ቤስት - ሚዲያ 🇪🇹🇪🇹🇪🇹


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


🇪🇹🇪🇹🇪🇹ስለ እናት ሀገራችን ኢትዮጵያ ቀን በቀን የሚወጡ ዜናዎችን እና እንዲሁም አለም አቀፍ መረጃዎችን ወደ እናንተ እናደርሳለን 🙏ሰላምና ፍቅር ለእናት ሀገራችን ይሁን❤
👉 ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ @Gebrel or @Wizbeki7 ያናግሩን።

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


💋 Sex Or Love❣⁉️






የ125 ብር ካርድ ሊለቀቅ ነው 9 ደቂቃ ብቻ ነው የቀረው። ቶሎ ከስር JOIN ሚለውን ነክታቹ JOIN REQUEST ላኩ 🏃‍♀️🏃‍♂️


ጎልልልልልልልልልል ሮናልዶዶዶዶ

ሮናልዶ አሁን ለአል ናስር ተገልብጦ ያስቆጠራትን አስደናቂ ኳስ ይመልከቱ 👇👇
https://t.me/+4JpAYkA-01QyMDU8


ፒኤስፒ ከ ሊቨርፑል የሚያደርጉትን የቻምፒየንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ በስልኮ ለመከታተል LIVE ሚለዉን ይጫኑት 👇👇👇
https://t.me/addlist/fDJhM0jRWXAwOGVk






የዩክሬኑን ፕሬዝዳንት ያበሻቀጡት የአሜሪካው ም/ፕሬዚደንት ጄዲ ቫንስ ቤተሰብ በመቶዎች የሚቆጠሩ የዩክሬን ደጋፊ ተቃዋሚዎች የቬርሞንት የእረፍት ጊዜ ማሳለፊያውን ካጨናነቁ በኋላ ወደ 'ያልታወቀ ቦታ' ተዛውረዋል።

@Ethiobestzena


❗ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ እኔን መተካት ከባድ ነው አሉ

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ሀገራቸው የኔቶ አባል ከሆነች በምትኩ ስልጣን እንደሚለቁ ተናግረዋል

የአሜሪካ ፖለቲከኞች ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ለቦታው አይመጥኑም የሚል ሀሳቦችን እያንሸራሸሩ ይገኛሉ

@Ethiobestzena


ከዛሬ ጀምሮ የኢትዮ ጅቡቲ የባቡር መንገደኞች የጉዞ ትኬታቸውን በቴሌብር አማካኝነት ብቻ መቁረጥ ይጠበቅባቸዋል ተባለ

ደንበኞች የብሔራዊ መታወቂያ ከሌላቸው የተቋሙ አገልግሎት ማግኘት እንደማይችሉም ተነግሯል

የኢትዮ ጅቡቲ የባቡር መንገድ አክስዮን ማህበር ከዛሬ የካቲት 24 ጀምሮ መንገደኞች የጉዞ ትኬታቸውን በቴሌብር አማካኝነት ብቻ መቁረጥ እንደሚጠበቅባቸው አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ጅቡቲ ባቡር አክስዮን ማህበር ከፍተኛ የኮሙኒኬሽን ባለሙያ ወይዘሮ እስራኤል ወልደመስቀል ለኢፕድ እንደገለጹት፤ የመንገደኞችን እንግልት ለመቀነስና ለጋራ ደህንነት መንገደኞች ከዛሬ ጀምሮ የጉዞ ትኬታቸውን በቴሌብር አማካኝነት በመቁረጥ አገልግሎቱን ማግኘት እንዲችሉ ተደርጓል።

ማህበሩ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓቱን ዲጂታላይዝድ ማድረጉን የገለጹት ባለሙያዋ፤ ደንበኞች የብሔራዊ መታወቂያ ከሌላቸው የተቋሙ አገልግሎት ማግኘት እንደማይችሉም ተናግረዋል።

ይህንንም ለደንበኞች የማሳወቅ ሥራው ከአንድ ወር በፊት ጀምሮ ሲሰራ እንደነበርና ከብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጋር በመተባበር መታወቂያውን እንዲያገኙት እየተደረገ እንደነበር አስታውሰዋል።

የብሔራዊ መታወቂያ ተግባራዊነቱ ለሀገር ውስጥ ተጠቃሚዎች ብቻ ሲሆን፤ ኢትዮጵያዊ ላልሆኑ ተጠቃሚዎች ፓስፖርታቸውን በመጠቀም ትኬት ማግኘት እንደሚችሉ ወይዘሮ እስራኤል ገልጸዋል።

በኦንላይን ትኬት የመቁረጥ አገልግሎት ተግባራዊ መደረግ መጀመሩ ይታወሳል።

@Ethiobestzena


አውሮፓ የሩሲያን ጥቃት ለመመከት ተጨማሪ 1000 የኑክሌር አረሮች ያስፈልጓታል ተባለ

የአሜሪካው ፕሬዝደንት ትራምፕ ለአውሮፓ የሰጡትን የደህነት ዋስትና ያነሳሉ የሚለው ስጋት አውሮፓውያን ከአሜሪካ ነጻ ሆነው ራሳቸውን የሚከላከሉበትን ለመቀየስ እየወያዩ ይገኛሉ።

@Ethiobestzena


ከ50 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የንብረት ስርቆት እና ውድመት እንደተፈጸመበት አገልግሎቱ አስታወቀ

በበጀት ዓመቱ ባለፉት ሰባት ወራት 50 ሚሊየን 222 ሺህ 987 ነጥብ 7 ብር የሚገመት የንብረት ስርቆት እና ውድመት እንደተፈጸመበት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ። አገልግሎቱ በ22 የተቋሙ አመራርና ሠራተኞች ላይ ርምጃ መውሰዱንም ገልጿል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ ዛሬ ባወጣው መግለጫ የተፈፀመው ስርቆትና ውድመትም የኃይል ስርቆት፣ የትራንስፎርመር ስርቆት፣ የኤሌክትሪክ መስመር ጉዳት፣ የመሰረተ ልማት ስርቆት፣ የተቋሙ ሠራተኞችን ሥራ እንዳይሠሩ ማወክና የኬብል ስርቆትን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጿል።

በሰባት ወራት ውስጥ ብቻ 163 የኃይልና መሰረተ-ልማት ስርቆት ወንጀል መፈጸሙን የገለጸው ተቋሙ ከእነዚህ መካከል 11 የወንጀል ጉዳዮች ውሳኔ ማግኘታቸውን አስታወቋል። በዚህም 13 ተከሳሾች ከሁለት ወር ቀላል እስራት እስከ 10 ዓመት ፅኑ እስራት እና እስከ 50 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ መቀጣታቸውን አክሎ ገልጿል፡፡

ባሳለፍነው ሳምንት ከ መተሃራ እስከ ባቡር ትራክሽን ጣቢያ አንድ ድረስ ከ80 ኪሎ ሜትር በላይ የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ እና 25 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የኦፕቲካል ፋይበር መስመር በአስር ቀናት ውስጥ መዘረፉን ተቋሙ ማስታወቁ ይታወሳል።

ይህ በእንዲህ እያለ ከደንበኞች የቀረቡ የብልሹ አሠራርና ሙስና ጥቆማዎችን መሰረት በማድረግ በ22 አመራርና ሠራተኞች ላይ አሥተዳደራዊ ርምጃ መውሰዱንም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በመግለጫው አስታወቋል፡፡ በዚሁ መሠረት አስፈላጊው ማጣሪያ ተደርጎ ሦስቱ በጽሑፍ ማስጠንቀቂያ እና 19ኙ ደግሞ በደመወዝ ቅጣት መቀጣታቸውን ነው ያስታወቀው፡፡

@Ethiobestzena


🚨ነዳጅ

የነዳጅ ምርቶች ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ተብሏል።

የመጋቢት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።


➡ አንድ ሊትር ቤንዚን 101.47 ብር

➡ አንድ ሊትር ናፍጣ 98.98 ብር

➡ አንድ ሊትር ኬሮሲን 98.98 ብር

➡ የአውሮፕላን ነዳጅ 109.56 ብር

➡ አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ 105.97 ብር

➡ አንድ ሊትር ቀላል ጥቁር ናፍጣ 108.30 ብር

@Ethiobestzena


በቶኪዮ ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች አሸነፉ

በቶኪዮ ማራቶን በሁለቱም ጾታ ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በበላይነት አጠናቅቀዋል።

በወንዶች ታደሰ ታከለ ሲያሸንፍ በሴቶች ደግሞ አትሌት ሱቱሜ አሰፋ በበላይነት አጠናቅቃለች።

በዓለም አትሌቲክስ የፕላቲኒየም ደረጃ በተሰጠው ማራቶን በሴቶች አትሌት ሱቱሜ አሰፋ 2 ሰዓት ከ16 ደቂቃ ከ31 ሰከንድ በመግባት በአንደኝነት አሸንፋለች።

በወንዶች የቶኪዮ ማራቶን አትሌት ታደሰ ታከለ በ2 ሰዓት ከ03 ደቂቃ ከ23 ሰከንድ በመግባት የግል ምርጥ ሰዓቱን ጭምር በማሻሻል አሸንፏል።

አትሌት ደረሳ ገለታ በ2 ሰዓት ከ03 ደቂቃ ከ51 ሰከንድ በመግባት ሁለተኛ ደረጃ ይዞ ማጠናቀቁን ከአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።

@Ethiobestzena


ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን(ቴዲ አፍሮ) የአድዋ ድል በዓልን በማስመልከት ያስተላለፈው መልዕክት።

@Ethiobestzena


የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለእስራኤል የ4 ቢሊዮን ወታደራዊ እርዳታ በአስቸኳይ እንዲደርሳት ማዘዛቸውን ገለጹ

የትራምፕ አስተዳደር በቅርብ ሳምንታት ውስጥ መሳሪያዎችን በፍጥነት ለእስራኤል ለመሸጥ የአስቸኳይ ጊዜ ስልጣን ሲጠቀም ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ነው ተብሏል።

@Ethiobestzena


"የገሃነም በሮች የሚከፈቱበት ጊዜ አሁን ነው

መብራት እና ውሃ ማቋረጥ፣ ወደ ጦርነት መመለስ - "

የእስራኤል የቀድሞ ባለስልጣን ቤን ጊቪር ወደ ጋዛ ከበባ ፈጣን እና ጭካኔ የተሞላበት መመለስን ደግፈው ተናገረዋል።

@Ethiobestzena


❗የውጭ ዜጋ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ወደ አገሪቱ እንዳይገቡ የሚያግድ ሕግ እየተዘጋጀ ነው

የአሜሪካው ተራድዖ ድርጅት (ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ) የገንዘብ እርዳታ ካቆመ ወዲህ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚንቀሳቀሱ መንግሥታዊ ያልኾኑ ድርጅቶች መካከል 85 በመቶዎቹ ሥራቸውን ማቆማቸውን ሪፖርተር ዘግቧል።

በተለይ በሰብዓዊ መብቶች፣ በሰላም፣ በጤና እና ልማት ዘርፎች የሚሠሩ ድርጅቶች ይበልጥ ተጎጂ እንደኾኑ የጠቀሰው ዘገባው፣ በትግራይ ለ100 ሺሕ የጦርነት ተፈናቃዮች ንጹህ የመጠጥ ውሃ ያቀርብ የነበረ መንግሥታዊ ያልኾነ ድርጅትም ሥራ ማቆሙን አመልክቷል።

መንግሥትም፣ የውጭ ዜጋ የሆኑ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ወደ አገሪቱ እንዳይገቡ የሚያግድ ሕግ እያዘጋጀ መኾኑን ምንጮች መናገራቸውን የዜና ምንጩ ዘገባ ያመለክታል።

@Ethiobestzena


ዓድዋ‼️

"ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል!"
እንኳን ለ129ኛዉ የዓድዋ ድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ -አደረሰን!

@Ethiobestzena

Показано 20 последних публикаций.