ሰሌዳ | Seleda


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Другое


የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ!
ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ @Contact_officework ያናግሩን

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Другое
Статистика
Фильтр публикаций


❗️አትሌት ቀነኒሳ ራሱን አገለለ

አንጋፋው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ከለንደን ማራቶን ራሱን ማግለሉን አስታወቀ፡፡

ቀነኒሳ ሲናገር ‹‹የፊታችን እሁድ በሚከናወነው የለንደን ማራቶን ላይ ለመሳተፍ ቀን እየቆጠርኩ ነበር›› ብሏል፡፡ ጨምሮም ‹‹ይሁንና በልምምድ ላይ ባጋጠመኝ ጉዳት የተነሳ በዘንድሮው ውድድር ላይ ልሳተፍ አልቻልኩም፡፡

በመላው አለም የምትገኙ አድናቂዎቼና ደጋፊዎቼ በሙሉ ለምትሰጡኝ ማበረታታቻ አመሰግናለሁ›› ያለው ቀነኒሳ በውድድሩ ለሚሳተፉ አትሌቶች መልካም እድል ተመኝቷል፡፡

@seledadotio
@seledadotio


👉📌 40%ልዩ ቅናሽ ! 🫵
💥 📍 ሳር ቤት ላይ 💥
ከ 91- 130 ካሬ
2 መኝታ (91)=5,842,200 ብር
3 መኝታ (130 )=8,346,000 ብር

ከ 10% ቅድመ ክፍያ ጀምሮ

💥ሙሉውን ከከፈሉ በካሬ 64,200 ብር

💥ከፍለው እስኪጨርሱ በዶላርም ሆነ በግንባታ እቃዎች ግሽበት ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ አናደርግም!

💥ቶሎ ይደውሉ ለ 20 ቤቶች ብቻ ነው

ቴምር ሪልስቴት

ከሀገር ውጪ ለምትኖሩ ባላችሁበት ሆናችሁ መግዛት የምትችሉበትን አማራጭ ይዘን ቀርበናል

ለበለጠ መረጃ በቀጥታ ወይም በዋትሳፕ ዋናው ቢሮ ይደውሉ
☎️ +251991130089 / +251969691209


⚡️በኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6.2 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ መደረሱ ተሰምቷል

በዛሬው እለት በቱርክ 6.2 በሬክተር ስኬል የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የሀገሪቱ የአደጋ እና የድንገተኛ አደጋ አስተዳደር ባለስልጣን (AFAD) አስታወቋል።

የመሬት መንቀጥቀጡ በኢስታንቡል እና በአጎራባች አካባቢዎች በጠንካራ ሁኔታ የተሰማ ሲሆን ይህም ነዋሪዎች በፍርሃት ህንጻዎችን ለቀው እንዲወጡ አድርጓል ሲል አናዶሉ ዘግቧል።

የኢስታንቡል ገዥ ፅህፈት ቤት “እስካሁን ምንም አይነት የጉዳት ሪፖርት አልደረሰም ፡፡ የሚመለከታቸው ክፍሎቻችን የመስክ ቅኝት ጥረታቸውን ቀጥለዋል” ብሏል።

የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን “መልካም ምኞቴን ለዜጎቻችን አቀርባለሁ፣ ጉዳዩን በቅርብት እየተከታተልን ነው” ብለዋል።
@seledadotio
@seledadotio


⚡️የትራምፕ ልዩ መልዕክተኛ ከፑቲን ጋር ለመነጋገር ወደ ሩሲያ ይጓዛሉ

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ልዩ መልእክተኛ ዊትኮፍ ከፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በዩክሬን ስላለው ጦርነት ለመደራደር በዚህ ሳምንት ወደ ሩሲያ እንደሚጓዙ ዋይት ሀውስ ማክሰኞ አረጋግጧል፡፡

ክሬምሊንም ልዩ መልእክተኛው በዚህ ሳምንት ሞስኮን ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል ሲል አስታውቋል፡፡

የዋይት ሀውስ ቃል አቀባይ ካሮሊን ሌቪት ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት "ወደ ትክክለኛው አቅጣጫ እየተጓዝን ነው ብለን ተስፋ እናደርጋለን። እናም ልዩ መልዕክተኛው ስቲቭ ዊትኮፍ በዚህ ሳምንት ወደ ሩሲያ እንደገና በማቅናት ከቭላድሚር ፑቲን ጋር መነጋገራቸውን ይቀጥላሉ" ብለዋል።

ትራምፕ ከሦስት ዓመታት በላይ የዘለቀውን ጦርነት ለማቆም በዚህ ሳምንት ሩሲያ እና ዩክሬን ከስምምነት ላይ ሊደርሱ የሚችሉበት "በጣም ጥሩ ዕድል" እንዳለ ሰኞ መናገራቸውን አናዶሉ አስታውሷል፡፡

ሚያዚያ ሶስት ፑቲን እና ዊትኮፍ ከዩክሬን ጋር ስላለው ግጭት አፈታት ዙሪያ 4 ሰአት ከ50 ደቂቃ የፈጀ ውይይት ማድረጋቸው የሚታወስ ነው ፡፡

@seledadotio
@seledadotio


💯ማስታወቂያ

የመኪና ግዢ ሂደትዎን እንዴት ቀላል ማድረግ እንደሚችሉ እያሰቡ ነው?

ትክክለኛውን መኪና በትክክለኛው ዋጋ ከትክክለኛው አከፋፋይ እንዲያገኙ እንረዳዎታለን።

መኪና ለመግዛት ካሰቡ ብዙ አማራጭ እኛ ጋር ያገኛሉ እንዲሁም ለዘመናዊ መኪና ፈላጊዎች ስለሚገዙት መኪና እናማክራለን!!!

ከስር ባለው ሊንክ የቴሌግራም ቻናላችንን Join በማለት ስለመኪና ወቅታዊ ዋጋ እና መረጃ ያግኙ
⬇️
https://t.me/AbrahamDealer
https://t.me/AbrahamDealer
https://t.me/AbrahamDealer
https://t.me/AbrahamDealer

@Ab_Cars
ስለመረጡን እናመሰግናለን


የጋና ፕሬዝዳንት ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ዋና ዳኛን አገዱ

የጋና ፕሬዝዳንት ጆን ማሃማ የሀገሪቱን ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዋና ዳኛ ከስራ አግደዋል፡፡ ይህ እርምጃ በሀገሪቱ ታሪክ የመጀመሪያ ነው።

ዳኛዋ ገርትሩድ ቶርኮርኖ ለመታገድ ያበቃቸው በዝርዝር ያልተነገሩ ሶስት ክሱች ቀርበው ምርመራ መጀመሩን ተከትሉ ነው፡፡

በጋና ውስጥ ያሉ ዋና ዳኞች የስልጣን ዋስትናን ያገኛሉ ፡፡ ከስራቸው ሊያሳግዳቸው የሚችለው ጥቂት ምክንያቶች ብቻ ሲሆኑ እነሱም የብቃት ማነስ እና የባህሪ ችግር ናቸው ይላል የቢቢሲ ዘገባ ።

የአቤቱታዎቹ ይዘት ለህዝብ ይፋ አልተደረገም፡፡ ዳኛዋም እስካሁም ምንም አስተያየት አልሰጠችም ፡፡ ይሆን እንጂ የጋና የቀድሞ ጠቅላይ አቃቤ ህግ እገዳው የፍትህ ስርዓቱን ለማዳከም የተደረገ ሙከራ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

"በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ በፍትህ አካላት ፣ በዚህች ሀገር ህገ-መንግስታዊ ስርዓት በዳኝነት ነፃነት ላይ የተደረገ ትልቁ ጥቃት ነው።"ብለዋል የቀድሞው ጠቅላይ አቃቤ ህግ፡፡

@seledadotio
@seledadotio


"የተደረገው የስልጣን ሽግግር ጠቅላይ ሚንስትሩ በተገኙበት በትግራይ መቐለ ቢሆን ትልቅ ትርጉም ይኖረው ነበር" ጌታቸው

አቶ ጌታቸው ረዳ በመቀሌ ከጄኔራል ታደሰ ወረደ የቀረበላቸውን የምስጋናና የሽኝት መርሐግብር ግብዣ ውድቅ አደረጉ


የጠቅላይ ሚንስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት አቶ #ጌታቸው_ረዳ የሹመት ስልጣናቸውን ካገኙ በኃላ ቃለ-መጠይቅ ሰጥተዋል።

ሚንስትሩ UMD ለተባለ ሚድያ በትግርኛ ቋንቋ በሰጡት ቃለ-መጠይቅ "በትግራይ የተደረገው የስልጣን ሽግግር የትግራይ ህዝብን ደህንነትና ህልውና የሚያስጠብቅ አይደለም" ብለውታል።

የኢፌዱሪ ጠቅላይ ሚንስትር ለድህንነታቸው ያደረጉትን ጥንቃቄ እውቅና በመስጠት ያመሰገኑት አቶ ጌታቸው፤ በማንኛውም መመዘኛ የትግራይ ህዝብ መልሶ ወደ ጦርነት እንዳይገባ የቻሉትን ሁሉ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል።

የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ከጫፍ እንዲደርስ አበክረው እንደሚሰሩ ገልፀው "በትግራይ ክልል የተጀመረው የለውጥ ፍላጎት ወደ ኋላ የሚጎትት ማንኛውም እንቅስቃሴ ተቀባይነት የለውም፤ አይሳካም" ብለዋል።

ትግራይ ላይ እሳቸውን ለመግደል የተሸረበ ሴራ እንደነበር፤ ይህንንም ሸሽተው ከትግራይ ፓለቲካ የመውጣት አንዳች ፍላጎት እንደሌላቸው ተናግረዋል።

"የተደረገው የስልጣን ሽግግር ጠቅላይ ሚንስትሩ በተገኙበት በትግራይ መቐለ ቢሆን ትልቅ ትርጉም ይኖረው ነበር" ያሉት አቶ ጌታቸው፤ "ትላንትን እየመዘዙ ቁርሾና ቂም በቀል ማቀጣጠል ፋይዳ የለውም" በማለት ተናግረዋል።

"እኔን በክብር መሸኘት ቅድሚያ የሚሰጠው አይደለም። ቅድሚያ የሚሰጠው በትግራይ ክልል የሰፈነው ህግ አልባ አካሄድ እንዲስተካከል መስራት ነው" ሲሉ አክለዋል።

"የትግራይ ህዝብ የሰጠኝ ክብርና እውቅና  ከፍተኛ ነው፤ ከዚህ ክብርና እውቅና በላይ የምመኘው የምስጋና መድረክ የለም" ሲሉ የገለፁ ሲሆን፤ በአዲሱ የክልሉ ጊዜያዊ ርዕሰ መስተዳድር የቀረበላቸውን የምስጋናና የክብር የሸኝት ፕሮግራም እንደማይቀበሉት አሳውቀዋል።

በክልሉ ያሉ ሌቦችና ህገወጦች አደብ ለማስገዛት ለሚደረገው ጥረት እንደሚያግዙ ህዝቡ ለማገለገል እንደ ትናንት ዛሬም ዝግጁ እንደሆኑም ገልፀዋል

@seledadotio
@seledadotio


የአሜሪካው ፔንታጎን ፣ በሱማሊያ የባሕር ግዛት ውስጥ በኹለት ጀልባዎች ላይ ሚያዝያ 8 ቀን የአየር ጥቃት መፈጸሙን ዛሬ ባወጣው መረጃ ገልጧል።

ፔንታጎን በጀልባዎቹ ላይ የአየር ጥቃቱን የፈጸመው፣ ጀልባዎቹ "የተራቀቁ የጦር መሳሪያዎችን" ወደ አልሸባብ በማጓጓዝ ላይ እንደኾኑ ስለደረሰበት እንደኾነ ጠቅሷል።


ፔንታጎን የጀልባዎቹን መነሻ ባይገልጽም፣ የየመን ኹቲዎች ለአልሸባብ የተራቀቁ የጦር መሳሪያዎችን እንደሚልኩ ግን አሜሪካ ካሁን ቀደም መግለጧ አይዘነጋም።

@seledadotio
@seledadotio


በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ 🇪🇹
እድሉ እንዳያመልጦ ይፍጠኑ⚡


ያለ ኢንተርኔት 🚫🌐
በነፃ የጂም ስልጠና 🏋️
የአመጋገብ መመሪያ 🍽️
የማማከር አገልግሎት 🧖‍♀️🧘‍♂️
ሁሉም በአንድ መተግበሪያ 📲

ከታች ያለውን ሊንክ በመጠቀም  አሁኑኑ ያውርዱ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

https://play.google.com/store/apps/details?id=com.davenative.Fitawurarifitness&pli=1


☄️የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር የኢትዮጵያ ግብኝታቸውን ሰረዙ

የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ በኢትዮጵያና ኬንያ ሊያደርጉት የነበረውን ይፋዊ ጉብኝት መሠረዛቸውን የፈረንሳዩ አፍሪካ ኢንተሌጀንስ ድረገጽ ዘግቧል።

ሩቢዮ፣ በቅርቡ በጸጥታና ንግድ ዙሪያ ለመወያየት በናይሮቢ እና አዲስ አበባ ጉብኝት ለማድረግ ማቀዳቸውን የዜና ምንጩ ቀደም ሲል ዘግቦ ነበር።

ሩቢዮ ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ጋር ሊያደርጉት ያቀዱት ውይይት፣ ቻይና በኢትዮጵያ ላይ ያላትን ተጽዕኖ ለመግታት ያለመ ጭምር እንደኾነም ዘገባው ጠቅሶ እንደነበር ይታወሳል።

@seledadotio
@seledadotio


ይሄንን ሥልጣን ያላለቀ አጀንዳዬን ለማስፈፀም እጠቀምበታለሁ። ጌታቸው ረዳ

"እኔ ከትግራይ ፖለቲካ መራቅ አልፈልግም... ያላለቀ የትግራይ አጀንዳ አለ። [በአዲሱ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች ልዩ አማካሪ ሹመት] የሥራ ዝርዝር (job description) አልተሰጠኝም።

አሁን ሳስበው... የሥራ ዝርዝሩን እኔ ራሴ የምጽፈው ይመስለኛል። ...ይሄንን ሥልጣን ያላለቀ አጀንዳዬን ለማስፈፀም እጠቀምበታለሁ።

የትግራይ ህዝብ ያላለቀ አጀንዳ አለው፤ አጀንዳው እንዲያልቅ ለማድረግ እሠራለሁ። ...አሁን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ reverse ለማድረግ እሠራለሁ"

- ጌታቸው ረዳ ዛሬ በUMD የከሰጠው የትግርኛ ቃለምልልስ ላይ የተወሰደ።

@seledadotio
@seledadotio


💥40% ልዩ የበዓል ቅናሽ
💥ለ 1️⃣5️⃣ ቀን

     እጅግ ዘመናዊ አፓርትመንቶች
📍ከአፍሪካ ህብረት ሳርቤት በሽያጭ ላይ ነን!

💥ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ ብር 🇪🇹
💥ምንም አይነት የዋጋ ጭማሪ አይኖርበትም

      የካሬ አማራጮች
👉ባለ 2 መኝታ - 91 ካሬ
👉ባለ 3 መኝታ - 130 ካሬ

መገልገያዎች

📌አራት ሊፍት
📌ባለ 2 ፎቅ የመኪና ማቆሚያ ቦታ
📌ቴራስ
📌ያልተገደበ የውሃ አቅርቦት
📌የመጠባበቂያ ጀነሬተር
📌 የደህንነት ካሜራ

💥10 % ቅድሚያ ሲሆን 90% ደሞ እስከ 3 አመት ሚከፈሉት

ለበለጠ መረጃ እና ለቢሮ ቀጠሮ
☎️ +251991130089 / +251969691209


⚡️አቶ ታምራት ላይኔ የዓለም አቀፍ የብሎክቼይን አስተዳደር አማካሪ ሆነው ተሾሙ፡፡

የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒትር አቶ ታምራት ላይኔ አድማሱን የሾማቸው ኩላዳኦ የተሰኘው የክሪፕቶ ከረንሲ ድርጅት ነው፡፡

ድርጅቱ አቶ ታምራትን ለምን እንደመረጣቸው ሲገልፅ ኢትዮጵያ ከአምባገነን መንግስት ወደዲሞክራሲ በምትሸጋገርበት ወቅት የተቋማት ግንባታና እርቀ ሰላም ላይ ትልቅ ሚና በመጫወታቸው እንደሆነ አስረድቷል፡፡

ከዚህ ልምዳቸው በመነሳት አሁን ደግሞ ድርጅቱ እያደገ በመጣው አዲሱ የክሪፕቶ ገበያ በመንግስታት ውስጥ ለመስፋፋት የሚያደርገውን ጥረት ያግዛሉ የሚል እምነት እንዳለው አስታውቋል፡፡

አቶ ታምራት ላይኔ ሹመቱን ከተቀበሉ በኋላ ሲናገሩ ‹‹አስተዳዳራዊ ውድቀቶች እምነትን መልሶ በመገንባት ስራ ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እንዳላቸው የመጀመሪያ የአይን ምስክር ነኝ፡፡ ኩላ ዳኦ የአለማችን የሀብት ክፍፍል ሚዛናዊ ባልሆነበት በዚህ ዘመን ይህን ለማስተካከል የሚጥር ድርጅት በመሆኑ አብሬው ለመስራት ወስኛለሁ›› ብለዋል፡፡

ድርጅቱ በክሪፕቶ ከረንሲ አማካኝነት የተለያዩ የልማትና የእርዳታ ስራዎችን የሚያከናውን እንደሆነ በድረ ገፁ ላይ አስታውቋል፡፡

@seledadotio
@seledadotio


⚡️በሐማስ እና በእስራኤል መካከል አዲስ የተኩስ አቁም ድርድር ሊደረግ ነው

በሐማስ እና በእስራኤል መካከል አዲስ የተኩስ አቁም ድርድር ሊደረግ መሆኑን ምንጮች ለቢቢሲ ገለጹ።

ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ፍልስጤማዊ ባለሥልጣን እንዳሉት የኳታር እና የግብፅ አደራዳሪዎች አዲስ የተኩስ አቁም ድርድር እያረቀቁ ነው።

የተኩስ አቁሙ ከአምስት እስከ ሰባት ዓመታት የሚዘልቅ እንደሚሆን ምንጩ ገልጸዋል። ሁሉም እስራኤላውያን ታጋቾች ተለቀው በምላሹ በእስራኤል እስር ቤቶች የሚገኙ ፍልስጤማውያን ይለቀቃሉ።

ጦርነቱ በይፋ ቆሞ የእስራኤል ወታደሮች ሙሉ በሙሉ ከጋዛ እንዲወጡም ይደረጋል።
በጉዳዩ ላይ ምክክር ለማድረግ የሐማስ ልዑካን ወደ ካይሮ እንደሚሄዱ ተገልጿል።

ከዚህ ቀደም የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ከአንድ ወር በፊት መፍረሱ ይታወሳል። ስምምነቱ ለመፍረሱ ሁለቱ ወገኖች አንዳቸው ሌላውን ሲከሱ፣ እስራኤል ጋዛ ላይ ጥቃት መፈጸም ቀጥላለች።

ነገር ግን አዲስ ድርድር ሊደረግ ስለመሆኑ እስካሁን ከእስራኤል በኩል የተባለ ነገር የለም።

የሐማስ የፖለቲካ ክንፍ ኃላፊ ሞሐመድ ዳርዊሽ እና ዋና ተደራዳሪው ኻሊል አል-ሀያ በካይሮ ለድርድር እንደሚገኙ ተጠቁሟል።

@seledadotio
@seledadotio


በቡርኪናፋሶ መሪ ኢብራሂም ትራኦሬ ላይ ያነጣጠር የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ከሸፈ

የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራው በርካታ ወታደራዊ አባላትን ያሳተፈ እንደነበር የሀገሪቱ የደህንነት ሚኒስትር ማሃማዱ ሳና አስታውቀዋል።

የሀገሪቱ የደህንነት አገልግሎት ተቋማት የሴራው አካል በሆኑ የቡርኪናቢ ወታደሮች እና የታጣቂ ቡድን መሪዎች መካከል የነበረውን ግንኙነት በመጥለፍ የሚገኙበትን ቦታ እና የወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን ዝርዝር ሁኔታ እንዳገኙ ሚኒስትሩ ጨምረው ገልጸዋል፡፡

በቡርኪናፋሶ ፕሬዝዳንት ላይ የተሴረው መፈንቅለ መንግሥት በመጀመሪያ ሚያዝያ 8 ቀን ለማካሄድ ታቅዶ እንደነበር ሚኒስትሩ ተናግረዋል ።

@seledadotio
@seledadotio


⚡️ብሪክስ የአሜሪካን ዶላርን የሚተካ የክፍያ ሥርዓት ለመጀመር በዝግጅት ላይ መሆናቸው ተነገረ

የብሪክስ አባል ሀገራት በአለም አቀፍ ንግድ ላይ የአሜሪካን ዶላር የበላይነትን ለመገዳደር አዲስ የክፍያ ሥርዓት ለመጀመር በዝግጅት ላይ መሆናቸውን በቅርቡ ይፋ አድርገዋል።

የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ እንደተናገሩት ይህ አዲስ የክፍያ ዘዴ ከባህላዊው ሥርዓት ፈጽሞ የተለየ ሲሆን በአለም አቀፍ የፋይናንስ ገበያዎች ላይ ከፍተኛ ለውጥ ሊያመጣ ይችላል።

በተለይም የአሜሪካ ዶላር በአለም አቀፍ የንግድ ልውውጦች ውስጥ ምንም ዓይነት ሚና እንደማይኖረውና አብዛኛዎቹ የንግድ ስምምነቶች በአባል ሀገራቱ የገንዘብ ምንዛሬዎች እንደሚፈጸሙ ይጠበቃል።

ሚኒስትሩ አክለውም ይህ አዲስ የክፍያ ሥርዓት ከብሪክስ አባል ሀገራት ውጭ ላሉ ሀገራትም ክፍት እንደሚሆን አረጋግጠዋል። ይህም ማለት ማንኛውም ሀገር የአሜሪካን ዶላር ሳይጠቀም የንግድ ልውውጦችን ማከናወን ይችላል ማለት ነው።

በተጨማሪም ይህ አዲስ የክፍያ ሥርዓት በአሜሪካና በአውሮፓ ቁጥጥር ሥር ባለው የ ስዊፍት የክፍያ ሥርዓት ላይ እንደማይመሰረትና ይልቁንም ከውጭ ተጽዕኖ ነፃ የሆነ የራሳቸውን የክፍያ መድረክ ለመፍጠር እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

@seledadotio
@seledadotio


❗️የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ የታክሲ ተራ አስከባሪ ማኅበራት ከገቢያቸው 20 በመቶውን ለመንግሥት እንዲሰጡ የሚያስገድድ ደንብ አጽድቋል።

ደንቡ ማኅበራቱ “ዝግ እና መደበኛ የባንክ አካውንት" እንዲከፍቱና ከሁለት ዓመት በኋላ “ወደ ሌላ የሥራ ዘርፍ እንዲሸጋገሩ” ግዴታ ይጥላል።

“የተርሚናል አገልግሎት አሠራርና ቁጥጥር” የተሰኘው ደንብ፣ ኢንተርፕራይዝ በማለት የሠየማቸው ማኅበራት የሚደራጁት በከተማዋ የሥራና ክህሎት ቢሮ መስፈርት መኾኑን ታውቋል።

ኢንተርፕራይዞቹ 30 በመቶ “የግዴታ ቁጠባ” መቆጠብ፣ 50 በመቶውን በተንቀሳቃሽ የባንክ ሒሳብ ማስቀመጥና ያንድ ዓመት ውል መፈረም እንዳለባቸውም ይደነግጋል።

@seledadotio
@seledadotio


❗️በተለያዩ ወንጀሎች ሲፈለግ የነበረው ግለሰብ ቁጥጥር ስር ውሏል

ከዚህ ቀደም በህገ ወጥ የማዕድን ንግድ ላይ በመሳተፍ እንዲሁም በህገወጥ የጦር መሳርያን ንግድን በበላይነት ይመራ የነበረው ኃይለ ሊባኖስ ወልደሚካኤል ዛሬ ሚያዚያ 13/2017 ዓ/ም በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፍያ ቁጥጥር ስር ውሏል።

ግለሰቡ ከዚህ ቀደም ይፈለግበት ከነበረው ወንጀሎች በተጨማሪ ዛሬ ወደ ሀገር ውስጥ ሲገባ ፍቃድ የሌላቸው እና ቁጥራቸው ብዙ የሆኑ የኮሙኒኬሽን መሳርያዎችን በድብቅ ሊያስገባ ሲል በጥርጣሬ በተደረገ ፍተሻ ቁጥጥር ስር መዋሉን የመረጃ ምንጮቻችን አረጋግጠውልና። በግለሰቡ ላይ ተጨማሪ መረጃዎችን በማሰባሰብ የምናጋራችሁ ይሆናል።

@seledadotio
@seledadotio


💥40% ልዩ የበዓል ቅናሽ
💥ለ 1️⃣5️⃣ ቀን

     እጅግ ዘመናዊ አፓርትመንቶች
📍ከአፍሪካ ህብረት ሳርቤት በሽያጭ ላይ ነን!

💥ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ ብር 🇪🇹
💥ምንም አይነት የዋጋ ጭማሪ አይኖርበትም

      የካሬ አማራጮች
👉ባለ 2 መኝታ - 91 ካሬ
👉ባለ 3 መኝታ - 130 ካሬ

መገልገያዎች

📌አራት ሊፍት
📌ባለ 2 ፎቅ የመኪና ማቆሚያ ቦታ
📌ቴራስ
📌ያልተገደበ የውሃ አቅርቦት
📌የመጠባበቂያ ጀነሬተር
📌 የደህንነት ካሜራ

💥10 % ቅድሚያ ሲሆን 90% ደሞ እስከ 3 አመት ሚከፈሉት

ለበለጠ መረጃ እና ለቢሮ ቀጠሮ
☎️ +251991130089 / +251969691209


⚡️ኢትዮጵያ የብሪክስ ባንክ እድትቀላቀል ድጋፍ አገኘች


"ኢትዮጵያ ባንኩን እንድትቀላቀል በሁሉም አባል ሃገራት ድጋፍ አግኝታለች" - አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ

ኢትዮጵያ በብሪክስ የተመሰረተውን የአዲሱ የልማት ባንክ የምትቀላቀልበት ጊዜ ቅርብ ስለመሆኑ በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ገልፀዋል።

አምባሳደሩ ኢትዮጵያ ባንኩን እንድትቀላቀል በሁሉም አባል ሃገራት ድጋፍ አግኝታለች ብለዋል።

አምባሳደር ልዑልሰገድ ለኢትዮጵያ የብሪክስ አዲሱ የልማት ባንክን መቀላቀል በዚህ አመት ትኩረት ከሰጠቻቸው ነገሮች አንዱ ስለመሆኑ በማንሳት የባንኩ አባል ለመሆን የሚያስችላትን ጥያቄ ማቅረቧን ገልፀዋል።

አምባሳደሩ ኢትዮጵያ የልማት ባንኩን ከተቀላቀለች በኋላ ግብርና፣ ኢነርጂ እና ኢንዱስትሪ ቅድሚያ የምትሰጣቸው ዘርፎች መሆናቸውን ገልፀዋል።

አምባሳደር ልዑልሰገድ አክለውም ኢትዮጵያ፣ ግብፅና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን ጥቅሞች ለማስጠበቅ እየሰሩ እንደሆነ አንስተዋል።

በብሪክስ በ2014 የተመሰረተው አዲሱ የልማት ባንክ የምዕራባውያን የፋይናንስ ተቋማትን እንዲገዳደር ታልሞ የተመሰረተ ሲሆን 8 የብሪክስ አባል ሃገራትን በአባልነት ይዟል።

@seledadotio
@seledadotio

Показано 20 последних публикаций.