በቶኪዮ ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች አሸነፉ
በቶኪዮ ማራቶን በሁለቱም ጾታ ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በበላይነት አጠናቅቀዋል።
በወንዶች ታደሰ ታከለ ሲያሸንፍ በሴቶች ደግሞ አትሌት ሱቱሜ አሰፋ በበላይነት አጠናቅቃለች።
በዓለም አትሌቲክስ የፕላቲኒየም ደረጃ በተሰጠው ማራቶን በሴቶች አትሌት ሱቱሜ አሰፋ 2 ሰዓት ከ16 ደቂቃ ከ31 ሰከንድ በመግባት በአንደኝነት አሸንፋለች።
በወንዶች የቶኪዮ ማራቶን አትሌት ታደሰ ታከለ በ2 ሰዓት ከ03 ደቂቃ ከ23 ሰከንድ በመግባት የግል ምርጥ ሰዓቱን ጭምር በማሻሻል አሸንፏል።
አትሌት ደረሳ ገለታ በ2 ሰዓት ከ03 ደቂቃ ከ51 ሰከንድ በመግባት ሁለተኛ ደረጃ ይዞ ማጠናቀቁን ከአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።
@Ethiobestzena
በቶኪዮ ማራቶን በሁለቱም ጾታ ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በበላይነት አጠናቅቀዋል።
በወንዶች ታደሰ ታከለ ሲያሸንፍ በሴቶች ደግሞ አትሌት ሱቱሜ አሰፋ በበላይነት አጠናቅቃለች።
በዓለም አትሌቲክስ የፕላቲኒየም ደረጃ በተሰጠው ማራቶን በሴቶች አትሌት ሱቱሜ አሰፋ 2 ሰዓት ከ16 ደቂቃ ከ31 ሰከንድ በመግባት በአንደኝነት አሸንፋለች።
በወንዶች የቶኪዮ ማራቶን አትሌት ታደሰ ታከለ በ2 ሰዓት ከ03 ደቂቃ ከ23 ሰከንድ በመግባት የግል ምርጥ ሰዓቱን ጭምር በማሻሻል አሸንፏል።
አትሌት ደረሳ ገለታ በ2 ሰዓት ከ03 ደቂቃ ከ51 ሰከንድ በመግባት ሁለተኛ ደረጃ ይዞ ማጠናቀቁን ከአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።
@Ethiobestzena