በፀጥታው ችግር ምክንያት ለጥቃት ተጋላጭ የሆኑ የሴቶችን የመደገፍ ስራ እየተሰራ መሆኑን የምዕራብ ጎጃም ዞን ሴቶች ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ገለፀ።
የምዕራብ ጎጃም ሴቶች ፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ የሴቶች የተደራጀ እና ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለዘላቂ ሰላም እና ልማት ግንባታ በሚል መሪ ቃል ከሴት የመንግስት ሰራተኞች ጋር የውይይት መድረክ በፍኖተ ሰላም ከተማ አካሂዷል።
መድረኩ ላይ የተገኙ በምዕራብ ጎጃም ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፓለቲካ ዘርፍ ኀላፊ አቶ ሙላት ጌታቸው በክልሉ የገጠመውን የሰላም እጦት በኢኮኖሚ ፣ በፓለቲካ እና ማህበራዊ ዘርፎች በርካታ ቀውሶች እያደረሰ መኾኑን ተናግረዋል።
ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት የመጀመሪያ ተጠቂዎች ሴቶች መኾናቸውን ገልፀው ለሰላም ግንባታ የሴቶች ሚና የጎላ በመኾኑ የበኩላቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።
ሴቶች በማህበራዊ ፣ በፓለቲካዊ እና ኢኮኖሚ ውስጥ ያላቸው ተሳትፎ ወሳኝ በመሆኑ ሰላምን ለመጠበቅ እና ለማሳደግ አይነተኛ አበርክቶ አለው ።
በፀጥታው ችግር ምክንያት ለጥቃት ተጋላጭ የሆኑ የሴቶች ማህበራትን በማስተባበር የመደገፍ ስራ እየተሰራ መኾኑን የምዕራብ ጎጃም ዞን ሴቶች ፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኀላፊ ስለእናት ዘሪሁን ተናግረዋል ።
በተለይም የሴት አደረጃጀቶችን በማጠናከር ሴቶች ለሰላም ግንባታ የበኩላቸውን እንዲወጡ እየተደረገ መሆኑን ገልፀው ፤ ታጥቀው ወደ ጫካ የገቡ ኃይሎችም ፊታቸውን ወደ ሰላም እንዲያዞሩ ነው ወ/ሮ ስለእናት የጠየቁት።
ሴቶች በማህበራዊ ፣ ፓለቲካ እና ኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ ጉልህ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክቱ ሁሉ አደረጃጀቶችን በመጠቀም የሰላም ግንባታ ሂደት ላይ ተሳትፏቸውን የማጠናከር ስራ እየተከናወነ መኾኑን የምዕራብ ጎጃም ዞን ሴቶች ሊግ ኀላፊ ወ/ሮ አክሊለ ዞማነህ ገልፀዋል።
በውይይት መድረኩ ላይ የተሳተፉ ሴት የመንግስት ሰራተኞችም የፀጥታ ችግሩ እያደረሰ ያለውን ጉዳት ቅድሚያ በመስጠት እና ከዚህ የከፋ ችግር ሳይከሰት ሁሉም አካላት ለውይይት እና ለድርድር ዝግጁ መሆን አለባቸው ለዚህ ደግሞ ሁሉም ማህበረሰብ ሊረባረብ ይገባል ነው ያሉት።
የምዕራብ ጎጃም ሴቶች ፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ የሴቶች የተደራጀ እና ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለዘላቂ ሰላም እና ልማት ግንባታ በሚል መሪ ቃል ከሴት የመንግስት ሰራተኞች ጋር የውይይት መድረክ በፍኖተ ሰላም ከተማ አካሂዷል።
መድረኩ ላይ የተገኙ በምዕራብ ጎጃም ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፓለቲካ ዘርፍ ኀላፊ አቶ ሙላት ጌታቸው በክልሉ የገጠመውን የሰላም እጦት በኢኮኖሚ ፣ በፓለቲካ እና ማህበራዊ ዘርፎች በርካታ ቀውሶች እያደረሰ መኾኑን ተናግረዋል።
ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት የመጀመሪያ ተጠቂዎች ሴቶች መኾናቸውን ገልፀው ለሰላም ግንባታ የሴቶች ሚና የጎላ በመኾኑ የበኩላቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።
ሴቶች በማህበራዊ ፣ በፓለቲካዊ እና ኢኮኖሚ ውስጥ ያላቸው ተሳትፎ ወሳኝ በመሆኑ ሰላምን ለመጠበቅ እና ለማሳደግ አይነተኛ አበርክቶ አለው ።
በፀጥታው ችግር ምክንያት ለጥቃት ተጋላጭ የሆኑ የሴቶች ማህበራትን በማስተባበር የመደገፍ ስራ እየተሰራ መኾኑን የምዕራብ ጎጃም ዞን ሴቶች ፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኀላፊ ስለእናት ዘሪሁን ተናግረዋል ።
በተለይም የሴት አደረጃጀቶችን በማጠናከር ሴቶች ለሰላም ግንባታ የበኩላቸውን እንዲወጡ እየተደረገ መሆኑን ገልፀው ፤ ታጥቀው ወደ ጫካ የገቡ ኃይሎችም ፊታቸውን ወደ ሰላም እንዲያዞሩ ነው ወ/ሮ ስለእናት የጠየቁት።
ሴቶች በማህበራዊ ፣ ፓለቲካ እና ኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ ጉልህ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክቱ ሁሉ አደረጃጀቶችን በመጠቀም የሰላም ግንባታ ሂደት ላይ ተሳትፏቸውን የማጠናከር ስራ እየተከናወነ መኾኑን የምዕራብ ጎጃም ዞን ሴቶች ሊግ ኀላፊ ወ/ሮ አክሊለ ዞማነህ ገልፀዋል።
በውይይት መድረኩ ላይ የተሳተፉ ሴት የመንግስት ሰራተኞችም የፀጥታ ችግሩ እያደረሰ ያለውን ጉዳት ቅድሚያ በመስጠት እና ከዚህ የከፋ ችግር ሳይከሰት ሁሉም አካላት ለውይይት እና ለድርድር ዝግጁ መሆን አለባቸው ለዚህ ደግሞ ሁሉም ማህበረሰብ ሊረባረብ ይገባል ነው ያሉት።