🎙መድረሻህን ሳታልም ጉዞ አትጀምር ፤
#መኖርህን_ሳታውቅ_አትሙት። 🤙🤝
እኛ፤ ሰዎችና የፈጣሪ ልጅ ፍጡሮች ነን፣ በዘመን መካከል የተገኘን፤ ዘር ሲያራርቀን፣ ሃይማኖት ሲለያየን፣ ሀብት ሲመዳድበን፣ ፖለቲካ ሲከፋፍለን፥ ሕይወትም ስንፈልጋት ስትጠፋ፣ ሳንፈልጋት ስትበዛ፣ ስንከተላት ስታመልጠን፣ ስንተዋት ስትከተለን እየባከንን የምንኖር።
ሕይወት፤ የመዘጋጃና የመኖሪያ ዕድሜ የሌላት፣ ከአፈር ለተሠራ ሰው የተሰጠች ስጦታ ነች። የሰው ልጅም ከተፈጠረ ጀምሮ ሕይወትን በውስጡ ለማሰንበት በትግል የሚኖር፣ ሲያጣትም እጅግ ጠሊቅ ሐዘን ውስጥ የሚገባ ፍጡር ነው።
ሰው የራሱንና የሚወዳቸውን እስትንፋስ ለማቆየት፤ ከሰከንድ እስከ ሰዓታት ከዛሬው እየተበደረ ለማያውቀው ነገ ሲገብር፣ ለማያውቀው ነገ ደስታ ዛሬ ሲያለቅስ፣ ለማያውቀው ነገ ጥጋብ ዛሬ ሲራብ ሲታረዝ፣ ለማያውቀው ነገ ተበድሮ ዛሬ ሲጨነቅ የሚኖርና መኖሩን ሳያውቅ የሚሞት ፍጡር ...።
... የተሸከሙትን ለሕይወት የሚረባ ፍሬ፣ ዱር እንደበቀለና ሰው እንደማያገኘው መልካም ፍሬ የሚነካው ቀርቶ የሚያየው ሳይኖር ያፈራውን ተሸክሞ የሚኖር ዛፍ ዓይነት ሰዎች ምንኛ ያሳዝናሉ! ...
ሜሎሪና - ስውር ጥበብ
✍ ናሁሰናይ ፀዳሉ አበራ
#መኖርህን_ሳታውቅ_አትሙት። 🤙🤝
እኛ፤ ሰዎችና የፈጣሪ ልጅ ፍጡሮች ነን፣ በዘመን መካከል የተገኘን፤ ዘር ሲያራርቀን፣ ሃይማኖት ሲለያየን፣ ሀብት ሲመዳድበን፣ ፖለቲካ ሲከፋፍለን፥ ሕይወትም ስንፈልጋት ስትጠፋ፣ ሳንፈልጋት ስትበዛ፣ ስንከተላት ስታመልጠን፣ ስንተዋት ስትከተለን እየባከንን የምንኖር።
ሕይወት፤ የመዘጋጃና የመኖሪያ ዕድሜ የሌላት፣ ከአፈር ለተሠራ ሰው የተሰጠች ስጦታ ነች። የሰው ልጅም ከተፈጠረ ጀምሮ ሕይወትን በውስጡ ለማሰንበት በትግል የሚኖር፣ ሲያጣትም እጅግ ጠሊቅ ሐዘን ውስጥ የሚገባ ፍጡር ነው።
ሰው የራሱንና የሚወዳቸውን እስትንፋስ ለማቆየት፤ ከሰከንድ እስከ ሰዓታት ከዛሬው እየተበደረ ለማያውቀው ነገ ሲገብር፣ ለማያውቀው ነገ ደስታ ዛሬ ሲያለቅስ፣ ለማያውቀው ነገ ጥጋብ ዛሬ ሲራብ ሲታረዝ፣ ለማያውቀው ነገ ተበድሮ ዛሬ ሲጨነቅ የሚኖርና መኖሩን ሳያውቅ የሚሞት ፍጡር ...።
... የተሸከሙትን ለሕይወት የሚረባ ፍሬ፣ ዱር እንደበቀለና ሰው እንደማያገኘው መልካም ፍሬ የሚነካው ቀርቶ የሚያየው ሳይኖር ያፈራውን ተሸክሞ የሚኖር ዛፍ ዓይነት ሰዎች ምንኛ ያሳዝናሉ! ...
ሜሎሪና - ስውር ጥበብ
✍ ናሁሰናይ ፀዳሉ አበራ