አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


🔔🔔🔔 አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ🔔🔔🔔
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሥርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች ፣ወቅታዊ መረጃ፣ሥርዓተ ማኅሌት ፣ዝማሬ፣የቅዱሳንን ታሪክ የምታገኙበት ቻናል ነው።
ለማንኛውም አስተያየት @SDS12317212729

@Dn_amu_ki_17

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


#የሃይማኖት_ተክል

#ጥር_24_አባታችን_ተክለ_ሃይማኖት ለሃያ ሁለት ዓመታት የቆሙበት ቀኝ እግራቸው ተሰብሮ መውደቁንና በአንድ እግራቸው ለሰባት ዓመታት ቆመው መጸለያቸውን ቅድስት ቤ .ክ በዓልን ሰርታ በታላቅ ድምቀት ታከብራለች ።

ለሰባ ሁለት ዘመን ያህል በተሠጣቸው ጸጋ መንፈሳዊ አጋንንትን በመስቀል ድል በመንሳት በቃላቸው ተናግረው በእጃቸው ዳሰው ድውይ በመፈወስ ሙት በማንሳት ከዚህም የበዙ ብዙ ተአምራት አድርገዋል ።

#ጻድቁ_አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት ለአሕዛብ ወንጌልን ለካሀዲያን አሜንን ለአማንያን ሥርዓተ ምንኩስናን ሲያስተምሩ ቆይተው ሥጋዬን ጠቀምኳት ብለው አንድም በጸጋ ላይ ጸጋ በክብር ላይ ክብር እንዲጨመርላቸው በተወለዱ በዘጠና ሁለት ዓመት እድሜያቸው በደብረ ሊባኖስ ካለችው አሰቦ ገዳመ ዋሻ ውስጥ በመግባት ለሰባት ዓመታት ተጋድሏቸውን ቀጥለዋል ።

ስምንት ጦሮችን አስተክለው ሁለቱን በፊት ሁለቱን በኋላ ፣ ሁለቱን በቀኝ ሁለቱን ደግሞ በግራ በማድረግ እጆቻቸውን በትእምርተ መስቀል በመዘርጋት የክርስቶስን ሕማምና ሞት ነገረ መስቀልን በማሰብ በተመስጦ ሌትና ቀን ያለማቋረጥ በጾምና በጸሎት በአርምሞ ተወስነው ሲጋደሉ ከቁመት ብዛት የተነሣ ጥር አራት ቀን አንዲቱ የእግራቸው አገዳ ተሰብራ የወደቀችበት ቀን ነው ።

ቅዱስ አባታችን በመዓልትና በሌሊት በትጋትና በቁመት በተጋድሎ ብዛት አንዲት የአገዳ እግራቸው ስትሰበር ዕድሜያቸው 92 ዓመት ሆኗቸው ነበር።

በተፈጥሮ ጠባህ ምድራዊ ሰው ስትሆን በሥነ ምግባርህ ሰማያዊ መልአክ ነህና ከልቅሶ ከዋይታው ዐርፍ ዘንድ በወርቅና በእንቁ በተሰራችው በሉዓላዊት ቤትህ ከዚህ ወስደህ አስቀምጠኝ🙏

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏




፩. አንዳንድ ቀን የሞቱ ሰዎችን የfacebook ገጽ አያለሁ። ከዕድሜያቸው ቀንሰው ዋጋ ሰጥተው የጻፉት ምን ነበር? ያ ያደረጉት ነገር ከሞት በኋላ ላለው ሕይወት አንዳች ቁም ነገር ኖሮት ይሆን? ለሰው ጠቅሞ ይሆን? እግዚአብሔር የሚወደው ነበር ይሆን?

፪. አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የሞቱ ሰዎችን ቃለ መጠይቅ እሰማለሁ። ዋጋ ሰጥተው የተናገሩት ነገር ከዘለዓለማዊው ሕይወት ጋር ግንኙነት ነበረው ይሆን? ለምን ነበር በዚህ ምድር የደከሙት? ቃለ መጠይቃቸው ላይ ትኩረት ያደረጉት በምን ጉዳይ ነበር? ያ ጉዳይ በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ አሁን ለሄዱበት ዓለም አዎንታዊ ሚና ነበረው ይሆን?

፫. የሞቱ ሰዎችን መጻሕፍትና የምርምር ውጤቶች (Researches) አነባለሁ። በዚህ ዓለም የደከሙለት ጉዳይ ከዘለዓለማዊው ሕይወት ጋር የተገናኘ ነበር? የትኩረታቸው ዋና ማዕከል ምን ነበር?

፬. ቤተክርስቲያን ስትሔዱ የብዙዎችን መቃብር አስባችሁት ታውቃላችሁ? አንዳንዶቹ ዕቅዳቸውን ሳይቋጩ ያረፉ ናቸው። አንዳንዶቹ ለምን እንደሚኖሩ ሳያውቁ ያረፉ ናቸው። አንዳንዶች አሁን እኛ ባለንበት ሁኔታ (መጥፎ ወይም መልካም) ሆነው ያረፉ ናቸው።

ሰው ሞትን መዘንጋት የለበትም። ስለዚህ እስካለ ድረስ ለሰው በጎ አስተዋጽኦ አበርክቶ ቢያልፍ መልካም ነው። እግዚአብሔር አድርጉ ያለንን አድርገን ለማለፍ ሕጉን በየዕለቱ እያነበብን እየተገበርን ብንኖር መልካም ነው። ለመሞት አንድ ቀን እንደቀረው ሰው ሆነን እንኑር። ሰውን እንደራሳችን እንውደድ። የእግዚአብሔርን ሕግ እንጠብቅ። ጎበዝ ዕድሜያችንን ለቁም ነገር እናውላት። ሁሉም ኃላፊ ነውና የማያልፈው ላይ ትኩረት እናድርግ። መሞታችን ካልቀረ ደግ ሥራ እየሠራን እንሙት።

#በትረ_ማርያም_አበባው

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏




#ልጅሽ_ወደ_ሕይወት_ወደ_ክብር_መንግሥት_ይጠራሻል

#የከበረች_እመቤታችን በ49 ዓ.ም ጥር 21 እሑድ ቀን 64 ዓመት ሲሆናት ልጇ ወዳጇ መጥቶ እናቴ ከዚህም ዓለም ድካም የምትለይበት የምታርፊበት ቀን ቀርቧል አላት ያንጊዜ እመቤታችን ደነገጠች።

መደንገጧ ሞትን ፈርታ የዚህ ዓለም ኑሮ አጓጉቷት አይደለም እንዴት የሕይወት እናት ሆኜ እሞታለሁ? የትንሣኤ እናት ሆኜ እንዴት እቀበራለሁ? ሕይወትንንና ትንሣኤን ያዩ ዐይኖቼ እንዴት በሞት ያሸልባሉ ?

ሕይወትንና ትንሣኤን ያቀፉ እጆቼ እንዴት ይገነዛሉ ? አካለ መለኮትን የተሸከመች ጀርባዬ ከመቃብር አፈር ላይ እንዴት ትተኛለች ? ገጸ መለኮትህን የሳሙ ከንፈሮቼ እንዴት በሞት ይዘጋሉ ? በፍጹም አልሞትም ስትለው ነው፡፡

ጌታ ግን አልሞትም ስትለው አልተሟገታትም ያለፈቃዷ ምንም ምን ማድረግ አልፈለገም ምክንያቱም እናቱ ናትና ይወዳታልና ሌላ ማሳመኛ ዘዴ አዘጋጀ ይህውም ልቧን ያውቃል የኀጥአን ነገር እንደማይሆንላት ርኅራኄዋን ስለሚያውቅ መላእክትን ወስዳችሁ በስቃይ ቦታ የሚቃጠሉ ነፍሳትን አሳይዋት ብሎ አዘዛቸው።

እነርሱም ለሰይጣንና በእርሱ ጎዳና ለሚጓዙ ሁሉ ወደ ተዘጋጀ ወደ ጨለማው ዳርቻ አደረሷት ከዚያ ነፍሳት ሲቃጠሉ አየችና አለቀሰች እንዲህም አለች ‹‹ ልጄ ወዳጄ ዛሬ በሲዖል ሲቃጠሉ በራዕይ ያየኋቸውን ነፍሳት እባክህን ማርልኝ አለችው››።

ጌታም ‹‹ እናቴ ! እኔ ዐምስት ሺ ዐምስት መቶ ዘመን በሲዖል ሲቃጠሉ የኖሩትን ነፍሳት ያዳንኳቸው ሞቼላቸው ነው አንቺም እንዲድኑ ከወደደሽ ሙቺላቸው አላት››።

እመቤታችንም ‹‹ አይደለም አንድ ጊዜ ቀርቶ ሰባት ጊዜ ልሙት አለችው ›› ይህንን ቃሏን ምክንያት አድርጎ እርሷም ለነፍሳት ልትሞትላቸው እርሱም ነፍሳትን ሊያድንላት ተስማሙ።

ወዲያው ከደብረ ዘይት ደናግል መጡ የቅርብ አገልጋይዋ ዮሐንስ ከሀገረ ስብከቱ ከኤፌሶን በደመና ተጭኖ መጣ ሐዋርያትም ከየሀገረ ስብከታቸው በመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ በደመና ተጭነው ወደ እመቤታችን ተሰበሰቡ።

ሁሉም በኅብረት ‹‹ የጌታችን እናት ጸጋን የተመላሽ ደስ ይበልሽ ›› እያሉ እየሰገዱ አመሰገኗት ሐዋርያትን እንዲህ አለቻቸው ‹‹ ዕጣን አምጥታችሁ እያጠናችሁ የጌታዬን የኢየሱስ ክርስቶስን ስም ጥሩ ›› አለቻቸው እነርሱም እንዳዘዘቻቸው አደረጉ ።

በዚህ ጊዜ ጌታችንም ከሰማይ ከጌትነቱ ዙፋን አባቷ ዳዊትን የነቢያትንና የመላእክትን ማኅበር አስከትሎ እንደ ግድግዳ ከበውት ወደ እርሷ መጣና አረጋጋት ያዘጋጀላትንም ተድላ ደስታ ነገራት።

የክብር ባለቤት ጌታችንም ‹‹ እንግዲህ ሥጋሽን ተድላ ወዳለበት ገነት አፈልሰዋለሁ ዳግመኛም ሥጋሽን ከነፍስሽ ጋር አዋኅጄ አስነሥቼ መላእክት የሚያመሰግኑበት ተመሳሳይ በሌለው ተድላ ደስታ ባለበት ማደሪያ አኖርሻለሁ›› አላት።

ከሥጋዋም የምትለይበት ጊዜ ሲደርስ ሐዋርያትና ደናግል ትባርካቸው ዘንድ እያለቀሱ ለመኗት እጅዋን በላያቸው ዘርግታ ባረከቻቸው።

በይባቤ መላእክት በመዐዛ ገነት እነሄኖክ እነእዝራ በበገና በመሰንቆ እያመሰገኗት ንጽሕት ነፍሷን ከንጹሕ ሥጋዋ ለይቶ በመለኮታዊ እጆቹ ይዞ በብርሃን ልብስ አጎናጽፎ ወደ ከፍተኛ መኖሪያ ከእርሱ ጋር አሳረጋት ።

ቅዱሳን ሐዋርያት ሥጋዋን እንደሚገባ ገንዘው ወደ ጌቴሴማኒ ተሸክመው እንዲወስዷት አዘዛቸው ሐዋርያትም በአጎበር አድርገው ወደ ጌቴሴማኒ ይዘዋት ሄዱ። ከዚህ በኋላ መልአኩ እመቤታችንን ከዮሐንስ ጋራ በደመና ነጥቆ ወስዶ በገነት ከዕፀ ሕይወት እግር አኑሯታል።

ማርያም ሆይ ስለሁላችን የነፍስ ይቅርታ ከልጅሽ ከወዳጅሽ ከእግዚአብሔር ዘንድ ለምኚልን🙏

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏




"ሰማይ አድምጥ ምድርም ስሚ"

ይህ ቃል በጸሎተ ሙሴ ላይ የሰፈረ የምስጋና ማንሻ ቃል ነው። የመጻሕፍት ምሥጢር የተገለጠላቸው መተርጉማን ቃሉን ሲፈቱት ለቅዱስ ገብርኤልና በእመቤታችን ይተረጉሙታል። ምድር አድምጥ (ስማ) እንደ ተባለ _ ገብርኤልም ከእግዚአብሔር የተነገረውን ቃል አድምጦ (ሰምቶ) ለእመቤታቸን ሰማያዊውን ብሥራት የነገራት ሲኾን ምድር ስሚ እንደተባለች ደግሞ ከምድር የሆነች እመቤታችንም የገብርኤልን ቃል ሰምታ ጌታን ፀንሳለችና ገብርኤልን በሰማይ እመቤታችንን በምድር መስሎ ያመሰግናቸዋል፡፡

(ዘዳግም 32)


#ደብረ_ይድራስ_ተራራ_ወስደው_አፅሙን_በተኑት

#ጥር_18 ቀን ቅዱስ ጊዮርጊስ በብዙ ተጋድሎ ውስጥ ሆኖ « እኔ የክርስቲያን ወገን ነኝ እምነቴም በጌታዬ በኢየሱስ ክርስቶስ ነው » በማለት የተመዘዘ ሰይፍ የነደደ እሳትን የከሀዲውን የዲድያኖስ ቁጣ ሳይፈራ መከራን ታግሷል የጌታውን የአምላኩን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት የመሰከረበት ዕለት ሲሆን ።

ቅዱስ ጊዮርጊስም በማይመረምረው ጥበበ እግዚአብሔር በመታመኑ ብዙ መከራ ደረሰበት በጉድጓዳ ብረት ምጣድ ውስጥ አብስለው አቃጥለው አሳርረው ሥጋውንና አጥንቱን ፈጭተው አመድ አድርገው በዕንጨት ቀፎ በማድረግ በዚህ ጥር 18 ቀን ደብረ ይድራስ ወደ ተባለ ረጅም ተራራ ወስደው አፅሙን በተኑት ።

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ነፍሱን ወደ ሥጋው መልሷት አንድ አካል ሆኖ ወደ ቀድሞ መልኩ ዳግም ተመልሶ አስነሣው ወደ ነገሥታቱም ተመልሶ በመሄድ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሰበከ ።

ለቁጥር የበዙ አሕዛብ አይተው አደነቁ ከንጉሥ ሠራዊትም ከአሕዛብም ብዙዎችን በጌታችንም አመኑ በማመናቸውም ምክንያት በከሀዲው በንጉሥ ዲድያኖስ ሰማዕትነትን ተቀበሉ ።

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም በታላቅ ድምቀት ይህንን ቀን ታሳቢ በማድረግ በዓልን ሰርታ ታከብረዋለች።

#የሰማዕቱ_በረከት_ይደርብን

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏




#በሃይማኖት_መጽናት

#ጥር_15 ቀን ቅዱስ ቂርቆስና ቅድስት ኢየሉጣን ለክርስቶስ ፍቅር ሲሉ ተጋድሏቸውን እስኪፈጽሙ ድረስ ራሳቸውን ለመከራና ለሞት አሳልፈው በመስጠት ከእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ተቀብለው በመንፈቀ ሌሊት አንገታቸውን ተቆርጠው በሰማዕትነት ያረፉበት ቀን ነው ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም በዓልን ሠርታ በታላቅ ድምቀት ታከብራቸዋለች።

ለስም አጠራሩ ስግደት የሚገባው የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈቀ ሌሊት ሰማዕትነት በሚቀበልበት ሰዓት ወርዶ ሕፃኑን ቅዱስ ቂርቆስን የምትሻውን ለምነኝ አለው።

ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስም ሥጋዬ በምድር አይቀበር ስሜን ለሚጠራ መታሰቢያዬን ለሚያደርግ ቤተ ክርስቲያኔን ለሚሠራ የተጋድሎዬን መጽሐፍ ለሚጽፍና ለሚያጽፍ ወይም ለሚያነበው ለቤተ ክርስቲያኔ መባ ለሚያገባ በውስጧም ለሚጸልይ ለሁሉም ፍላጎታቸውን ስጣቸው ኃጢአታቸውንም ይቅር በል ስሜም በሚጠራበት በዚያች ቦታ የከብት ዕልቂት አይምጣ በሰውም ላይ አባር ቸነፈር በእህልም ላይ ድርቅ የውኃም ማነስ አይሁን ብሎ ተማጸነው ።

መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የለመንከኝን ሁሉ እሰጥሃለሁ አንተም በቀኜ ትኖራለህ ሥጋህንም ኤልያስ በዐረገበት ሠረገላ ውስጥ አኖራለሁ አለው ሕፃን ቂርቆስም በሰማ ጊዜ እጅግ ደስ ብሎት ጌታችንን አመሰገነው ።

ከዚህም በኋላ በሌሊቱ እኩሌታም ከእናቱ ጋር አንገቱን ተቆረጠ መድኃኒታችንም በማይጠፋ አክሊል ጋረደው ነፍሶቻቸውንም በታላቅ ክብር ከእርሱ ጋር አሳረገ ።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቂርቆስና በኢየሉጣ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏




#ጊዜው_ገና_ነው

አንድ ምንጩ የማይታወቅ አስተማሪ የሆነ አፈ-ታሪክ አለ በዚህ አፈ-ታሪክ መሠረት ከዕለታት በአንዱ ቀን አጋንንት ስብሰባ አደረጉ ይባላል ይህንን ስብሰባ የጠራው የአጋንንቱ አለቃም “ዓለምን ሁሉ ከእኔ ጋር ለማሰለፍ እፈልጋለሁ ምን ይደረግ? ማንንስ ልላክ?” ብሎ ጠየቀ ከሥሩ ያሉትም አንድ በአንድ እየተነሱ አሳቦችን ማቅረብ ጀመሩ።

አንዱ ተነሳና “እኔን ብትልከኝ ፈጣሪ የለም ብዬ ሰዎችን ማሳመን እችላለሁ!” ብሎ ተናገረ። የአጋንንቱ አለቃ ግን “እርሱ አይሠራም ብዙዎቹ አያምኑህም ፈጣሪ እንዳለ ያውቃሉ” ብሎ መለሰ።

ሌላኛው ተነሳና “እኔን ከላክኸኝ ገነትም ሆነ ሲኦል የሚባል ቦታ እንደሌለ አሳምናቸዋለሁ!” አለ። የአጋንንቱ አለቃ ግን “እርሱም አይሠራም ብዙዎቹ ከሞት በኋላ ሕይወት እንዳለ ያውቃሉ” ብሎ መለሰ።

ሌላው ደግሞ ተነሳና “እኔን ላከኝ ፈጣሪም አለ ገነትም አለ ሲኦልም አለ ነገር ግን ስለዚህ ነገር ሁሉ ለማሰብ ጊዜው አሁን አይደለም ብዬ አሳምናቸዋለሁ” አለ። የአጋንንቱ አለቃም ደስ እያለው “ይህ ጥሩ መንገድ ነው!” በማለት አሳቡን ተቀበለና ላከው ይባላል።

ሰይጣን ማዘግየት ጥሩ ስልት መሆኑን ስለሚያውቅ ለማዘግየት ይፋጠናል በሐዲስ ኪዳን ላይ ቅዱስ ጳውሎስ "ወደ እናንተ ልንመጣ ወደን ነበርና እኔ ጳውሎስም አንድና ሁለት ጊዜ ሰይጣን ግን አዘገየን” 1ተሰ፡ 2፥18 ሲል እናገኘዋለን። ሰይጣን ላያስቀረን ይችላል ግን ቢያንስ ሊያዘገየን ብዙ ይሞክራል።

እርሱ ዓለማዊ ጓዞቻችንን ለአፍታ ስንኳ አውርደን ከእግዚአብሔር ጋር ስላለን ግንኙነት እንድናስብ አይፈልግም ስለ ጸሎት ብታስብ "አሁን ደክሞሃል ጊዜው አይደለም ሌላ ጊዜ ትጸልያለህ" ይልሃል ለመጾም ብትዘጋጅ "አሁን ጉልበት ስለሚያስፈልግህ ብላ የምትጾምበት ጊዜ አይደለም ሌላ ጊዜ ትጾማለህ" ይልሃል ለመስገድ ብትዘጋጅ "ኧረ ተረጋጋ ጊዜው አይደለም ጾም ሲገባ ትሰግዳለህ" ይልሃል ንሥሓ ልትገባ ብትዘጋጅ "ቆይ እንጂ ዘልለህ ጨርሰህ አንዴ ብትታጠበው አይሻልም?" ለማለት የሚቀድመው የለም ቅዱስ ቁርባን ልቀበል ነው ካልክ "አንተኮ ገና ነህ ለወደፊት ጣጣህን ስትጨርስ ቀስ ብለህ አመቻችተህ ትቆርባለህ" ብሎ ያዘናጋሃል።

በዚህ ሁሉ መዘግየት ውስጥ መልአከ ሞት መቼ እንደሚመጣ ማን ያውቃል? ለመንፈሳዊ ነገር ስንነሳ ሰይጣን "ጊዜው ገና ነው" ማለቱ አይቀርም እኛ ደግሞ የእግዚአብሔር ቃል“ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ የመዳን ቀን አሁን ነው” 2ኛ ቆሮ፡ 6፥2 እንደሚል እናስታውስ ለመዳናችን ቀጥሮ አንስጥ።

ፍሬሰንበት ገ/ አድኀኖም
#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏




#ቃና_ዘገሊላ_በአባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ

ወይን የኾነ የቃና ውኀ በመጭመቂያ ጨምቀው በመጥመቂያ ውስጥ የጠመቁት የልማድ ወይን አይደለም ሙሽራ እንዳያፍር ሰርገኞችም እንዲረኩ የተሰጠ የእግዚአብሔር ልጅ የተዐምራቱ ወይን ነው እንጂ፡፡

የጌታ ኢየሱስ እናቱ ወይን እኮ የላቸውም እባክህ ይህን ችግር አስወግድ ብላዋለችና ጌታ ኢየሱስም አንቺ ሴት ከአንቺ ምን አለኝ ገና ጊዜዬ አልደረሰምና አላት በልቡ ለተከማቸ ፍቅሯ በሚሻል ነገር መለሰላት ስለምድራዊ ወይን ለመነችው እርሱም ከጐኑ ስለሚፈሰው የደሙ ወይን በምሥጢር መለሰ፡፡

ጊዜዬ አልደረሰም ያለው የአባቴን ድንቆች በምገልጥበት ከአንቺም በነሣሁት ሥጋ ረኃብንና ጥምን ጭንቁንም ኹሉ በምቀበልበት ከኀጥአን ጋራ በምቀመጥበት አመንዝሮችንም በማነጻበት ሦስት ዓመታት ቀርተውኛልና ከጐኔ በፈሰሰ የምሥጢር ወይን ምእመናንን አረካቸው ዘንድ የምወጋበት ሰዓት አልደረሰም ተብሎ ይተረጐማል፡፡ ይኽን ስለ ተዐምራቱ ወይን ተናግሮታል የሚል ቢኖር እኔም ጊዜው እኮ ደረሰ ማድረጉንም አላዘገየም እለዋለሁ

ያንጊዜም ውኀውን ቀድተው በስድስቱ የደንጊያ ጋኖች እንዲጨምሩ አዘዘ ባሕርዩም ወይን ወደመኾን ተለወጠ ጋኖች ውኀውን ወይን ወደመኾን የለወጡት አይደለም እርሱ ወደጋኖች እንዲቀዱት ያዘዘውን ውኀ ወይን ወደ መኾን ለወጠው እንጂ ጋኖች ውኀውን ወይን የሚለውጡትስ ቢኾን አይሁድ ዘወትር ኹለት ኹለት ሦስት ሦስት ማድጋ በሚይዙ በእነዚያ ጋኖች ውስጥ የሚያጠሩባቸው አይደሉምን፡፡

የቃና ወይን በኦሪት ሕግ ተመሰለች የጠጧትን አላጸደቀቻቸውምና ነገር ግን በመዓዛዋ ጣፋጭነት ልባቸውን ደስ አሰኘች እንዲሁ ኦሪትም ቀድመው የተቀበሏትን አላጸደቀቻቸውም የእግዚአብሔር ቃል ናትና እርሷን በመስማትም ልባቸውን ደስ አሰኘች ስለዚህም ነገር ጳውሎስ በኦሪት ሕግ መጽደቅ በተሳናቸው ጊዜ እግዚአብሔር ልጁን ላከ ከሴትም ተወለደ በኦሪት ያሉትንም ይዋጅ ዘንድ የኦሪትን ሕግ ፈጸመ አለ፡፡

ውኀው በቃና ወይን ወደመኾን እንደተለወጠ እንዲሁ የሙሴ በትር በደብረ ሲና ነቢዩ ከፊቱ እስኪሸሽ ድረስ የሚንቀሳቀስ እባብ ወደ መኾን ተለወጠ ኹለተኛም ነቢዩ ጐንበስ ብሎ እስኪያነሣው ድረስ በትር ወደ መኾን ተመለሰ በዚያም በትር በፈርዖንና በታላላቆቹ ፊት ተዐምራትን አደረገ የጌታ ኢየሱስም የደሙ ወይን በወንጌል ሕግ ተመሰለ ማርካትና ማጽደቅን ችሏል መድኃኒታችን ሥጋዬ እውነተኛ የጽድቅ ምግብ ነው ደሜም እውነተኛ የሕይወት ውኃ ነው ሥጋዬን የበላ የእኔን ሥጋ ስለበላ በሕይወት ይኖራል ደሜንም የጠጣ ሞትን አይቀምሰውም ብሏል እኮን ስለወንጌሉም ያመነ የተጠመቀ ሁሉ ይድናል ያላመነ ግን ይፈረድበታል አለ፡፡

የአምላክን እናት ከልጇ ዘንድ ወይንን ወደ መፈለግ ዜና እንመለስ ወይን እኮ የላቸውም ወይናቸው አልቋልና ብላ ስለምን ለመነችው ከውኀ ወይን እንደሚቀዳ ዐወቀችን ወንጌላዊው ዮሐንስ ይኽም ጌታ ኢየሱስ በቃና ዘገሊላ ያደረገውን ተዐምር የመጀመሪያው ነው ክብሩን አሳያቸው ደቀመዛሙርቱም አመኑበት እንዳለ ከዚያን ጊዜ በፊት እንደዚህ አላደረገምና፡፡

ድንግልስ ውኀውን ወይን ወደ መሆን እንደሚለውጠው አላወቀችም ነገር ግን በአብ ጥላ እንደፀነሰችው በልዑል ኃይልም እንደ ወለደችው ታውቃለችና ስለዚህም ድንግል የምሥራቹን ከነገራት መልአክ ዘንድ አባቱ ሰማያዊ እንደኾነ ተረድታለችና ስለወይን ማለደችው ስለዚህም ነገር በልቧ ድንቆችን የሚያደርግ የእርሱ ልጅ እንደ አባቱ ድንቅ ያደርጋልና ደቀ መዛሙርቱ ስለ ወይን አልማለዱትም ለእናቱም እንደነገራት መልአኩ አልነገራቸውምና የዮሴፍ ልጅ ይመስላቸው ነበር ተዐምራትንም ካደረገ በኋላ ከነቢያት አንዱ እንደኾነ እንጂ የእግዚአብሔር ልጅ እንደኾነ አላመኑበትም.....

#እንኳን_አደረሳችሁ_መልካም_በዓለ_ቃና_ዘገሊላ!

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏




#ቃና_ዘገሊላ

እኛ ስንጨርስ እሱ የሚጀምር አምላክ ስቡሕ ዘተሰብሐ፡፡

በቃና ሰዎች የተዘጋጁበት ኹሉ አለቀ፡፡ የሰው ዝግጅት ሲያልቅ የማያልቀው የእግዚአብሔር ተአምር ጀመረ፡፡

የማያልቀው ወይን እንዲቀዳ ልጇም ተአምሩን ይጀምር ዘንድ ምክንያት የኾነች "የኢየሱስም እናት በዚያ ነበረች፡፡"

ይኽ ታሪክ የአንድ የሰርግ ቤት ታሪክ ብቻ አይደለም ይኽ የዐለም ታሪክ ነው፡፡ ስድስቱ ጋኖች ስድስት ሺ ዘመናትን ይወክላሉ 5500 ዐመተ ፍዳን ማለት ነው፡፡

በስድስት ሺ የዘመን ጋኖች ውስጥ የነበረው ትንቢትና ተስፋ ሲያልቅ 'እኔ የወይን ግንድ ነኝ' ብሎ የነገረን ጣፋጩ ወይን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ማርያም መወለዱን… ያስረዳል፡፡


#ወናሁ_ተርኅወ_ሰማይ_እነሆ_ሰማይ_ተከፈተ ማቴ፡3፥16

#ሰማይ_የተዘጋ_ቤት_አይደለም እንደ ቤተ መቅደስ መጋረጃ የለውም ነገር ግን በሰውና በእግዚአብሔር መካከል የኀጢአት መጋረጃ የጥንተ አብሶ ተራራ ነበር።

ሰማይም ሳይከፈት ምሥጢራት ሳይገለጡ ዘመናት ተቆጥረዋል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮርዳኖስ ሲጠመቅ ሰማይ ተከፈተ ድንቅ ምሥጢር ተገለጠ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ከራሱ ላይ ተቀመጠ አብ በደመና አብ የምወደው ልጄ ይህ ነው እረሱን ስሙት አለ ሰማይ ተከፈተ አንድነት ሦስትነት በዮርዳኖስ ተገለጠ የሰማይ መዝጊያው የበደል ደብዳቤ ተቀደደ።

#ሰውና_እግዚአብሔር _አባትና_ልጅ_ሆኑ።

ሰማይ ተከፈተ የመንግሥተ ሰማይ መግቢያ የሆነው የልጅነት ጥምቀታችን በጌታ መጠመቅ ተቀደሰ ኀይል አገኘ።

ሰማያዊ እሳት በዮርዳኖስ ውኀ ላይ በቆመ ጊዜ ውኀው ፈላ እንጅ አሳቱ አልጠፋም።

ለልማዱ በውኋ ላይ አሳት ይጠፋል አይነድም እርሱ ግን የማይጠፋ እሳት ነውና ባሕሩን አፈላው የጥምቀት ውኀ በራሱ ጊዜ ፍል ውኀ ሆነ።

ዛሬ ብዙ ምእመናን ምሥጢሩን ባለማወቅ ልጆቻቸውን ክርስትና ሲያስነሱ ውኀ አሙቀው በፔርሙዝ ተሸክመው ቤተ ክርስቲያን ድረስ ያመጣሉ ቀሳውስቱንም ያስቸግራሉ።

በውኑ ከእናቶቻችን እስቶቭ ከእኅቶቻችን የምድጃ ክሰል ይልቅ የመንፈስ ቅዱስ እሳትነት ውኀውን እንደሚያፈላው ልጃቸው በሙቀተ መንፈስ ቅዱስ እንደሚጠመቅ ዮርዳኖስን መመልከት አልነበረባቸውምን?

የማይጠፋ አሳት ሊያድረበት የተዘጋጀን ሕፃን በሚጠፋ አሳት መለብለብ ከስሕተት በላይነው ሰማይ ሲከፈት መንፈስ ቅዱስ ሲወርድ ልማድ ይቀየራል።

#እንኳን_ለብርሀነ_ጥምቀቱ_አደረሳችሁ

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏




#ይህ_የሐዲስ_ኪዳኑ_ታቦት_ግን...

የኦሪት ጽላት እግዚአብሔር ሙሴንና አሮንን የሚያነጋግርበት በደመና ተከናንቦ ለእስራኤል ብቻ በረድኤት የሚገለጥበት ዙፋን ነበር፡፡

ይህ የሐዲስ ኪዳኑ ታቦት ግን የአምላክ ሥጋና ደም የሚፈተትበት ( ጌታችን ) ሥጋዬን የበላ ደሜን የጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው ሥጋዬን ብሉ ደሜን ጠጡ እያለ ያመኑትን የሚጠራበት የምሕረት
ምሥዋዕ ( መሠዊያ ) ነው፡፡

እናም ለታቦት ክብርና ስግደትም የሚደረግለት ለዚህ ነው በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት በታቦታቱ ሁሉ ላይ የተጻፈው ‹‹ አልፋና ኦሜጋ ›› የሚለው የመድኃኔ ዐለም ክርስቶስ ስም ነው።

ከስሙ ጋር ደግሞ በሁሉም ታቦታት ላይ የሚከተለው ጥቅስ በግእዝ ተጽፏል፡፡ ‹‹ ከመ ለስሙ ለኢየሱስ ክርስቶስ ይስግድ ኲሉ ብርክ ዘበሰማያት ወዘበምድር ›› ‹‹ ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ ›› የሚል ነው ፡፡ ፊልጵ 2፥10

በታቦቱ ፊት የሚሰግድ ሰው ለምን እንደሚሰግድ በታቦቱ ላይ የሚጻፈው ይህ ጥቅስ ያስረዳናል ምክንያቱ ‹‹ ጉልበት ሁሉ ለኢየሱስ ስም ይሰግዱ ዘንድ ›› ስለሚገባ ነው ፡፡

የክርስቶስ ሥጋ እንደሚቆረስ ደሙ እንደሚፈስስ የሚያምን ሰው በዚህ መሠዊያ ፊት በፍርሃት ለክርስቶስ ይሰግዳል ፡፡

ሥጋ ወደሙን ‹‹ ተራ መታሰቢያ ብቻ ነው ›› የሚል ሰው ግን በመሠዊያው ፊት እንዲሰግድና መሠዊያውን እንዲያከብር አንጠብቅም ፡፡

የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በታቦቷ ጽፋ ክብር የምትሠጥ የሐዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያን ልጆች ስለሆንን እግዚአብሔርን እናመሰግናለን ፡፡

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏



Показано 20 последних публикаций.