሪ መጠን 60 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ሲሆን ጨረታው ለሁሉም ባንኮች ክፍት እንደሚሆን ታውቋል።


የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አዲስ ህመም እየገጠመው ነው!

ኢኮኖሚው የውጪ ምንዛሬ ቢያከማችም! መልሶ የሚሸጥበት የኢትዮጵያ ብር አቅርቦት እጥረት ገጥሞታል!

ባንኮች የጥሬ ብር አከማችተዋል ብለው ለሚያስቡት ተቋም እና ግለሰብ የጊዜ ገደብ ቁጠባ ከ20 ከመቶ በላይ ወለድ እንደሚያስቡ እየተደራደሩ ነው!

በጊዜ ገደብ ገንዘብ መቆጠብ ያለውን እድል እና ስጋት እንመልከት....

በዝርዝር አዲሱን ህመም እንፈትሽ....https://youtu.be/y6Ug5H6zk2k


አሜሪካ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ልትወጣ ስለማሰቧ እየገለፀች ነው!

ምክንያታቸው UN ባለ ትልቅ በጀት አዋጪዋን ሀገር አሜሪካንን ማስቀደም አልቻለም ነው!

አሜሪካ 28% (በ2022 ብቻ 18 ቢሊየን ዶላር ከፍላለች)፤ ቻይና 15%፤ ጃፓን (8.5%)፤ ጀርመን እና እንግሊዝ በተከታታይ ከፍተኛ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በጀት ድርሻ የያዙ ናቸው።

የድርጅቱ አባል ሆነው የሚጠበቅባቸውን የበጀት መዋጮ የማያደርጉ ሀገራት ጥቂት አይደሉም! ለምሳሌ ኢራን፤ ባርባዶስ፤ ኮሞሮስ፤ ኮንጎ፤ ጊኒ፤ ፓፓዋ ኒው ጊኒ፤ ቬንዙዌላ፤ ሱዳን እና ሳዎቶሜ ናቸው።

ኢትዮጵያ በ2022 (289 ሺ ዶላር)፤ በ2023 (292ሺ ዶላር)፤ በ2024 (315 ሺ ዶላር)፤ 2025 (340ሺ ዶላር) መዋጮ አድርጋለች!

የአሜሪካንን መውጣት እንደ አንድ ሃገር መውጣት ለመመልከት ከባድ ነው!

መግለጫውን ማንበብ ለምትፈልጉ https://www.whitehouse.gov/presidential-actions/2025/02/withdrawing-the-united-states-from-and-ending-funding-to-certain-united-nations-organizations-and-reviewing-united-states-support-to-all-international-organizations/


ዩክሬን ለጦርነት የተሰጣትን 500 ቢሊየን ዶላር ድጋፍ በተፈጥሮ ሃብት መክፈል አለባት! የማታሸንፉትን ጦርነት ማን ጀምሩ አላችሁ (ትራምፕ!) በራሽያ እና በዩክሬን መካከል የተጀመረው ጦርነት 3 ዓመት ሞላው!

ጦርነቱ እንዲያበቃ አሜሪካ እና ራሽያ ውይይት ቢጀምሩም ዋናዋ የሚመለከታት ሀገር ዩክሬን ለውይይቱ አልተጋበዘችም!

ዩክሬን ለጦርነት የተሰጣትን 500 ቢሊየን ዶላር ድጋፍ በተፈጥሮ ሃብት መክፈል አለባት! የማታሸንፉትን ጦርነት ማን ጀምሩ አላችሁ (ትራምፕ!) እየተባለ ነው!

የሁለቱን ሀገራት ኢኮኖሚ ከጦርነቱ 3 ዓመት በፊት እና ከጦርነቱ ጀምሮ ላለፊት 3 ዓመታት ከፋፍለን እንመልከተው....

ዩክሬን ለውድመት የዳረጋትን የ500 ቢሊየን ዶላር ድጋፍ እንዴት አድርጋ መክፈል እንደምትችል እንመልከት....https://youtu.be/cyR3sOAkZxM


#መልካም_ዜና: አሊባባ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ #በኢትዮጵያ_ብር ክፍያ መቀበል እንደሚጀምር አስታወቀ!

አለም አቀፍ የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ተቋም የሆነው አሊ ባባ እንደገለፀው ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ #በአሊ_ኤክስፕረስ የበርካታ አገራትን ገንዘብ ጥቅም ላይ ያውላል፡፡

ከእነዚህ አገራት መካከል ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ፤ ግብፅ፣ ኬንያ እና ደቡብ አፍሪካ ይገኙበታል፡፡ የክፍያ መፈፀሚያ ገንዘቦችን ማስፋፋት ያስፈለገው ለአፍሪካ ተጠቃሚዎች በስፋት ተደራሽ ለመሆን በማሰብ እንደሆነ የጠቀሰው አሊ ባባ በተጨማሪም በአለም አቀፍ የክሬዲት ካርዶችና #የውጭ_ምንዛሬ ላይ ያለውን ጥገኝነት ለማስቀረት እንደሆነ አስረድቷል፡፡

የአፍሪካ አገራትን ገንዘብ በግብይቱ ውስጥ ጥቅም ላይ ማዋሉ በአለም አቀፍ የክፍያ ስርአት የተነሳ ለአፍሪካዊያን ትልቅ ማነቆ የሆነውን ችግር ለመቅረፍ ማቀዱንም አስታውቋል፡፡ በዚህም አዳዲስ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎችን እንደሚያገኝ ተስፋ ሰንቋል፡፡

ለዚህ እንዲረዳው በተጠቀሱት አገራት ከሚገኙ የዲጂታል ክፍያ አገልግሎት ሰጪዎች ጋር ጥምረት መፍጠሩን የገለፀው አሊ ባባ ከሚቀጥለው ሳምንት ማለትም #የካቲት_17 ጀምሮ ብርን ጨምሮ የተለያዩ ገንዘቦችን በግብይት ስርአቱ ውስጥ እንደሚያካትት አስታውቋል፡፡

#ለምሳሌ፦ አሊባባ ከቴሌ ብር ጋር ለመስራት ቢስማማ ከአሊ ኤክስፕረስ ላይ ኦንላይን/Online እቃ ለመግዛት ቴሌ ብር ተጠቅሞ መክፈል ይቻላል ማለት ነው!


የንግድ ጦርነት (Trade War)!

በዓለም ላይ ላለፉት 150 ዓመታት የንግድ ጦርነት ልምምዶች አሉ!

በንግድ ጦርነት ደጋፊዎች እና ተቺዎች መካከል ክርክር አለ!

የንግድ ጦርነት ምንነት፤ በዓለም ላይ የነበሩ ጦርነቶች፤ ጦርነት ውስጥ ያሉ እድሎች እና አደጋዎችን በምሳሌ እንመልከት.....https://youtu.be/ZcnRGR9oqpY


#ምን_ማለት_ነው?

"ኢትዮጵያ ለውጭ ባንኮች ፈቃድ የምትሰጠው #ለወዳጅ_አገራት መሆኑን የብሄራዊ ባንክ ገዥ ተናገሩ....

ጥሩ ስም ያላቸው አለም አቀፍ ባንኮች በኢትዮጵያ ውስጥ መሰማራታቸው ጠቃሚ ቢሆንም ፈቃድ ለማግኘት ባንኮቹ የሚገኙበት #አገር ከግምት ውስጥ እንደሚገባ....

የውጭ ባንኮቹ መነሻ አገራት ከኢትዮጵያ ጋር መልካም ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸውና ከኢትዮጵያ ጋር ለመተባበር ፈቃደኛ መሆን ይገባቸዋል" ብለዋል።

የፖለቲካ ዓለሙ ዘላቂ ወዳጅም ጠላትም በማያድልበት ምዕዳር ውስጥ የንግድ ግንኙነትን በሚገፋ የፖለቲካ መለኪያ ለመምራት መሞከር ደካማ ምክንያታዊነት ያለው ነው!

አቶ ማሞ ምህረቱ ከመንግስታዊው ዘመን ኢኮኖሚ መጽሔት ጋር ካደረጉት ቃለ ምልልስ!


📍 ፒያሳ አድዋ ሙዚየም ፊትለፊት
የንግድ ሱቆች በ 900 ሺ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ እንዲሁም ፒያሳ ሊሴ ገ/ማሪያም ት/ቤት አጠገብ የመኖርያ አፓርትመንት በምዝገባ ላይ እንገኛለን።

🎖ለልማት ተነሺዎች አና ለመርካቶ ነጋዴዎች።

🎖መረከቢያ ጊዜ 1 አመት ከ 6ወር

🎖በዶላር ሳይሆን በኢትዮጵያ ብር ይስተናገዳሉ !!!

🎖 የሱቆቹ ስፋታቸው ከ10--- 30ካሬ

📞0974981373

❗️ፒያሳ ሊሴ ገ/ማሪያም ት/ቤት አጠገብ
👉30%ሲከፍሉ 25% ቅናሽ ያገኛሉ
በ18 ዙር ምቹ አከፋፈል 10% ቅድመ ክፍያ  የቤት ባለቤት ይሁኑ።30%ሲከፍሉ 25% ቅናሽ ያገኛሉ
  ስቲዲዮ ,,,
    ♦️46 ካሬ
    ♦️48 ካሬ
ባለ1 መኝታ:
        ♦️64ካሬ
        ♦️66ካሬ
        ♦️71ካሬ
        ♦️75 ካሬዎች
ባለ2 መኝታ:
        ♦️ 71,ካሬ
         ♦️75,ካሬ
         ♦️78,ካሬ
         ♦️91, ካሬ
         ♦️92 እና 99 ካሬ
ባለ3 መኝታ:130 እና 142 ካሬ
NB:100% ለከፈለ 25% Discount.
Nb:ምንም አይነት ዶላር  ጭማሪ አያሳስብዎትም
📣📣📣📣📣
0974981373


በኢትዮጵያ ዋጋ ንረት በአንድ ዓመት ውስጥ በ13.9% ቀነሰ!

የኢትዮጲያ ብሄራዊ ባንክ የ6 ወር አፈጻጸም ሪፖርት ወጥቷል! ሪፖርቱ ለማመን የሚከብዱ ቁጥሮችን ይዟል!

ለምሳሌ፡- የዋጋ ንረት በአንድ ዓመት ውስጥ ከ29.4% ወደ 15.5% ቀንሷል! የዋጋ ንረቱ በአንድ ዓመት ውስጥ በ13.9% ቀንሷል! የኢትዮጲያ የዋጋ ንረቱ በአምስት ዓመት ውስጥ ዝቅተኛው ደረጃ ላይ ደርሷል!

የዋጋ ንረት፤ የውጪ ምንዛሬ ግኝት፤ የረሚታንስ ግኝት (በባንኮች የሚደረጉ የግለሰቦች ዝውውር) ፤ የውጪ ንግድ ውጤት (የImport ቅነሳ እና የExport ጭማሪ)፤ የኢንተርባንክ የገንዘብ ገበያ ግብይት፤ ወዘተ፡፡

የመጨረሻውን የኢኮኖሚ ሪፎርም አዝማሚያ ማሳየት ስለሚችል የሪፖርቱን ዋና ዋና የኢኮኖሚ ግኝቶች ከገለልተኛ ተቋማት መረጃ አንጻር በንጽጽር እንመልከተው…..https://youtu.be/N8LUAYfS0Bc


የአፍሪካ ሃገራት እና የብልፅግና እርቀት!

የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ወቅት በመሆኑ መታወቅ ያለበት! Legatum Prosperity Index!

ስለ ፖለቲካ ሳይሆን ስለ ኢኮኖሚ እንመልከት...https://youtu.be/RcY_HAmmUbg


የኢትዮጲያ ብሄራዊ ባንክ 3 የወለድ አይነት/ተመኖች ላይ ያለው ወቅታዊ መረጃ!

#ዝቅተኛ_የተቀማጭ_ገንዘብ_ወለድ_መጠን 7 በመቶ ነው! ይህም ማለት ባንክ ቤት ገንዘብ በቁጠባ ለሚያስቀምጡ የሚታሰበው የወለድ መጠን 7 በመቶ ነው፡፡

#የግምጃ_ቤት_ሰነድ_የወለድ_መጠን 15.17 በመቶ ነው! ይህም ማለት መንግስት የሚያቀርባቸውን የግምጃ ቤት ሰነዶች ለሚገዙ ተቋማት እና ግለሰቦች የክፍያ ወቅቱን ጠብቆ የሚታሰበው የወለድ መጠን 15.17 በመቶ ነው፡፡

#የብሔራዊ_ባንክ_የወለድ_ተመን 15 በመቶ ነው! ይህም ማለት ንግድ ባንኮች ከብሄራዊ ባንክ ብድር በፈለጉ ጊዜ ሲበደሩ ለብሄራዊ ባንኩ የሚከፍሉት ወይም የሚታሰብባቸው የወለድ መጠን 15 በመቶ ነው፡፡  የፖሊሲ ወለድ ተመን በመባል የሚታወቀው ይህ ወለድ የንግድ ባንኮች የብድር ወለድ የመነሻ ተመን ሆኖ ያገለግላል፡፡

#ለማስታወስ፦ የንግድ ባንኮች የብድር ወለድ በባንኮቹ እና በደንበኞች መካከል በድርድር የሚወሰን ነው።


ትዮጵያ ሪፎርም #ከባድ እና #ጊዜ_የሚወስድ ነው ፤ እባካችሁ ታገሱ ብሏል IMF! ዳይሬክተሯ የሰጡት 7 ቁልፍ አስተያየት እና ተማፅኖዎች!

ዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም (IMF) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ ትናንት እና ዛሬ እሁድ ኢትዮጵያ ውስጥ ናቸው!

በዚህም ወቅት ከጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር ጨምሮ ከፌዴራል ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር መክረዋል።

የነበራቸውን ቆይታ በተመለከተ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ጋር በጋራ መግለጫ ዛሬ ሰጥተው ነበር።

ዳይሬክተሯ ከተናገሯቸው መካከል....

"የኢትዮጵያ ሪፎርም #ከባድ እና #ጊዜ_የሚወስድ ነው ፤ እባካችሁ ታገሱ" ከሚል ተማፅኖ ጀምሮ 7 ቁልፍ ጉዳዮችን አንስተዋል! እንመልከታቸው ...https://youtu.be/uX2Xp22xZVU


ቢመርም መዋጥ ያለበት ግልፅ እውነት አለ!

በብዙ መለኪያ አሜሪካንን እንደ ማንኛውም አንድ ሀገር ቆጥሮ መኖር አይቻልም/አልተቻለም!

አሜሪካን ስለፈቀደች ብቻ የሚፈርሱ፤ የሚራቡ እና የሚያድጉ ሀገራት ቁጥር ብዙ ነው!

ለብዙ ሀገራት ከአሜሪካን ጋር መጣላት ምርጫ የሌለው ከፍተኛ የህልውና አደጋቸው ነው!

ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ብትጣላ IMF ወዳጇ/የሪፎርም ደጋፊዋ ሆኖ መቀጠል ይችላል?

የኢትዮጵያን ሁኔታ በአስተያየት እንኳን ከአሜሪካን ድጋፍ ለመላቀቅ ፍፁም ከባድ ነው!

በዓለም ላይ ከ1945 ጀምሮ የአሜሪካ ኢኮኖሚዊ፤ ዲፕሎማሲያዊ እና ፖለቲካዊ ተፅዕኖ በብዙ ምሳሌ ጠለቅ አድርገን እንመልከት.....https://youtu.be/8uvq8zcnvfs


2017 ግማሽ ዓመት የባንኮች አፈጻጸም ሪፖርት ተዘጋጅቷል፡

የኢትዮጵያ ባንኮች በ6 ወር ውስጥ ያገኙት የውጭ ምንዛሬ መጠን፤ ባንኮቹ ያላቸው የደንበኞች ቁጥር፤ አጠቃላይ ያላቸው የሀብት መጠን፤ የሰጡት የብድር መጠን፤ ባንኮቹ ያላቸው የተቀማጭ ገንዘብ መጠን፤ የቅርንጫፎች ብዛት፤ በደረጃ እና በዝርዝር ቀርቧል!

ለምሳሌ፡-

በኢትዮጲያ የተቀማጭ ሃሳብ ደንበኞች ቁጥር ከሀገሪቷ ህዝብ በ50 ሚሊየን ይበልጣል!

የ1 የመንግስት የንግድ ባንክ ድርሻ የግል ባንኮችን ድምር ያክላል!

የ4 የግል ባንኮች ድርሻ የግል ባንኮችን ግማሽ የፋይናንስ ድርሻ ይይዛሉ!

የሪፖርቱን ዝርዝር መረጃ ለመመልከት...https://youtu.be/sklEvUhCbeI


ገና ያስጨንቁናል! አሜሪካ ለራሷ ስታስብ ዓለም ለምን ተጨነቀ? ትራምፕ የተማሩትን ኢኮኖሚክስ እየተገበሩት ነው!

ትራምፕ እና አዲሷ አሜሪካ ምክንያታዊ ያልሆነ ማንኛውም የአስተዳደር ወጪ እና የውጪ እርዳታ አይኖርም እያሉ ነው።

የአሜሪካ ውሳኔ ከሃብታም እስከ ድሃ ሀገራት አስጨናቂ ሆኗል! ለምን?

ወደኋላ ከተመለከትን ትራምፕ የመጀመሪያ ድግሪ ወደያዙበት የኢኮኖሚክስ አስተምህሮት እያዘነበሉ ይመስላል!

እስቲ ሁላችንንም የሚነኩ የኢኮኖሚ ውሳኒያቸውን እንመልከት....https://youtu.be/Br5xQNXY7J0

Показано 20 последних публикаций.