ለጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች የሙያ ማሻሻያ ስልጠና ተሰጠ፡፡
--------------
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ጤና መምሪያ ጋር በተባበር ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ዙሪያ በብሄረሰብ አስተዳደሩ ለሚገኙ ለአየሁ ጓጉሳ እና ባንጃ ወረዳ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ዳንኤል አዳነ (ረ/ፕሮፌሰር)ከዩኒቨርሲቲው የትኩረት መስኮች አንዱ ማህበረሰብ አቀፍ ጤና መሆኑን ጠቅሰው ስልጠናው ከብሄረሰብ አስተዳደሩ ጤና መምሪያ ጋር በመተባበር ከማህበረሰቡ ጋር በቅርበት ለሚገናኙት የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች የተዘጋጀ የሙያ ማሻሻያ ስልጠና መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም ስልጠናው በዩኒቨርሲቲው የሙያ ማሻሻያ ማእከል (CPD) ውስጥ የተሠጠ ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ዙሪያ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች በቂ ዕውቀት እንዲኖራቸው በኮምፒውተር የታገዘ እና ስልጠና መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ CPD ማዕከል እስከ አሁን ከ110 በላይ በብሄረሰብ አስተዳደሩ ለሚገኙ ጤና ባለሙያዎች ስልጠና መሠጠቱንም ጨምረው ተናግረዋል፡፡
የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ጤና መምሪያ የጤና ኤክስቴንሽን ትብብር ኦፊሰር የሆኑት ያረጋል መብራቱ በበኩላቸው ስልጠናው ለብሄረሰብ አስተዳደሩ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች በስኳር፣ ቲቪ፣ኤች. አይ. ቪ እና መሰል በሽታዎች ዙሪያ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በኮምፒውተር የታገዘ ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡
https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid02TkrW1RM3YE23AAmhQQX1bKXmrKLb8fBWwvuU4xHrHyAZwiBSxK18YgJD5nxie6w3l/?app=fbl