Ministry of Education Ethiopia


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Образование


This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Образование
Статистика
Фильтр публикаций


የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተልዕኮ ማስፈጸሚያ ቁልፍ የተግባር አመላካችና የአገልግሎት ጥራትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው።
--------------------------------------------------
(የካቲት 26/2017 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስቴር ከሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች እንደ መነሻ ያሰባሰባቸውን 91 ቁልፍ የተግባር አመላካችና የአገልግሎት እርካታ ትንተና እና ሰነድ ዝግጅት ስራዎችን እያከናወነ ነው።

ትንተናውን መሠረት አድርጎ የሚዘጋጀው ሠነድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ቁልፍ ተግባራት አፈጻጸምና የአገልግሎት አሠጣጥ እርካታ ላይ ያለውን ጥንካሬና ክፍተት በመለየት ለቀጣይ አፈጻጸም ግብዓት የሚገኝበት መሆኑን በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ስርዓተ ትምህርትና ፕሮግራሞች ዴስክ ሀላፊ አቶ ተስፋዬ ነጋዎ ገልጸዋል።

ከሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተሰበሰቡ መረጃዎች ላይ መሠረት አድርጎ በመከናወን ላይ ያለው የትንተና እና ሰነድ ዝግጅት ተቋማቱ የቁልፍ ተግባር አፈጻጸምና የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያሉበትን ደረጃ ከማመላከት ባለፈ በቀጣይ ያለባቸውን ሀላፊነት ከተጠያቂነት ጋር እንዴት መወጣት እንዳለባቸው የሚያመላክት መሆኑን የስራ ሀላፊው ገልጸዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር የምርምር ስነ-ምግባር ዴስክ ሀላፊ ዶ/ር አቡሌ ታከለ በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ ባደረጉት ገለጻ የተሰበሰቡ መረጃዎችን መሠረት አድርጎ የሚከናወነው ትንተና እና ሰነድ ዝግጅት ቁልፍ የተግባር አመላካቾችን ለማጥራትና የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ደረጃን ለማሳደግ የሚያግዝ መሆኑን አመላክተዋል።

የትምህርት ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር የተፈራረመውን የቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያ ስምምነት አፈጻጸም የሚደግፉ በርካታ የሪፎርም ስራዎች እያከናወነ መሆኑ በመርሃ ግብሩ ላይ ተገልጿል።


የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብር የትምህርት ተሳትፎና ጥራት ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተገለጸ፡፡
------------------------------------------------
የካቲት 26 /2017 ዓ.ም 10ኛው የአፍሪካ የትምህርት ቤት ምገባ ቀን በሐረሪ ብሔራዊ ክልል መንግስት በሐረር ከተማ በሚገኘው ሞዴል አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከብሯል።

በክብረበዓሉ ላይ የተገኙት የሐረሪ ብሔራዊ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ኦርዲን በድሪ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም መርሃ-ግብሩ የመማር ማስተማር ሂደቱን ይበልጥ ውጤታማ በማድረግና የትምህርት ተሳትፎ እና ጥራትን ከማሳደግ ባለፈ የትምህርት ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ እንደሚያግዝም ጠቁመው መርሃ-ግብሩ ከሚሰጠው ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አንጻር ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት መሆኑን ጠቅሰዋል። ከመርሃ-ግብሩ አንጻር በክልሉ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብር በለውጡ መንግስት ትኩረት ተሰጥቶት ቀጣይነት ባለው መልኩ በስፋት ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኝና ውጤት እያስመዘገበ ያለ መርሃ-ግብር መሆኑን ገልጸዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://www.facebook.com/share/p/1CNAcDWr4w/


የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲት የህክምና ፋከልቲ ተማሪዎች ምረቃ ያደረጉት ሙሉ ንግግር ፤ ይህንን ሊንክ በመጫን ማግኘት ይችላሉ፤ https://moe.gov.et/resources/others/5


በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቤተ-ሙከራዎች ውስጥ የሚገኙት መጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈባቸው ኬሚካሎች ቆጠራ በመካሄድ ላይ መሆኑ ተገለጸ።
----------------------------------------------
በትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት መሪ ሥራ አስፈጽሚ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቤተ-ሙከራዎች ውስጥ የሚገኙት መጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈባቸው ኬሚካሎች ቆጠራ በመካሄድ ላይ መሆኑ ገልጿል፡፡

የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች ተጠባባቂ መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰራዊት ሃንዲሶ(ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ሥራ ክፍሉ በ2017 ዓ.ም በአቅድ ከያዛቸው የሪፎርም ስራዎች መካከል አንዱ የምርምር ግብዓቶችንና ፋሲሊቲዎችን በማሻሻል የቤተ-ሙከራ ስታንዳርዳይዜሽንን እና አክሬዲቴሽን ስርዓትን መዘርጋት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

አክለውም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚገኙ የኢንዱስትሪ፤ የምርምር እና የላብራቶሪ ኬሚካሎች አያያዝ፤ ክምችትና የማጓጓዝ ሂደትና የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸውን ኬሚካሎች የቆጠራ ሥራ ለመሥራት እንዲቻል ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አካዳሚክ ቴክኒካል ረዳት ባለሙያዎች ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም ይህ ሥራ የሚሰራው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ብቻ ሳይሆን በአቅራቢያቸው በሚገኙ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ስር ባሉ ቤተ-ሙከራዎች ውስጥ የሚገኙትን ኬሚካሎች ምንጭ፣ አይነት፣ ደረጃ፣ መጠን እና ባህሪይ የማወቅ መረጃ የማሰባሰብ ሥራ እንደሚሰራም ሃላፊው ጨምረው ገልጸዋል፡፡


በደቡብ ምዕራብ ቀጣና የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ስፖርት ውድድር ተጠናቀቀ።
--------------------------------

(የካቲት 24/2017 ዓ.ም) በጅማ ከተማ አስተናጋጅነት ሲካሄድ የቆየው በደቡብ ምዕራብ ቀጣና ስር የተደለደሉ የጅማ ዞን ት/ቤቶች ስፖርት ሊግ ውድድር ተጠናቀቀ፡፡

በጅማ ዞን ስር የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ውድድር ፍጻሜውን ሲያገኝ በወንደች እግር ኳስ ሰቃ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ናዳ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን 5 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የዋንጫ ተሸላሚ ሲሆን በወንዶች ቮሊ ቦል ደግሞ ቀርሱ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ስግሞ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን 3 ለ1 በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት ሆኗል፡፡

በሴቶች ቮሊ ቦል ዶዮ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት አሌ ትምህርት ቤትን 3 ለ 0 በማሸነፍ የዋንጫ አሸናፊ ሆኗል፡፡
በአትሌትክስ ስፖርት ብዙ ሜዳሊያዎችን የሰበሰበው ማና ወረዳ ትምህርት ቤቶች የአጠቃላይ አሸናፊ በመሆን የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል፡፡

ውድድሩም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ጎልተው የወጡበትና በየስፖርት ዓይነቱ ጥሩ ስፖርታዊ ክህሎት ያላቸው ተማሪዎች የታዩበት የውድድር መድረክ ሆኖ መጠናቀቁ ተገልጿል፡


በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰሩ ጥናትና ምርምሮች ተገቢውን ሥነ-ምግባር የተከተሉና የህብረተሰቡን ችግሮ የሚፈቱ ሊሆኑ እንደሚገባ ተጠቆመ።
------------------------------------
(የካቲት 22/2017 ዓ.ም) በትምህርት ሚኒስቴር በጥናትና ምርምር ሥነ ምግባር ላይ ያተኮረ ሥልጠና ለመንግስትና ለግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሰጥቷል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ተጠባባቂ መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰራዊት ሀንዲሶ (ዶ/ር) በሀገራችን የከፍተኛ ትምህርት ታሪክ በርካታ ጥናትና ምርምሮች ቢሰሩም ህብረተሰቡ ላይ ያመጡት ለውጥ ግን የሚጠበቀውን ያክል አይደለም ብለዋል።

እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ እንዳልሂነም ገልጸዋል።

ጥራት ያለው ጥናት ለመስራትና ለሳይንስ ያለን እይታ እንዲጨምር የምንፈልግ ከሆነ በቅንጅት መስራት ያስፈልጋልም ብለዋል።

በዚህም የሚሰሩ ምርምሮች ተገቢውን ስነምግባር የተከተሉ፣ የህብረተሰቡን ችግር የሚፈቱና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሊሆኑ እንደሚገባም አሳስበዋል።

በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ እዮብ አየነው (ዶ/ር) በበኩላቸው ትምህርት ሚኒስቴር በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሪፍርሞችን ቀርፆ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል ብለዋል።

በዚህም በመንግስትም ሆነ በግል ተቋማት የሚሰሩ ጥናትና ምርምሮች ከመመረቂያነት ባለፈ ጥራት ያላቸው ችግር ፈቺ እንዲሆኑ ለማድረግና ወጥ የሆነ አሰራር ሥርዓትን ለመከተል እንዲቻል ይህ ስልጠና መዘጋጀቱን ገልፀዋል።

በስልጠናው ከመንግስትና ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተወከሉ ምሁራን ተሳታፊ ሆነዋል።


ተማሪዎች ሰለስራ ቅጥርና ፈጠራ ያላቸውን ግንዛቤ ለማሳደግ እየተሠራ ነው።
------------------------------------------
(የካቲት 22/2017 ዓ.ም) በቅርቡ በትምህርት ሚኒስቴር እና በኢንፎ ማይንድ ሶሊሽን መካከል የተፈረመውን የትብብር መግባቢያ ስምምነት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተከናውኗል።

የኢፊዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ በትብብሩ ፕሮግራም ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት የስራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

ሚንስትር ዴኤታው በማያያዝም ዜጎች በሀገሪቱ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ከራሳቸው ባለፈ ለሀገራቸው አበርክቶ እንዲኖራቸው የትምህርት ዘርፉና ተባባሪ አካላት ሚናቸው የጎላ በመሆኑ ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ኤባ ሜጄና በበኩላቸው የትብብር ፕሮግራሙ ተማሪዎች በትምህርት ቆይታቸውም ይሁን ወደ ስራው አለም ሲቀላቀሉ የሚያስፈልጓቸውን ክህሎቶች እንዲገነቡ የሚያግዝ በመሆኑ የትምህርት ዘርፉ አስፈላጊውን ጥረትና ድጋፍ እንደሚያደርግ አብራርተዋል።

በዚህም በቀጣይ በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስራ ቅጥርና ፈጠራ ማጎልበቻ ማዕከላት እንደሚገነቡ ገልጸዋል።

የኢንፎ ማይንድ ሶሊሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ የሱፍ ረጃ በበይነ መረብ ባስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት የከፍተኛ ትምህርት ምሩቃን በስራ ቅጥርና ፈጠራ እንዲሁም በሌሎች ተያያዥ ጉዳዬች ላይ ያላቸውን አቅም ለማጎልበት በሚደረገው ርብርብ ውስጥ ተቋማቸው ሚናውን እንደሚወጣ አብራርተዋል።


የትብብር መርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ የሀገሪቱን የስራና ቅጥርና ፈጠራ ነባራዊ ሁኔታ የተመለከቱ ጥናቶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።


በተለያዩ ክልሎች የመምህራንና የትምህርት አመራሮችን ብቃትና ተነሳሽነት ለማሳደግ ስልጠናዎች እየተሰጡ ነው።
---------------------------------------
የካቲት 22/ 2017 ዓ.ም በሁሉም ክልሎች በተመረጡ የስልጠና ማዕከላት እተሰጠ ያለው ስልጠና በስነ-ልቦና እና ማህበራዊ ድጋፍ፣ በስራና ተግባር ተኮር ትምህርት እና በአፍ መፍቻ ቋንቋ ትምህርት ማስተማር ስነ ዘዴ ላይ ያተኮረ ነው፡፡

የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) የስነልቦና እና ማህበራዊ ድጋፍ ስልጠና ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት ችግሮች በነበሩባቸው አካባቢዎች ለሚያስተምሩ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች እየተሰጠ ያለው ስልጠና መምህራን ተግዳሮቶችን ተቋቁመው የማስተማርና ስራቸውን በአግባቡ መምራት እንዲችሉ እንደሚያግዝ ተናግረዋል፡፡ ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://www.facebook.com/share/p/1B5iVo18oY/


የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞችና አመራሮች 129ኛውን የአድዋ ድል በዓል አከበሩ፡፡
-------------------------------------
የካቲት 21/2017 ዓ.ም) «ዓድዋ የጥቁር ሕዝቦች ድል! » በሚል መሪ ቃል ዘንድሮ ለ129ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአድዋ ድል በዓል የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞችና አመራሮች በፓናል ውይይት አክብረዋል፡፡

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በመርሃ- ግብሩ ላይ በመገኘት ባስተላለፉት መልዕክት የአድዋ ድል የመላው ጥቁር ህዝቦች ድልና የነጻነት አርማ በመሆኑ የድሉን እሴቶችና ቱሩፋቶች ለይቻላል መንፈሰ ማጎለበቻነት በመጠቀም በያዝናቸው የሥራ ዘርፎች ላይ የሚጠበቅብንን ስኬት ማስመዘግብ እንደሚገባ ተናገግረዋል፡፡

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ጨምረውም የአድዋን ድል ከማክበርና ቱሩፋቶቹንም ከመጠቀም በተጨማሪ እኛ መሥራት ያለብንን የቤት ሥራ በወቅቱ በማከናወን የሀገራችን ልማት ማፋጠን ይኖርብናል ብለዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የማህበራዊ ሳይንስ ስርዓተ ትምህርት ዴስክ ሃላፊ አቶ ኡመር ኢማም የውይይት መነሻ ያቀረቡ ሲሆን የህዝቦች አብሮ የመኖርና የመልማት እንዲሁም የሀገርን ሉዓላዊነትን የማስከበር ጉዳዮች ላይ ይህ ትውልድ ከቅድመ አያቶቹ ብዙ መማር እንደሚገባው አንስተዋል፡፡

አቶ ኡመር አክለውም የአድዋ ድል ቅድመ አያቶቻችን ብሄራቸው፣ ቋንቋቸው፣ ሀይማኖታቸው፣ባህላቸውና ሌሎች ልዩነቶቻቸው ሳይገድባቸው የሀገርን ሉዓላዊነትና አንድነት ያስከበሩ መሆኑን አብራርተው አሁን ያለው ትውልድ ከዚህ መማር እንደሚገባው ገለጸዋል።
======////======



Показано 10 последних публикаций.