የዓድዋ ድል በዓል በባህር ዳር እና ደሴ ከተሞች ተከበረ
*************
129ኛው የዓድዋ ድል በዓል በባህር ዳር እና ደሴ ከተሞች ተከብሯል፡፡
በዓሉ በባህር ዳር ከተማ በግዮን አደባባይ በተለያዩ ትዕይንቶች መከበሩ ታውቋል፡፡
በተመሳሳይ የዓድዋ ድል በዓል በደሴ ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት በፒያሳ አደባባይ ተከብሯል፡፡
የደሴ ከተማ ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ ፤ የዓድዋ ድል ቁልፍ ምስጢር ሀገርን ከውስጣዊ ልዩነቶች አብልጦ ማየት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ከንቲባው ድሉ በቅኝ ግዛት ስር ለነበሩ አፍሪካውያን የነጻነት ብርሃን መፈንጠቁንም አመላክተዋል፡፡
በሳሙኤል ወርቃየሁ፣ ተስፋሁን ደስታ እና ራሄል ፍሬው
*************
129ኛው የዓድዋ ድል በዓል በባህር ዳር እና ደሴ ከተሞች ተከብሯል፡፡
በዓሉ በባህር ዳር ከተማ በግዮን አደባባይ በተለያዩ ትዕይንቶች መከበሩ ታውቋል፡፡
በተመሳሳይ የዓድዋ ድል በዓል በደሴ ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት በፒያሳ አደባባይ ተከብሯል፡፡
የደሴ ከተማ ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ ፤ የዓድዋ ድል ቁልፍ ምስጢር ሀገርን ከውስጣዊ ልዩነቶች አብልጦ ማየት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ከንቲባው ድሉ በቅኝ ግዛት ስር ለነበሩ አፍሪካውያን የነጻነት ብርሃን መፈንጠቁንም አመላክተዋል፡፡
በሳሙኤል ወርቃየሁ፣ ተስፋሁን ደስታ እና ራሄል ፍሬው