የወንዝ ዳርቻ ልማት በኬንያ ናይሮቢ?!
የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ፣ የናይሮቢ የወንዝ ልማት ፕሮጀክትን በይፋ ማስጀመራቸው ተዘግቧል - የአዲስ አበባ የወንዝ ዳርቻ ልማት ዓይነት ይመስላል፡፡ በዚህም የተነሳ ይመስላል አንዳንዶች ፕሬዚዳንቱ ከኢትዮጵያ አይተው ነው ፕሮጀክቱን የጀመሩት ለማለት ሰበብ የሆናቸው፡፡ ለዚህ ግን በቂ ማረጋገጫ ያለ አይመስልም፡፡ ቢያንስ ለጊዜው፡፡ ለነገሩ ከእኛም አይተው ወይም ቀድተው ቢሆን እሰየው ነው፡፡ ለአርአያነት በመብቃታችን ልንኮራ ነው የሚገባው፡፡
ወደ ዘገባው ስንመለስ፣ ግዙፉ የናይሮቢ የወንዝ ልማት ፕሮጀክት የ60 ኪሎ ሜትር የፍሳሽ መስመር ዝርጋታና የ50 ሺ መኖሪያ ቤቶች ግንባታን ያካትታል፡፡
ፕሬዚዳንት ሩቶ በትላንትናው ዕለት የናይሮቢ ወንዞች ልማት የኢንጂነሪንግ ሥራን ያስጀመሩ ሲሆን፤ ፕሮጀክቱ በእጅጉ የተበከሉትን የናይሮቢ ወንዞች ለማጽዳትና የከተማዋን ከባቢያዊ ሁኔታ ለማደስ ያለመ ነው ተብሏል፡፡
በናይሮቢ ወንዝ ዳርቻዎች በ388 ሚሊዮን ዶላር ወጪ የማህበራዊ መኖሪያ ቤቶች እንደሚከናወንም ተጠቁሟል፡፡
የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ፣ የናይሮቢ የወንዝ ልማት ፕሮጀክትን በይፋ ማስጀመራቸው ተዘግቧል - የአዲስ አበባ የወንዝ ዳርቻ ልማት ዓይነት ይመስላል፡፡ በዚህም የተነሳ ይመስላል አንዳንዶች ፕሬዚዳንቱ ከኢትዮጵያ አይተው ነው ፕሮጀክቱን የጀመሩት ለማለት ሰበብ የሆናቸው፡፡ ለዚህ ግን በቂ ማረጋገጫ ያለ አይመስልም፡፡ ቢያንስ ለጊዜው፡፡ ለነገሩ ከእኛም አይተው ወይም ቀድተው ቢሆን እሰየው ነው፡፡ ለአርአያነት በመብቃታችን ልንኮራ ነው የሚገባው፡፡
ወደ ዘገባው ስንመለስ፣ ግዙፉ የናይሮቢ የወንዝ ልማት ፕሮጀክት የ60 ኪሎ ሜትር የፍሳሽ መስመር ዝርጋታና የ50 ሺ መኖሪያ ቤቶች ግንባታን ያካትታል፡፡
ፕሬዚዳንት ሩቶ በትላንትናው ዕለት የናይሮቢ ወንዞች ልማት የኢንጂነሪንግ ሥራን ያስጀመሩ ሲሆን፤ ፕሮጀክቱ በእጅጉ የተበከሉትን የናይሮቢ ወንዞች ለማጽዳትና የከተማዋን ከባቢያዊ ሁኔታ ለማደስ ያለመ ነው ተብሏል፡፡
በናይሮቢ ወንዝ ዳርቻዎች በ388 ሚሊዮን ዶላር ወጪ የማህበራዊ መኖሪያ ቤቶች እንደሚከናወንም ተጠቁሟል፡፡