ለሰላም ግንባታ የኅብረተሰቡ ሚና” በሚል መሪ ሃሳብ በደሴ ከተማ በክ/ከተማ ደረጃ የመንግሥት ሰራተኞች የሰላም ዉይይት ተካሄደ።
በደሴ ከተማ አስተዳደር በክ/ከተማ ደረጃ የሚገኙ የመንግሥት ሰራተኞች “ለሰላም ግንባታ የኅብረተሰቡ ሚና” በሚል ሃሳብ የሰላም ዉይይት አካሂደዋል።
ሰላምን ለማፅናት በተለይም የመንግሥት ሰራተኛዉ ማኅብረሰብ ስለ ሰላም ማወቅና የሰላም ግንባታን ባህል ማድረግ መቻል እንዳለበት የተገለፀ ሲሆን የሰላም ባህል በውጫዊ ብዝኃነት ላይ የተመሰረተ ሰብዓዊነትና የአዲስ ሥልጣኔ ፍሬ ተደርጐ ሊታይ የሚገባው ተግባር መሆኑ ተወስቷል።
ደሴ ከተማ የሰላም ተምሳሌትነቷን ለማስጠበቅ፣ ለኑሮ ምቹና ተስማሚ እንድትሆን በማድረግና ከሰላም ሥራዉ ጎን ለጎን መንግሥት ሰራተኛዉ በመደበኛ የሥራ ገበታዉ ላይ በመገኘትና የአገልጋይነት መንፈስን በመላበስ ለኅብረተሰቡ የተቀላጠፈና የላቀ አገልግሎት መሥጠት እንዳለበት ተመላክቷል።
ሰላም የህልውና ጉዳይና የሀገር ዕድገት መሰረት በመሆኑ የመንግሥት ሰራተኞች እውነተኛ ሰላም ወዳድነታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።
መረጃ፦የደሴ ከተማ ፖሊስ ህዝብ ግንኙነት ነው።
በደሴ ከተማ አስተዳደር በክ/ከተማ ደረጃ የሚገኙ የመንግሥት ሰራተኞች “ለሰላም ግንባታ የኅብረተሰቡ ሚና” በሚል ሃሳብ የሰላም ዉይይት አካሂደዋል።
ሰላምን ለማፅናት በተለይም የመንግሥት ሰራተኛዉ ማኅብረሰብ ስለ ሰላም ማወቅና የሰላም ግንባታን ባህል ማድረግ መቻል እንዳለበት የተገለፀ ሲሆን የሰላም ባህል በውጫዊ ብዝኃነት ላይ የተመሰረተ ሰብዓዊነትና የአዲስ ሥልጣኔ ፍሬ ተደርጐ ሊታይ የሚገባው ተግባር መሆኑ ተወስቷል።
ደሴ ከተማ የሰላም ተምሳሌትነቷን ለማስጠበቅ፣ ለኑሮ ምቹና ተስማሚ እንድትሆን በማድረግና ከሰላም ሥራዉ ጎን ለጎን መንግሥት ሰራተኛዉ በመደበኛ የሥራ ገበታዉ ላይ በመገኘትና የአገልጋይነት መንፈስን በመላበስ ለኅብረተሰቡ የተቀላጠፈና የላቀ አገልግሎት መሥጠት እንዳለበት ተመላክቷል።
ሰላም የህልውና ጉዳይና የሀገር ዕድገት መሰረት በመሆኑ የመንግሥት ሰራተኞች እውነተኛ ሰላም ወዳድነታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።
መረጃ፦የደሴ ከተማ ፖሊስ ህዝብ ግንኙነት ነው።