"በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል በማንኛውም ቅፅበት ጦርነት ሊነሳ ይችላል"
በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል "በማንኛውም ቅፅበት ጦርነት ሊነሳ ይችላል" ሲሉ ጄኔራል ፃድቃን ገብረትንሳይ አስጠነቀቁ።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳም፤ "በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል በግልጽ የሚታይ መቃቃር አለ። የእኔ ስጋት ይህ ከቃላት አልፎ ወደ ጦርነት እንዳያድግ ነው" ብለዋል።
ጦርነቱ ለቀጠናውም ዳፋ እንደሚሆንም ጄኔራል ፃድቃን በእንግሊዝኛ ባስነበቡት ጽሑፍ አስታውቀዋል።
በሁለቱ አገራት መካከል የሚደረግ ጦርነት በሁለቱም ወገኖች እንደሚባለው "አጭርና ወሳኝ" እንደማይሆን የገለጹት ጄኔራል ፃድቃን፤ ለቀጠናው አውዳሚ እንደሚሆን ጠቅሰዋል።
"ጦርነቱ ሲያከትም አሁን የምናውቀው የአገራቱ ጂኦግራፊ ይለወጣል። በአፍሪካ ቀንድና ከቀይ ባሕር አሻግሮም ጉልህ የፖለቲካ አሰላለፍ ለውጥ ያስከትላል" ብለዋል።
በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ ያልተማከለ አስተዳደርና ዴሞክራታይዜሽን ካቢኔ ሴክሬተሪያት ኃላፊ፣ ሌተናንት ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳይ፣ በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል የሚቀሰቀሰው ጦርነት "የሱዳንና የቀይ ባሕር ደኅንነት ላይ በቀጥታ ተጽዕኖ ያሳድራል" ብለዋል።
"በጦርነቱ ማዕከላዊ የምትሆነው በደንብ የሠለጠነና ልምድ ያካበተ ከፍተኛ የወታደር ቁጥር ያላት ትግራይ ናት" ሲሉም አክለዋል፡፡ (ቢቢሲ እንደዘገበው።)
በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል "በማንኛውም ቅፅበት ጦርነት ሊነሳ ይችላል" ሲሉ ጄኔራል ፃድቃን ገብረትንሳይ አስጠነቀቁ።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳም፤ "በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል በግልጽ የሚታይ መቃቃር አለ። የእኔ ስጋት ይህ ከቃላት አልፎ ወደ ጦርነት እንዳያድግ ነው" ብለዋል።
ጦርነቱ ለቀጠናውም ዳፋ እንደሚሆንም ጄኔራል ፃድቃን በእንግሊዝኛ ባስነበቡት ጽሑፍ አስታውቀዋል።
በሁለቱ አገራት መካከል የሚደረግ ጦርነት በሁለቱም ወገኖች እንደሚባለው "አጭርና ወሳኝ" እንደማይሆን የገለጹት ጄኔራል ፃድቃን፤ ለቀጠናው አውዳሚ እንደሚሆን ጠቅሰዋል።
"ጦርነቱ ሲያከትም አሁን የምናውቀው የአገራቱ ጂኦግራፊ ይለወጣል። በአፍሪካ ቀንድና ከቀይ ባሕር አሻግሮም ጉልህ የፖለቲካ አሰላለፍ ለውጥ ያስከትላል" ብለዋል።
በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ ያልተማከለ አስተዳደርና ዴሞክራታይዜሽን ካቢኔ ሴክሬተሪያት ኃላፊ፣ ሌተናንት ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳይ፣ በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል የሚቀሰቀሰው ጦርነት "የሱዳንና የቀይ ባሕር ደኅንነት ላይ በቀጥታ ተጽዕኖ ያሳድራል" ብለዋል።
"በጦርነቱ ማዕከላዊ የምትሆነው በደንብ የሠለጠነና ልምድ ያካበተ ከፍተኛ የወታደር ቁጥር ያላት ትግራይ ናት" ሲሉም አክለዋል፡፡ (ቢቢሲ እንደዘገበው።)