በተሁለደሬ ወረዳ በመግደል ሙከራ ወንጀል ተከሶ በሌለበት የተፈረደበት በቁጥጥር ስር ውሏል።
የካቲት 27 ቀን 2017 ዓ.ም
በደቡብ ወሎ ዞን ተሁለደሬ ወረዳ የመግደል ሙከራ ከተፈፀመ በኋላ በዋስ እንደተፈታ ከህግ ተሰውሮ በሌለበት የተፈረደበት በቁጥጥር ስር መዋሉን የወረዳው ፖሊስ ገለፀ፡፡
ተከሳሹ ሁሴን ታደሰ ኢብራሒም ሊፈረድበት የቻለው ግንቦት 19 ቀን 2015 ዓ.ም በተሁለደሬ ወረዳ 017 ቀበሌ ልዩ ቦታው ሰግለን የተባለው ስፍራ በዕለታዊ ግጭት ተነሳስቶ ጎረቤቱን በያዘው ክላሽንኮቭ ጠመንጃ ተኩሶ ይስተዋል።
የወረዳው ፖሊስም በደረሰው ጥቆማ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር አውሎ የምርመራ መዝገቡን በሰውና በቴክኒክ ማስረጃ ካጣራ በኋላ ለሚመከተው የፍትህ አካል ልኳል።
ግለሰቡም የክስ ሂደቱን ከስር ውጭ ሆኖ እንዲከታተል የተሰጠውን የዋስትና መብቱን ተጠቅሞ ከማረሚያ ቤት ከወጣ በኋላ ይሰውራል። የደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ተከሳሽ በሌለበት ጉዳዩን ሲመረምር ቆይቶ የካቲት 10 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሹ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ 7 ዓመት ፅኑ እስራት ይወስንበታል።
የወረዳው ፖሊስም ተከሳሽን ሲያፈላልግ ከቆዬ በኋላ የካቲት 26 ቀን 2017 ዓ.ም በሐይቅ ከተማ ከማህበረሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት በቁጥጥር ስር አውሎ የእስር ጊዜውን እንዲፈፅም ለሐይቅ ማረሚያ ቤት አስክቧል።
መረጃው ፡- የደ/ወሎ ዞን ተሁለደሬ ወረዳ ፖሊስ ኮሙኒኬሽንና ሚዲያ ክፍል ነው።
የካቲት 27 ቀን 2017 ዓ.ም
በደቡብ ወሎ ዞን ተሁለደሬ ወረዳ የመግደል ሙከራ ከተፈፀመ በኋላ በዋስ እንደተፈታ ከህግ ተሰውሮ በሌለበት የተፈረደበት በቁጥጥር ስር መዋሉን የወረዳው ፖሊስ ገለፀ፡፡
ተከሳሹ ሁሴን ታደሰ ኢብራሒም ሊፈረድበት የቻለው ግንቦት 19 ቀን 2015 ዓ.ም በተሁለደሬ ወረዳ 017 ቀበሌ ልዩ ቦታው ሰግለን የተባለው ስፍራ በዕለታዊ ግጭት ተነሳስቶ ጎረቤቱን በያዘው ክላሽንኮቭ ጠመንጃ ተኩሶ ይስተዋል።
የወረዳው ፖሊስም በደረሰው ጥቆማ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር አውሎ የምርመራ መዝገቡን በሰውና በቴክኒክ ማስረጃ ካጣራ በኋላ ለሚመከተው የፍትህ አካል ልኳል።
ግለሰቡም የክስ ሂደቱን ከስር ውጭ ሆኖ እንዲከታተል የተሰጠውን የዋስትና መብቱን ተጠቅሞ ከማረሚያ ቤት ከወጣ በኋላ ይሰውራል። የደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ተከሳሽ በሌለበት ጉዳዩን ሲመረምር ቆይቶ የካቲት 10 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሹ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ 7 ዓመት ፅኑ እስራት ይወስንበታል።
የወረዳው ፖሊስም ተከሳሽን ሲያፈላልግ ከቆዬ በኋላ የካቲት 26 ቀን 2017 ዓ.ም በሐይቅ ከተማ ከማህበረሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት በቁጥጥር ስር አውሎ የእስር ጊዜውን እንዲፈፅም ለሐይቅ ማረሚያ ቤት አስክቧል።
መረጃው ፡- የደ/ወሎ ዞን ተሁለደሬ ወረዳ ፖሊስ ኮሙኒኬሽንና ሚዲያ ክፍል ነው።