ሰሌዳ | Seleda


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Другое


የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ!
ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ @Contact_officework ያናግሩን

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Другое
Статистика
Фильтр публикаций


☄️በሀገር ውስጥ የሚመረቱ የመድኃኒቶች ጥራትና ደህንነትን ለማረጋገጥ ያግዛል የተባለዉ አዲስ መመሪያ ወጣ

የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን በሀገር ውስጥ የሚመረቱ የመድኃኒቶች ጥራትና ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚያግዝ አዲስ መመሪያ አውጥቷል።

"የባዮኤክቫለንስ ጥናት ማዕከል እና የባዮአናሊቲካል ላብራቶሪ ቁጥጥር መመሪያ ቁጥር 1043/2017" ተብሎ የሚጠራው ይህ መመሪያ፣ በገበያ ላይ የሚውሉ የመድኃኒት ምርቶች ተመሳሳይ የፈዋሽነት እና የደህንነት ደረጃዎችን ማሟላታቸውን ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።

በተለይም በጽንስ ስም የሚመረቱ መድኃኒቶች ከታወቁ የመድኃኒት ምርቶች ጋር ተመሳሳይ የሆነ የፈዋሽነት እና የደህንነት ደረጃ እንዲኖራቸው ለማድረግ ያለመ ነው።

ይህ መመሪያ "ባዮኢኩዊቫለንስ" የተሰኘ ልዩ ጥናት በማድረግ በጽንስ ስም የሚመረቱ መድኃኒቶች ከታወቁ የመድኃኒት ምርቶች ጋር ያላቸውን ተመሳሳይነት ማረጋገጥ እንደሚጠበቅባቸው ይደነግጋል።

በተጨማሪም፣ መመሪያው የመድኃኒት
ማምረቻ ተቋማትና ላቦራቶሪዎች ፈቃድና ቁጥጥር ላይ እንደሚያተኩር ካፒታል ለመረዳት ችሏል።

መመሪያው በኢትዮጵያ የመድኃኒት ቁጥጥር ላይ ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን፣ ለመድኃኒት ኢንዱስትሪው ዕድገት አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ይጠበቃል። በተጨማሪም፣ ለሕዝብ ተደራሽና ጥራት ያላቸውን መድኃኒቶች ለማቅረብ ያለመ ነው ተብሏል።

@seledadotio
@seledadptio


☄️ሰሌክታ ግሩፕ በፖለቲካ አለመረጋጋት ምክንያት ከኢትዮጵያ ወጣ

በስዊዘርላንድ ዋና መስሪያ ቤቱን ያደረገው ሰሌክታ ግሩፕ በሰሜን ኢትዮጵያ ኩንዚላ የሚገኘውን የምርት ማዕከሉን በፖለቲካ አለመረጋጋት እና በወታደራዊ ሁኔታዎች ምክንያት ወደ ኬንያ እና ኡጋንዳ ማዛወሩን አስታዉቋል።

ኩባንያው የዚህ ውሳኔ ምክንያት በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ለሰራተኞች ደህንነት ስጋት መፍጠሩ እና የሎጂስቲክስ ችግሮች መከሰታቸው እንደሆነ ገልጿል።

የኩባንያዉ ዋና ስራ አስፈፃሚ አንስጋር ክሌም ይህን ውሳኔ "አሳማሚ እርምጃ" ብለው የገለፁት ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ያደረጉትን ከፍተኛ ኢንቨስትመንት እና ጥረት ከንቱ መሆኑን ተናግረዋል።

ይህ ውሳኔ በኩንዚላ አካባቢ ከ1,000 በላይ የስራ እድሎችን የሚያሳጣ ሲሆን፣ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ወደ 10,000 የሚሆኑ ሰዎችን ይጎዳል። ኩባንያው ለአካባቢው ማህበረሰብ የኢኮኖሚ ህይወት መስመር እንደነበር እና መውጣቱ ትልቅ ጉዳት እንደሚያስከትል ገልጿል።

ካፒታል ያገኘዉ መረጃ እንደሚያመለክተዉ ሰሌክታ ግሩፕ በኬንያ እና ኡጋንዳ ያሉትን የምርት ማዕከላት በማጠናከር ለደንበኞች የምርት አቅርቦት እንዳይቋረጥ ማረጋገጡን ገልጿል። ወደፊት ሁኔታዎች ሲሻሻሉ ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ ተስፋ እንዳለውም አስታውቋል።

ሰሌክታ ግሩፕ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም የሆነ የአበባ እና የጌጣጌጥ እፅዋት አምራች ኩባንያ መሆኑ ይታወቃል።

@seledadotio
@seledadotio


⚡️"የሪፖርተር መረጃ የተሳሳተ ነው

ተቋሙ ምንም አይነት  አዲስ ታሪፍ ጭማሪ አልተደረገም"

ከሚያዝያ ወር ጀምሮ አዲስ የታሪፍ ማሻሻያ ተግባራዊ ሊደረግ እንደሆነ ተደርጎ በአንዳንድ የመገናኛ ብዙሃንና የማህበራዊ ሚዲያ የትስስር ገፆች እየተሰራጨ የሚገኘው መረጃ የተሳሳተ ነው።

ተቋሙ ከመስከረም  2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ4 ተከታታይ አመታት  በማኅበረሰቡ ላይ ጫና እንዳይፈጠር በየሩብ አመቱ ተከፍሎ ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘውን የታሪፍ ማስተካከያ  ከማስፈፀም ውጪ አዲስ ተግባራዊ ያደረገው የታሪፍ ማሻሻያ አለመኖሩን እንገልፃለን ብሏል።

@seledadotio
@seledadotio


☄️የኤሌክትሪክ ታሪፍ ድጋሚ የዋጋ ጭማሪ ሊደረግበት ነው

በዚህም መሠረት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከሚያዝያ እስከ ሰኔ ወር ድረስ በመኖሪያ ቤት ታሪፍ ላይ 0.50 ኪሎ ዋት ሰዓት የሚጠቀሙ ደንበኞች የፍጆታ ታሪፍ 0.60 ሳንቲም እንዲከፍሉ የሚደረግ ሲሆን፣

የአገልግሎት ክፍያ ተመንን በተመለከተ ለድኅረ ክፍያ አሥር ብር ከ95 ሳንቲም ሲከፍሉ፣ ለቅድመ ክፍያ አራት ብር ከ18 ሳንቲም እንደሚከፍሉ ሪፖርተር ያገኘው ሰነድ ያሳያል፡፡

የመኖሪያ ቤት ታሪፍን በተመለከተ ከ51 እስከ 100 ኪሎ ዋት የሚጠቀሙ ደንበኞች አንድ ብር ከ49 ሳንቲም፣ ከ101 እስከ 200 ኪሎ ዋት ሁለት ብር ከ67 ሳንቲም፣ ከ201 እስከ 300 ኪሎ ዋት የሚጠቀሙ ደንበኞች ሦስት ብር ከ84 ሳንቲም እንደሚከፍሉና በየኪሎ ዋቱ መጠን ክፍያው የሚለያይ እንደሆነ ሰነዱ ያስረዳል።

@seledadotio
@seledadotio


❗የአለም ዋንጫ ተሳታፊ አገራት ወደ 64 ከፍ ለደረግ ነው


የአለም እግር ኳስ ማህበር ፊፋ በ2030 የአለም ዋንጫ ላይ የሚሳተፉ ሀገራትን ቁጥር ወደ 64 ለማሳደግ እያጤነ እንደሚገኝ ተሰምቷል፡፡

ባሳለፍነው ረቡዕ በጀመረው የእግር ኳስ ማህበሩ ምክር ቤት ጉባኤ ላይ ኡራጓይ ያቀረበችው ሀሳብ ተቀባይነት ካገኘ ከማህበሩ አባላት አንድ አራተኛው በአለም ዋንጫ እንዲሳተፉ እድል ይፈጠራል።

በአለም አቀፍ ደረጃ ሰፊ ተከታታዮች እና ተወዳጅነት ያለው የአለም ዋንጫ በየአራት አመቱ በተለያዩ ሀገራት አዘጋጅነት ከ1930 ጀምሮ ለ22 ጊዜ ተካሂዷል፡፡

በ18 የተለያዩ ሀገራት አስተናጋጅነት የተካሄደው ውድድር ከጊዜ ወደጊዜ ከተሳትፎ እና ከአካታችነት ኮታ ጋር በተያያዘ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች ይነሱበታል።

@seledadotio
@seledadotio


⚡️ሁሉም ወንድ ዜጎቿ ወደ ወታደራዊ ስልጠና

ፖላንድ ሁሉም ወንድ ዜጎቿ በወታደራዊ ስልጠና ውስጥ እንዲያልፉ የሚያደርግ ረቂቅ ህግ ለፓርላማው አቀረበች፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶናልድ ተስክ ረቂቅ ህጉን ለፓርላማው ባቀረቡበት ወቅት በሀገሪቱ ከፍተኛ ወታደራዊ ስልጠና እንዲሰጥ ያስችላል የተባለው ዕቅድ ዝርዝር በመጪዎቹ ወራት ይፋ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡

እቅዱ ወታደራዊ ስልጠና የሚያገኙት ወንዶች በቀጥታ መከላከያ ሰራዊቱን የሚቀላቀሉ ሳይሆኑ በግጭት ወቅት ብቁ ወታደራዊ ቁመና ተላብሰው መሰለፍ የሚችሉበትን ክህሎት እንዲያገኙ የሚያደርግ ነው።

ፖላንድ በአሁኑ ወቅት 200 ሺህ ወታደሮች ያሏት ሲሆን በአቅራቢዋ ከሚገኙ ሀገራት አንጻር አነስተኛ ነው የተባለውን የሰራዊት ቁጥር ወደ 500 ሺህ ለማሳደግ አቅዳለች።

@seledadotio
@seledadotio


⚡️በአዲስ አበባ ከተማ 18 ሄክታር መሬት ለሊዝ ጨረታ ሊቀርብ ነው

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ፤ በጥቅሉ 18 ሄክታር ስፋት ያላቸው 427 ቦታዎችን ለሊዝ ጨረታ ሊያቀርብ ነው። በመዲናይቱ ዘጠኝ ክፍለ ከተሞች የሚገኙት እነዚህ ቦታዎች፤ ለመኖሪያ እና ለንግድ አገልግሎት የሚውሉ መሆናቸው ተገልጿል።

በከተማይቱ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ የመሬት ዝግጅት እና ባንክ ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ተስፋዬ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንደተናገሩት፤ ለጨረታ የሚቀርቡት ቦታዎች “በተለያየ አግባብ ወደ መሬት ባንክ የገቡ ይዞታዎች” ናቸው። በአሁኑ ዙር ጨረታ በቦሌ እና ልደታ ክፍለ ከተሞች የሚገኙ የመሬት ይዞታዎች እንዳልተካተቱ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

ለጨረታ የሚቀርቡት ቦታዎች ዝርዝር፤ በነገው ዕለት ታትሞ በሚወጣው “አዲስ ልሳን” ጋዜጣ ማግኘት እንደሚቻል የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ይህንን ተከትሎ የጨረታ ሰነድ ሽያጩ “ከእጅ ንኪኪ በጸዳ መልኩ” ከመጪው ሰኞ መጋቢት 1 እስከ መጋቢት 12 ድረስ ባሉት ቀናቶች የሚከናወን መሆኑንም ጠቁሟል።

@seledadotio
@seledadotio


✨አየር መንገዱ ዛሬ ማታ የሚጀመሩ ሁለት በረራዎችን ጨምሮ በሴቶች ብቻ የሚደረጉ 6 በረራዎች ሊያካሂድ ነው።


የኢትዮጵያ አየር መንገድ አለም አቀፉን የሴቶች ቀን አስመልክቶ በሴቶች ብቻ የሚደረግ በረራ ሊያካሂድ መሆኑን አስታውቋል።


በረራው ወደ 6 አገራት የሚደረግ ሲሆን፤ ሁለቱ ዛሬ ማታ የቀሩት አራት በረራዎች ደግሞ ነገ የሚደረጉ ናቸው።


በረራዎቹ  ከካፒፔን እስከ አየር ተቆጣጣሪ እና ቴክኒሻን ድረስ በሴቶች ብቻ የሚደረጉ መሆናቸው ተገልጿል።


ባህርዳር፣ አቴንስ፣ ዴልሂ ፣ዱባይ፣ ሳኦፖሎ እና ዊንድሆክ ከተሞች መዳረሻ ናቸው ተብሏል።


በዓለም ለ114ኛ ጊዜ በአገራችን ለ49ኛ ጊዜ የሚከበረው የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ በረራዎቹ መዘጋጀታቸው ነው የተገለፀው።


ዕለቱ "መብት፣ እኩልነት እና አቅም መጎልበት ለሴቶች በሙሉ" በሚል መሪ ቃል የሚከበር ይሆናል ተብሏል።


አየር መንገዱ አሁን ላይ 8 ዋና አብራሪ ሴት ካፒቴኖች እና 70 ምክትል ሴት አብራሪዎች እንዳሉት ተገልጿል።

@seledadotio
@seledadotio


👀የሚስቱ እግር እባብ መስሎት ከባድ ጉዳት ያደረሰው ባል

ይህ ነገር የተፈጠረው በአውስትራሊያ ከተማ ሜልበርን ሲሆን ባል ከስራ ደክሞት ወደ ቤቱ ይሄዳል

ወዲያው ቤቱ ገብቶ ወደ መኝታ ክፍል ሲገባ ሚስት ባሏን ለማማል ብላ እንደ እባብ ያለ እስቶኪንግ አድርጋ ተኝታ ነበር

ወዲያው ባል ወይኔ ጉድ ሁለት እባብ አልጋ ላይ አለ ብሎ በBaseball መምቻ እንጨቱ ቀስ ብሎ ገብቶ አንድ እግሯን ሲመታው ሚስት
"ውይ ኡኡኡ.... እኔ ነኝ" ብላ በመንቃት ሁለተኛው ሳይደግም አንደኛው ተሰብሮ ሆስፒታል ገብታለች

@seledadotio
@seledadotio

9k 0 127 197

⚡️ዲዲ አዳዲስ ክሶች ቀረቡበት

አሁን የተመሰረተበት ክስ ደግሞ ሰራተኞቹን ለረጅም ሰዓታት እንዲሰሩ በማስገደድ እና የ20 አመት ህገወጥ ዝውውር ንግዱን ያልደገፉትን በማስፈራራት ነው ተብሏል።

@seledadotio
@seledadotio


በአፋጣኝ የተኩስ ማቆም ፣ የአየር እና የባህር ላይ ጥቃቶችን ማቆም በሩሲያ እና በዩክሬን ግጭት ውስጥ በራስ የመተማመን እርምጃ ያዳብራል ለውጤታማ ድርድርም ይረዳል ሲሉ ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን ሃሳብ አቅርበዋል።

@seledadotio
@seledadotio


ማስታወቂያ‼️

የመኪና ግዢ ሂደትዎን እንዴት ቀላል ማድረግ እንደሚችሉ እያሰቡ ነው?

ትክክለኛውን መኪና በትክክለኛው ዋጋ ከትክክለኛው አከፋፋይ እንዲያገኙ እንረዳዎታለን።🔥

መኪና ለመግዛት ካሰቡ ብዙ አማራጭ እኛ ጋር ያገኛሉ እንዲሁም ለዘመናዊ መኪና ፈላጊዎች ስለሚገዙት መኪና እናማክራለን!!!

ከስር ባለው ሊንክ የቴሌግራም ቻናላችንን Join በማለት ስለመኪና ወቅታዊ ዋጋ እና መረጃ ያግኙ 👇👇👇👇👇👇
https://t.me/AbrahamDealer
https://t.me/AbrahamDealer
https://t.me/AbrahamDealer
https://t.me/AbrahamDealer

@Ab_Cars
ስለመረጡን እናመሰግናለን


❗️ትራምፕ ለኢራን መሪ ካሜኒ የኒውክሌር ስምምነትን ለመደራደር ደብዳቤ እንደላኩ ተናግረዋል

Trump says he sent a letter to Iran’s leader Khamenei to negotiate a nuclear deal

@seledadotio
@seledadotio


👀በኢትዮጲያ የአዞ ስጋ ሽያጭ ሊጀመር ነው፡፡

የአዞ ስጋን የሚያዘጋጅ እና የሚሸጥ ምግብ ቤት በአርባምንጭ ሊከፈት መሆኑን ጣቢያችን ሰምቷል፡፡

የአርባምንጭ አዞ እርባታ ስራ አስኪያጅ አቶ ዳዊት ዳኜ ለኢትዮ ኤፍ ኤም በሰጡት ማብራሪያ፤ በአርባምንጭ ከተማ የአዞ ስጋ ምግብ ቤት ለመክፈት እንቅስቃሴ መጀመሩን ገልጸዋል።

የውጪ ሃገር ቱሪስቶች የአዞ ስጋ ለመመገብ የሚጠይቁ መሆኑን የገለፁት አቶ ዳዊት፤ ጥናት ተደርጎ ከአንድ ዓመት በኋላ ሬስቶራንቱን ለመክፈት እንደታሰበም ተናግረዋል።

የውጭዎቹ ቱሪስቶች ጋር ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለ ዋና ስራ አስኪያጁ አቶ ዳዊት አንስተው ፤ አሁን ላይ በሃሳብ ደረጃ ነው ያለው ጉዳዩ ወደተግባር አልተገባም ብለዋል፡፡

በአካባቢው አዞዎቹን የሚንከባከቡ ሰዎች የአዞ ስጋ እንደሚመገቡ የሚናገሩት አቶ ዳዊት ይህም በስፋት እንደተለመደ እና አዲስ ነገር እንዳለሆነ አስተውሰዋል፡፡

የአዞ ስጋ በጣም ጣፋጭ እና መድሃኒትም መሆኑንን በጥናት አረጋግጠናል እናም በቅርቡም የአዞ ስጋ ሽያጭ በይፋ እንደሚጀመርም ገልጸዋል፡፡


2ሺ5መቶ ኦዞዎች እንዳሏቸው እና አሁንም ሰፋ ባለ መልኩ እየተፈለፈሉ መሆኑን አቶ ዳዊት ተናረዋል፡፡

@seledadotio
@seledadotio


⚡️ከ750 በላይ የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ሠራተኞች በተቋሙ ከስራ 'እንደሚሰናበቱ መገለጹና 5 ሠራተኞች መታሰራቸው' ቅሬታ አስነሳ

በማህበራት ተደራጅተው ከአስራ አምስት ዓመት በላይ ለሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ያገለገሉ ከ750 በላይ ሠራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ “በመጠየቃቸው ብቻ ዩኒቨርስቲው ከስራ ገበታቸው እንደሚያሰናብታቸው” መግለጹንና ከጥያቄው ጋር ተያይዞ ከ5 በላይ ሠራተኞች መታሰራቸውን ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ።

ለደህንነታቸው በመስጋት ስሜ ባይጠቀስ ያሉ ሠራተኛ፤ "እኔ ጽዳት ነው የምሰራው። 17 ዓመታት አገልግያለሁ። በወር 1100 ብር ነው ሚከፈለኝ። ጭማሪ ስንጠይቅ የምንከፍለው ጭማሪ የለም እናሰናብታቹኋላን አሉን። ከፈለጋችሁ መክሰስ ትችላላችሁ የሚል ምላሽ ተሰጠን" ብለዋል።

@seledadotio
@seledadotio


⚡️መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጲያ በሚል መሪ ቃል በመስቀል አደባባይ የወንጌል መርሃግብር ሊካሄድ ነዉ፡፡

የዝማሬ፣ የአምልኮ እና የወንጌል መርሀግብር የካቲት 29 እና 30 በመስቀል አደባባይ ከቀኑ 7 ሰዓት ጀምሮ እንደሚደረግ የቢሊ ግራሃም የወንጌል ማህበር አስታወቀ፡፡

የቢሊ ግራሃም የወንጌል ማኅበር በመስቀል አደባባይ ለሚያደርገው የሁለት ቀናት መርሐ ግብር መጋቢ ፍራንክሊን ግራሃም ወደ አዲስ አበባ መምጣታቸዉ ተገልጿል፡፡

ሰማሪታንስ ፐርስ ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ከ3 ሚሊየን ለሚበልጡ ሰዎች የምግብ እርዳታ ማቅረቡን እና ከ5 መቶሺህ ለሚበልጡ ሰዎች የህክምና እርዳታ መስጠቱ ተነስቷል፡፡

በተጨማሪም ከ2መቶ60ሺህ ለሚበልጡ ሰዎች ንጹህ ውሃ፣ የንጽህና መጠበቂያ ግብዓቶች እና አገልግሎቶች እንዳበረከተም ነዉ የተገለጸዉ፡፡

ሰማሪታንስ ፐርስ በትግራይ፣ አፋር እና አማራ ክልሎች ውስጥ ለሚገኙ 3መቶሺህ ስደተኞች እና ተፈናቃዮች ምግብ እያቀረበ እንደሚገኝም ተገልጿል፡፡

በትግራይ እና አማራ ክልሎች ውስጥ ከ52 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ተንቀሳቃሽ የሕክምና አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝም በመግለጫዉ ወቅት ተነስቷል፡፡

ድርጅቱ ከኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ከተማ በቆሼ የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ቦታ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች የሚደረግ ድጋፍ መኖሩም በመግለጫው ወቅት ተገልጿል፡፡

@seledadotio
@seledadotio


ፒያሳ❗️ፒያሳ❗️ፒያሳ❗️ፒያሳ
   ጊወርጊስ አደባባይ ፊትለፊት

#ቴምር ሪልስቴት(የንግድ ሱቅ)
4,235ካሬ ላይ ያረፈ ግዙፍ የገበያ ማዕከል በ18ወር የሚረከቡት ከ20ካሬ ጀምሮ የንግድ ሱቆች በሽያጭ ላይ ነን

የ20ካሬ ሱቅ ጠቅላላ ዋጋ👇👇👇
🏪4th & 5th floor=3,900,000ብር
  ቅድመ ክፍያ=900,000ብር
🏪3rd Floor=4,200,000ብር
   ቅድመ ክፍያ=1,200,000ብር
🏪2nd Floor=4,800,000ብር
   ቅድመ ክፍያ=1,500,000ብር
🏪1st Floor=5,500,000ብር
   ቅድመ ክፍያ=2,000,000ብር
🏪Ground Floor=7,000,000ብር
   ቅድመ ክፍያ=2,800,000ብር

#ቴምር ሪልስቴት(አፓርታማ)
🎅ፒያሳ ኢኖቬሽን ሚኒስቴር ፊትለፊት(ሊሴ ት/ቤት ጀርባ) አፓርታማ ሽያጭ

🧲66ካሬ-142ካሬ(1መኝታ-3መኝታ) 10% ቅድመ ክፍያ ብቻ ቀሪ ክፍያ በ18ግዜ ዙር በ3አመት ተከፍሎ ይጠናቀቃል

👉30% እና ከዛ በላይ ለሚከፍል ከከፈሉት ላይ 25% የሚደርስ ቅናሽ አዘጋጅተናል!!
❗️በኢትዮጵያ ብር ብቻ የሚዋዋሉት!!!
    
    ፈጥነው ይደውሉ
   📞+251926172402 / +251951513585

#temerrealestate #apartment #AddisAbabaApartments #realestateinethiopia


☄️አሜሪካ ዘለንስኪን ለመተካት ከተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች ጋር በድብቅ ውይይት መጀመሯ ተሰማ

የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ደጋፊዎች የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮለደሚር ዘለንስኪን ከሚቃወሙ የፖለቲካ መሪዎች ጋር ሚስጥራዊ ውይይት መጀመራቸው ተነግሯል፡፡

ዋሽንግተን በዩክሬን ምርጫ እንዲደረግ ግፊት እያደረገች መሆኗን ተከትሎ ነው ፕሬዝዳንት ዘለንስኪን ሊተኩ ከሚችሉ የፖለቲካ ሰዎች ጋር ነው እየመከረች የምትገኘው።

ቮለድሚር ዘለንስኪ በአሁኑ ወቅት በሀገራቸው ዜጎች ያላቸው የተቀባይነት ደረጃ 44 በመቶ ነው።

@seledadotio
@seledadotio


⚡️በወርቅ ማምረት ሥራ ላይ የተሠማሩ የ32 አምራቾች ፈቃድ መሰረዙ ተገለፀ


በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል፣ የማዕድን ዘርፉ አፈጻጸም አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የክልሉ ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ኤጀንሲ አስታውቋል።

በክልሉ ከሚገኙ 58 ልዩ አነስተኛና 12 ባሕላዊ የወርቅ አምራቾች መካከል አፈጻጸማቸው ደካማ የሆኑት 32ቱ ፈቃዳቸው መሰረዙ ተገለጿል ።

የክልሉ የማዕድንና ኢነርጂ ልማት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ገብረማርያም ሰጠኝ በስድስት ወራት ውስጥ ምንም ዓይነት ወርቅ ማምረት ያልቻሉ 12 ልዩ አነስተኛና ሁለት ባሕላዊ አምራቾች አሉ። አሳማኝ ምክንያት ካላቀረቡ በቀጣይ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው አስጠንቅቀዋል።

በድንጋይ ከሰል ማምረት ፍቃድ ከወሰዱ ከ20 በላይ ባለፍቃዶች መካከል፣ እስካሁን ወደ ማምረት የገቡት ስምንት ብቻ መሆናቸው ተጠቁሟል።

በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት 150 ኪሎ ግራም ወርቅ ለማምረት ታቅዶ 75.525 ኪሎ ግራም፣ እንዲሁም 100 ሺህ ቶን ድንጋይ ከሰል ለማምረት ታቅዶ 50 ሺህ ቶን ብቻ ማምረት መቻሉ ተነገረ ሲሆን የምርት እጥረቱ ምክንያት ሕገወጥነት እና ወደ ሥራ ያልገቡ አምራቾች መኖራቸው እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል ሲል ካፒታል ዘግቧል ።

@seledadotio
@seledadotio


☄️የባንክ ተሽከርካሪ በመገልበጡ በሚሊየን የሚቆጠር ገንዘብ ተበተነ

የሶርያ ማእከላዊ ባንክ ተሽከርካሪ በመገልበጡ በሚሊየን የሚቆጠር ገንዘብ መበተኑ ሳያንስ የበተነውን እንደ እቃ ለመሰብሰብ ባካባቢው የነበሩ ሰዎች እንዲተባበሩት ማድረጉ እያስገረመ ነው።

ከአመታት ጦርነት በኋላ የመንግስት ሽግግር ላይ የምትገኘው ሶርያ ማእከላዊ ባንክ የሆነ ተሽከርካሪ አንድ ጎማው ፈንድቶ የመገልበጥ አደጋ ሲገጥመው በውስጡ ይዞት የነበረው በሚሊየኖች የሚቆጠር የሶርያ ፓውንድ መበተኑ ተዘግቧል።

አሽከርካሪው እንዳልተጎዳ የተገለፀ ሲሆን። እዚም እዚያ የተበተነውን ገንዘብ ለመሰብሰብ ባካባቢው የነበሩ ሰዎች መሳተፋቸው አጀብ አሰኝቷል።

በምስሉም ላይ የታሰረ ገንዘብ ጨምሮ የተበተነውን የሶርያ ፓውንድ ሰዎች ሲለቅሙ ይታያል።

ከሶርያ የወጡ ዘገባዎች እንደገለፁት ገንዘቡ ለሰራተኞች ደሞዝ ለመክፈል ሲጓጓዝ የነበረ መሆኑ ተዘግቧል::

@seledadotio
@seledadotio

Показано 20 последних публикаций.