"ለፍትህ ስርዓቱ ውጤታማነት በትብብር መስራት ይገባል"
ምክትል ኮሚሽነርና የወንጀል ምርመራ ዘርፍ ኀላፊ ረ/ኮሚሽነር ውበቱ አለ
አማራ ፖሊስ፡ጥር/2017 ዓ.ም
የአማራ ክልል ወንጀል ምርመራ ዘርፍ የሰድስት ወራት አፈፃፀምን በገመገመበት ወቅት ንግግር ያደረጉት የኮሚሽኑ ወንጀል ምርመራ ዘርፍ ኀላፊ ረዳት ኮሚሽነር ውበቱ አለ በዘንድሮው ግማሽ ዓመት በተፈለገው አግባብ ተንቀሳቅሶ ለመስራት እንቅፋቶች ቢኖሩም በብዙ ችግሮች ውስጥ ሆኖ በግማሽ ዓመቱ ከቀረቡ 5453 መዝገቦች 4725ቱ ተጣርተው ለዐቃቤ ህግ ተልከዋል። ይህም የምርመራ የማጣራት ዐቅምን 86.9 በመቶ ያደርሰዋል ብለዋል።
ምንም እንኳን ወቅቱ ፈታኝ ቢሆንም በተፋጠነ የፍትህ ስርዓት መታዬት ከነበረባቸው 1108 መዝገቦች 956ቱን በማቅረብ 86.4 በመቶ መፈፀምም ተችሏል።
በወንጀል ምርመራ ዘርፍ የታክቲክ ወንጀል ምርመራ ም/ዘርፍ ኀላፊ ረዳት ኮሚሽነር ክንዱ ወንዴ በበኩላቸው የነበሩንን ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለዬት ድክመቶቻችንን አርመን የቀጣይ አቅጣጫ ማስቀመጥ ይኖርብናል ብለዋል።
ምክትል ኮሚሽነርና የወንጀል ምርመራ ዘርፍ ኀላፊ ረ/ኮሚሽነር ውበቱ አለ
አማራ ፖሊስ፡ጥር/2017 ዓ.ም
የአማራ ክልል ወንጀል ምርመራ ዘርፍ የሰድስት ወራት አፈፃፀምን በገመገመበት ወቅት ንግግር ያደረጉት የኮሚሽኑ ወንጀል ምርመራ ዘርፍ ኀላፊ ረዳት ኮሚሽነር ውበቱ አለ በዘንድሮው ግማሽ ዓመት በተፈለገው አግባብ ተንቀሳቅሶ ለመስራት እንቅፋቶች ቢኖሩም በብዙ ችግሮች ውስጥ ሆኖ በግማሽ ዓመቱ ከቀረቡ 5453 መዝገቦች 4725ቱ ተጣርተው ለዐቃቤ ህግ ተልከዋል። ይህም የምርመራ የማጣራት ዐቅምን 86.9 በመቶ ያደርሰዋል ብለዋል።
ምንም እንኳን ወቅቱ ፈታኝ ቢሆንም በተፋጠነ የፍትህ ስርዓት መታዬት ከነበረባቸው 1108 መዝገቦች 956ቱን በማቅረብ 86.4 በመቶ መፈፀምም ተችሏል።
በወንጀል ምርመራ ዘርፍ የታክቲክ ወንጀል ምርመራ ም/ዘርፍ ኀላፊ ረዳት ኮሚሽነር ክንዱ ወንዴ በበኩላቸው የነበሩንን ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለዬት ድክመቶቻችንን አርመን የቀጣይ አቅጣጫ ማስቀመጥ ይኖርብናል ብለዋል።