ፕሬዚዳንቱ በትላንትናው ዕለት ሰኞ በካሙኩንጂ የምርጫ ክልል ለነዋሪዎች ባደረጉት ንግግር፤ "ዛሬ መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም በናይሮቢ ወንዝ ማደስ ፕሮግራም ሥር ትልቅ ፕሮጀክት እየጀመርን ነው፡፡ የናይሮቢን ወንዝ ጽዱ ለማድረግ 60 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የፍሳሽ ማስወገጃ መስመር እንገነባለን" ብለዋል፡፡
ፕሮጀክቱ የከተማዋን ጽዳትና ንጽህና ብቻ አይደለም የሚያሻሻሽለው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ ይልቁንም ከ30ሺ ለማያንሱ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥርም ተናግረዋል፡፡
"ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ የናይሮቢን ወንዝ ወደ መዝናኛ ስፍራ እንደምንቀይር ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ።" ብለዋል፤ ሩቶ በንግግራቸው፡፡
ፕሮጀክቱ የማህበረሰብ ፓርኮችን፣ የህዝብ አዳራሾችንና የመጸዳጃ ቤቶችን ልማት እንደሚያካትት የተገለጸ ሲሆን፤ በተጨማሪም በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች ያለውን ግንኙነት ለማስተሳሰርና ለማቀላጠፍ 44 የእግረኛና የተሽከርካሪ ድልድዮች ይገነባሉ ተብሏል፡፡
የናይሮቢ ወንዝ እድሳት ፕሮግራም፤ የኑሮ ሁኔታን ለማሻሻል፣ ኢኮኖሚያዊ እድሎችን ለማጎልበትና የናይሮቢን ተፈጥሯዊ ከባቢ ለመመለስ ያለመ የመንግሥት ሰፊ የከተማ እድሳት ስትራቴጂ አካል መሆኑ ታውቋል፡፡
ፕሮጀክቱ የከተማዋን ጽዳትና ንጽህና ብቻ አይደለም የሚያሻሻሽለው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ ይልቁንም ከ30ሺ ለማያንሱ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥርም ተናግረዋል፡፡
"ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ የናይሮቢን ወንዝ ወደ መዝናኛ ስፍራ እንደምንቀይር ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ።" ብለዋል፤ ሩቶ በንግግራቸው፡፡
ፕሮጀክቱ የማህበረሰብ ፓርኮችን፣ የህዝብ አዳራሾችንና የመጸዳጃ ቤቶችን ልማት እንደሚያካትት የተገለጸ ሲሆን፤ በተጨማሪም በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች ያለውን ግንኙነት ለማስተሳሰርና ለማቀላጠፍ 44 የእግረኛና የተሽከርካሪ ድልድዮች ይገነባሉ ተብሏል፡፡
የናይሮቢ ወንዝ እድሳት ፕሮግራም፤ የኑሮ ሁኔታን ለማሻሻል፣ ኢኮኖሚያዊ እድሎችን ለማጎልበትና የናይሮቢን ተፈጥሯዊ ከባቢ ለመመለስ ያለመ የመንግሥት ሰፊ የከተማ እድሳት ስትራቴጂ አካል መሆኑ ታውቋል፡፡