#ጊዜው_ገና_ነው
አንድ ምንጩ የማይታወቅ አስተማሪ የሆነ አፈ-ታሪክ አለ በዚህ አፈ-ታሪክ መሠረት ከዕለታት በአንዱ ቀን አጋንንት ስብሰባ አደረጉ ይባላል ይህንን ስብሰባ የጠራው የአጋንንቱ አለቃም “ዓለምን ሁሉ ከእኔ ጋር ለማሰለፍ እፈልጋለሁ ምን ይደረግ? ማንንስ ልላክ?” ብሎ ጠየቀ ከሥሩ ያሉትም አንድ በአንድ እየተነሱ አሳቦችን ማቅረብ ጀመሩ።
አንዱ ተነሳና “እኔን ብትልከኝ ፈጣሪ የለም ብዬ ሰዎችን ማሳመን እችላለሁ!” ብሎ ተናገረ። የአጋንንቱ አለቃ ግን “እርሱ አይሠራም ብዙዎቹ አያምኑህም ፈጣሪ እንዳለ ያውቃሉ” ብሎ መለሰ።
ሌላኛው ተነሳና “እኔን ከላክኸኝ ገነትም ሆነ ሲኦል የሚባል ቦታ እንደሌለ አሳምናቸዋለሁ!” አለ። የአጋንንቱ አለቃ ግን “እርሱም አይሠራም ብዙዎቹ ከሞት በኋላ ሕይወት እንዳለ ያውቃሉ” ብሎ መለሰ።
ሌላው ደግሞ ተነሳና “እኔን ላከኝ ፈጣሪም አለ ገነትም አለ ሲኦልም አለ ነገር ግን ስለዚህ ነገር ሁሉ ለማሰብ ጊዜው አሁን አይደለም ብዬ አሳምናቸዋለሁ” አለ። የአጋንንቱ አለቃም ደስ እያለው “ይህ ጥሩ መንገድ ነው!” በማለት አሳቡን ተቀበለና ላከው ይባላል።
ሰይጣን ማዘግየት ጥሩ ስልት መሆኑን ስለሚያውቅ ለማዘግየት ይፋጠናል በሐዲስ ኪዳን ላይ ቅዱስ ጳውሎስ "ወደ እናንተ ልንመጣ ወደን ነበርና እኔ ጳውሎስም አንድና ሁለት ጊዜ ሰይጣን ግን አዘገየን” 1ተሰ፡ 2፥18 ሲል እናገኘዋለን። ሰይጣን ላያስቀረን ይችላል ግን ቢያንስ ሊያዘገየን ብዙ ይሞክራል።
እርሱ ዓለማዊ ጓዞቻችንን ለአፍታ ስንኳ አውርደን ከእግዚአብሔር ጋር ስላለን ግንኙነት እንድናስብ አይፈልግም ስለ ጸሎት ብታስብ "አሁን ደክሞሃል ጊዜው አይደለም ሌላ ጊዜ ትጸልያለህ" ይልሃል ለመጾም ብትዘጋጅ "አሁን ጉልበት ስለሚያስፈልግህ ብላ የምትጾምበት ጊዜ አይደለም ሌላ ጊዜ ትጾማለህ" ይልሃል ለመስገድ ብትዘጋጅ "ኧረ ተረጋጋ ጊዜው አይደለም ጾም ሲገባ ትሰግዳለህ" ይልሃል ንሥሓ ልትገባ ብትዘጋጅ "ቆይ እንጂ ዘልለህ ጨርሰህ አንዴ ብትታጠበው አይሻልም?" ለማለት የሚቀድመው የለም ቅዱስ ቁርባን ልቀበል ነው ካልክ "አንተኮ ገና ነህ ለወደፊት ጣጣህን ስትጨርስ ቀስ ብለህ አመቻችተህ ትቆርባለህ" ብሎ ያዘናጋሃል።
በዚህ ሁሉ መዘግየት ውስጥ መልአከ ሞት መቼ እንደሚመጣ ማን ያውቃል? ለመንፈሳዊ ነገር ስንነሳ ሰይጣን "ጊዜው ገና ነው" ማለቱ አይቀርም እኛ ደግሞ የእግዚአብሔር ቃል“ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ የመዳን ቀን አሁን ነው” 2ኛ ቆሮ፡ 6፥2 እንደሚል እናስታውስ ለመዳናችን ቀጥሮ አንስጥ።
ፍሬሰንበት ገ/ አድኀኖም
#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!
አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube
Sador Sisay on Youtube
Sador Sisay on Instagram
Sador Sisay on Facebook
Sador Sisay on Tiktok
#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏
አንድ ምንጩ የማይታወቅ አስተማሪ የሆነ አፈ-ታሪክ አለ በዚህ አፈ-ታሪክ መሠረት ከዕለታት በአንዱ ቀን አጋንንት ስብሰባ አደረጉ ይባላል ይህንን ስብሰባ የጠራው የአጋንንቱ አለቃም “ዓለምን ሁሉ ከእኔ ጋር ለማሰለፍ እፈልጋለሁ ምን ይደረግ? ማንንስ ልላክ?” ብሎ ጠየቀ ከሥሩ ያሉትም አንድ በአንድ እየተነሱ አሳቦችን ማቅረብ ጀመሩ።
አንዱ ተነሳና “እኔን ብትልከኝ ፈጣሪ የለም ብዬ ሰዎችን ማሳመን እችላለሁ!” ብሎ ተናገረ። የአጋንንቱ አለቃ ግን “እርሱ አይሠራም ብዙዎቹ አያምኑህም ፈጣሪ እንዳለ ያውቃሉ” ብሎ መለሰ።
ሌላኛው ተነሳና “እኔን ከላክኸኝ ገነትም ሆነ ሲኦል የሚባል ቦታ እንደሌለ አሳምናቸዋለሁ!” አለ። የአጋንንቱ አለቃ ግን “እርሱም አይሠራም ብዙዎቹ ከሞት በኋላ ሕይወት እንዳለ ያውቃሉ” ብሎ መለሰ።
ሌላው ደግሞ ተነሳና “እኔን ላከኝ ፈጣሪም አለ ገነትም አለ ሲኦልም አለ ነገር ግን ስለዚህ ነገር ሁሉ ለማሰብ ጊዜው አሁን አይደለም ብዬ አሳምናቸዋለሁ” አለ። የአጋንንቱ አለቃም ደስ እያለው “ይህ ጥሩ መንገድ ነው!” በማለት አሳቡን ተቀበለና ላከው ይባላል።
ሰይጣን ማዘግየት ጥሩ ስልት መሆኑን ስለሚያውቅ ለማዘግየት ይፋጠናል በሐዲስ ኪዳን ላይ ቅዱስ ጳውሎስ "ወደ እናንተ ልንመጣ ወደን ነበርና እኔ ጳውሎስም አንድና ሁለት ጊዜ ሰይጣን ግን አዘገየን” 1ተሰ፡ 2፥18 ሲል እናገኘዋለን። ሰይጣን ላያስቀረን ይችላል ግን ቢያንስ ሊያዘገየን ብዙ ይሞክራል።
እርሱ ዓለማዊ ጓዞቻችንን ለአፍታ ስንኳ አውርደን ከእግዚአብሔር ጋር ስላለን ግንኙነት እንድናስብ አይፈልግም ስለ ጸሎት ብታስብ "አሁን ደክሞሃል ጊዜው አይደለም ሌላ ጊዜ ትጸልያለህ" ይልሃል ለመጾም ብትዘጋጅ "አሁን ጉልበት ስለሚያስፈልግህ ብላ የምትጾምበት ጊዜ አይደለም ሌላ ጊዜ ትጾማለህ" ይልሃል ለመስገድ ብትዘጋጅ "ኧረ ተረጋጋ ጊዜው አይደለም ጾም ሲገባ ትሰግዳለህ" ይልሃል ንሥሓ ልትገባ ብትዘጋጅ "ቆይ እንጂ ዘልለህ ጨርሰህ አንዴ ብትታጠበው አይሻልም?" ለማለት የሚቀድመው የለም ቅዱስ ቁርባን ልቀበል ነው ካልክ "አንተኮ ገና ነህ ለወደፊት ጣጣህን ስትጨርስ ቀስ ብለህ አመቻችተህ ትቆርባለህ" ብሎ ያዘናጋሃል።
በዚህ ሁሉ መዘግየት ውስጥ መልአከ ሞት መቼ እንደሚመጣ ማን ያውቃል? ለመንፈሳዊ ነገር ስንነሳ ሰይጣን "ጊዜው ገና ነው" ማለቱ አይቀርም እኛ ደግሞ የእግዚአብሔር ቃል“ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ የመዳን ቀን አሁን ነው” 2ኛ ቆሮ፡ 6፥2 እንደሚል እናስታውስ ለመዳናችን ቀጥሮ አንስጥ።
ፍሬሰንበት ገ/ አድኀኖም
#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!
አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube
Sador Sisay on Youtube
Sador Sisay on Instagram
Sador Sisay on Facebook
Sador Sisay on Tiktok
#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏