አዲስ አድማስ የዛሬ 25 ዓመት ስትጀመር---
አዲስ አድማስ የዛሬ 25 ዓመት ስትጀመር፣ እኔና እኩዮቼ ለዓቅመ ጋዜጣ ልንደርስ አካባቢ ነበር፡፡ እናም በሠርቶ አደር ጋዜጣ በተለጠፈ ግርግዳ የንባብ ክህሎትን ያዳበርን እኛ፣ እንዲሁም ቅዳሜን ከእኛ ጋር፣ እሁድን ላንድ አፍታ፣ ለወጣቶችና፡ የመሳሰሉትን የለገዳዲና የኢትዮጵያ ሬድዮ ፕሮግራሞች እየሰማን ላደግን እኛ፣ ከግል ጋዜጣና ሬድዮ ጋር በጥሩ የወጣትነት ዘመናችን ላይ ተገናኝተናል፤ 1990ዎቹ መጀመርያና አጋማሽ አካባቢ።
አዲስ አድማስ ጋዜጣ፣ ኤፍ ኤም 97.1፣ በኋላም ሸገር ሬድዮ በተሻለ የመዝናኛና የዕውቀት ይዘት ወጣትነታችንን ያደመቁ የዘመን ቅርሶች ናቸው።
በግሌ አዲስ አድማስን ማንበብ የጀመርኩት 1996 ዓ.ም. ላይ ነው። ችስታ ስለነበርኩ ከታተመ ሳምንት ወይም ከዚያ በላይ ያለፈው፣ ሌሎች ሰዎች ገዝተው አንብበው ሲጨርሱ በተውሶ አንብቤ በክብር እመልሳለሁ።
⬇️⬇️
አዲስ አድማስ የዛሬ 25 ዓመት ስትጀመር፣ እኔና እኩዮቼ ለዓቅመ ጋዜጣ ልንደርስ አካባቢ ነበር፡፡ እናም በሠርቶ አደር ጋዜጣ በተለጠፈ ግርግዳ የንባብ ክህሎትን ያዳበርን እኛ፣ እንዲሁም ቅዳሜን ከእኛ ጋር፣ እሁድን ላንድ አፍታ፣ ለወጣቶችና፡ የመሳሰሉትን የለገዳዲና የኢትዮጵያ ሬድዮ ፕሮግራሞች እየሰማን ላደግን እኛ፣ ከግል ጋዜጣና ሬድዮ ጋር በጥሩ የወጣትነት ዘመናችን ላይ ተገናኝተናል፤ 1990ዎቹ መጀመርያና አጋማሽ አካባቢ።
አዲስ አድማስ ጋዜጣ፣ ኤፍ ኤም 97.1፣ በኋላም ሸገር ሬድዮ በተሻለ የመዝናኛና የዕውቀት ይዘት ወጣትነታችንን ያደመቁ የዘመን ቅርሶች ናቸው።
በግሌ አዲስ አድማስን ማንበብ የጀመርኩት 1996 ዓ.ም. ላይ ነው። ችስታ ስለነበርኩ ከታተመ ሳምንት ወይም ከዚያ በላይ ያለፈው፣ ሌሎች ሰዎች ገዝተው አንብበው ሲጨርሱ በተውሶ አንብቤ በክብር እመልሳለሁ።
⬇️⬇️