፩. አንዳንድ ቀን የሞቱ ሰዎችን የfacebook ገጽ አያለሁ። ከዕድሜያቸው ቀንሰው ዋጋ ሰጥተው የጻፉት ምን ነበር? ያ ያደረጉት ነገር ከሞት በኋላ ላለው ሕይወት አንዳች ቁም ነገር ኖሮት ይሆን? ለሰው ጠቅሞ ይሆን? እግዚአብሔር የሚወደው ነበር ይሆን?
፪. አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የሞቱ ሰዎችን ቃለ መጠይቅ እሰማለሁ። ዋጋ ሰጥተው የተናገሩት ነገር ከዘለዓለማዊው ሕይወት ጋር ግንኙነት ነበረው ይሆን? ለምን ነበር በዚህ ምድር የደከሙት? ቃለ መጠይቃቸው ላይ ትኩረት ያደረጉት በምን ጉዳይ ነበር? ያ ጉዳይ በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ አሁን ለሄዱበት ዓለም አዎንታዊ ሚና ነበረው ይሆን?
፫. የሞቱ ሰዎችን መጻሕፍትና የምርምር ውጤቶች (Researches) አነባለሁ። በዚህ ዓለም የደከሙለት ጉዳይ ከዘለዓለማዊው ሕይወት ጋር የተገናኘ ነበር? የትኩረታቸው ዋና ማዕከል ምን ነበር?
፬. ቤተክርስቲያን ስትሔዱ የብዙዎችን መቃብር አስባችሁት ታውቃላችሁ? አንዳንዶቹ ዕቅዳቸውን ሳይቋጩ ያረፉ ናቸው። አንዳንዶቹ ለምን እንደሚኖሩ ሳያውቁ ያረፉ ናቸው። አንዳንዶች አሁን እኛ ባለንበት ሁኔታ (መጥፎ ወይም መልካም) ሆነው ያረፉ ናቸው።
ሰው ሞትን መዘንጋት የለበትም። ስለዚህ እስካለ ድረስ ለሰው በጎ አስተዋጽኦ አበርክቶ ቢያልፍ መልካም ነው። እግዚአብሔር አድርጉ ያለንን አድርገን ለማለፍ ሕጉን በየዕለቱ እያነበብን እየተገበርን ብንኖር መልካም ነው። ለመሞት አንድ ቀን እንደቀረው ሰው ሆነን እንኑር። ሰውን እንደራሳችን እንውደድ። የእግዚአብሔርን ሕግ እንጠብቅ። ጎበዝ ዕድሜያችንን ለቁም ነገር እናውላት። ሁሉም ኃላፊ ነውና የማያልፈው ላይ ትኩረት እናድርግ። መሞታችን ካልቀረ ደግ ሥራ እየሠራን እንሙት።
#በትረ_ማርያም_አበባው
#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!
አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube
Sador Sisay on Youtube
Sador Sisay on Instagram
Sador Sisay on Facebook
Sador Sisay on Tiktok
#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏
፪. አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የሞቱ ሰዎችን ቃለ መጠይቅ እሰማለሁ። ዋጋ ሰጥተው የተናገሩት ነገር ከዘለዓለማዊው ሕይወት ጋር ግንኙነት ነበረው ይሆን? ለምን ነበር በዚህ ምድር የደከሙት? ቃለ መጠይቃቸው ላይ ትኩረት ያደረጉት በምን ጉዳይ ነበር? ያ ጉዳይ በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ አሁን ለሄዱበት ዓለም አዎንታዊ ሚና ነበረው ይሆን?
፫. የሞቱ ሰዎችን መጻሕፍትና የምርምር ውጤቶች (Researches) አነባለሁ። በዚህ ዓለም የደከሙለት ጉዳይ ከዘለዓለማዊው ሕይወት ጋር የተገናኘ ነበር? የትኩረታቸው ዋና ማዕከል ምን ነበር?
፬. ቤተክርስቲያን ስትሔዱ የብዙዎችን መቃብር አስባችሁት ታውቃላችሁ? አንዳንዶቹ ዕቅዳቸውን ሳይቋጩ ያረፉ ናቸው። አንዳንዶቹ ለምን እንደሚኖሩ ሳያውቁ ያረፉ ናቸው። አንዳንዶች አሁን እኛ ባለንበት ሁኔታ (መጥፎ ወይም መልካም) ሆነው ያረፉ ናቸው።
ሰው ሞትን መዘንጋት የለበትም። ስለዚህ እስካለ ድረስ ለሰው በጎ አስተዋጽኦ አበርክቶ ቢያልፍ መልካም ነው። እግዚአብሔር አድርጉ ያለንን አድርገን ለማለፍ ሕጉን በየዕለቱ እያነበብን እየተገበርን ብንኖር መልካም ነው። ለመሞት አንድ ቀን እንደቀረው ሰው ሆነን እንኑር። ሰውን እንደራሳችን እንውደድ። የእግዚአብሔርን ሕግ እንጠብቅ። ጎበዝ ዕድሜያችንን ለቁም ነገር እናውላት። ሁሉም ኃላፊ ነውና የማያልፈው ላይ ትኩረት እናድርግ። መሞታችን ካልቀረ ደግ ሥራ እየሠራን እንሙት።
#በትረ_ማርያም_አበባው
#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!
አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube
Sador Sisay on Youtube
Sador Sisay on Instagram
Sador Sisay on Facebook
Sador Sisay on Tiktok
#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏