በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ወገራ ወረዳ ነፍጥ አንስተው ሲዋጉ የነበሩ ታጣቂዎች የመንግስትን የሠላም ጥሪ ተቀብለው ወደማህበረሰቡ ተወላቅለዋል።
የወገራ ወረዳ ሠላምና ደህንነት ኃላፊ አቶ ደሴ አስናቀው በምህረት የገቡ ተዋጊዎችን በተቀበሉበት ወቅት እንዳሉት መገዳደል ይብቃ ህዝባችን ስቃዩ በዝቷል ሰላሙን አግኝቶ በሙሉ አቅሙ ወደ ልማት ሊገባ ይገባል ያሉ ሲሆን ይህ የሚሆነው ደግሞ ጫካ የገቡት ሁሉም አካላት መንግስት እያቀረበ ያለውን የሰላም ጥሪ ተቀብለው መምጣት ሲችሉ ነው ብለዋል፡፡
ይህ እንዲሆን የፀጥታ አካላትና የሀገር ሽማግሌዎች ጥረት ከፍተኛ ነበር ያሉት ኃላፊው በዚህም አስራ ስምንት(18)የሚሆኑ ታጣቂዎች በሰላም ወደ ማህበረሰቡ የገቡ ሲሆን ከዚህ ውስጥ አስራ ሦስት የሚሆኑት እስከ ሙሉ ትጥቃቸው ተቀላቅለዋል ነው ያሉት።
አሁንም ሌሎች ተዋጊዎችም የመንግስትን የሠላም ጥሪ በመቀበል ምህረት እንዲገቡ ነው ኃላፊው ጥሪ ያቀረቡት ።
መረጃው፦የወገራ ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን ነው።
የወገራ ወረዳ ሠላምና ደህንነት ኃላፊ አቶ ደሴ አስናቀው በምህረት የገቡ ተዋጊዎችን በተቀበሉበት ወቅት እንዳሉት መገዳደል ይብቃ ህዝባችን ስቃዩ በዝቷል ሰላሙን አግኝቶ በሙሉ አቅሙ ወደ ልማት ሊገባ ይገባል ያሉ ሲሆን ይህ የሚሆነው ደግሞ ጫካ የገቡት ሁሉም አካላት መንግስት እያቀረበ ያለውን የሰላም ጥሪ ተቀብለው መምጣት ሲችሉ ነው ብለዋል፡፡
ይህ እንዲሆን የፀጥታ አካላትና የሀገር ሽማግሌዎች ጥረት ከፍተኛ ነበር ያሉት ኃላፊው በዚህም አስራ ስምንት(18)የሚሆኑ ታጣቂዎች በሰላም ወደ ማህበረሰቡ የገቡ ሲሆን ከዚህ ውስጥ አስራ ሦስት የሚሆኑት እስከ ሙሉ ትጥቃቸው ተቀላቅለዋል ነው ያሉት።
አሁንም ሌሎች ተዋጊዎችም የመንግስትን የሠላም ጥሪ በመቀበል ምህረት እንዲገቡ ነው ኃላፊው ጥሪ ያቀረቡት ።
መረጃው፦የወገራ ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን ነው።