እንማር


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Цитаты


እዚህ Channel ላይ ያስተምራሉ ያዝናናሉ ብለን የምናስባቸውን
🎯 መፅሀፎች
🎯ተከታታይ ልቦለድ
🎯ግጥም
🎯ፍልስፍና
🎯ምክር
የተለያዩ PDF መፅሐፍት እንደፍላጎቶ አሉ
    Ads - @Kiya988
https://youtube.com/channel/UCr7-LDddhyqtFUCH0OHhM2Q
Buy ads: https://telega.io/c/Enmare1988

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Цитаты
Статистика
Фильтр публикаций




My besti once said...."እንጀራ መሻገት ሊጀምር ሲል ታሞቂዋለሽ...አይ ነገ ላሙቀው ብትዩ መሻገቱ እየባሰበት ይሄዳል....ሳታሞቂው በቆየሽ ቁጥር መበላሸቱ ይብሳል....አሙቀሽ መብላት የምትችይውን እንጀራ ባለማሞቅሽ ምክንያት ትጥይዋለሽ....አእምሮም እንደዛው ነው....ማዳን እየቻልሽ እስኪሞት ከጠበቅሽው ይጥልሻል...."


https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka


የዘላቂ ፍቅር ሚስጥር
============
"ፍቅር ይዞኝ አልበላ፣ አልጠጣ አለኝ። ሁሌ ስለ እሷ ነው የማስበው፤ በየቀኑ ካርድ እሰከምንጨርስ ነው የምናወራው።" ያላችሁን ሰው ከሁለት አመት በኋላ ብታገኙት የያዘው ፍቅር ለቆታል። ምክኒያቱም ስሜታዊው ፍቅር እድሜው ከሁለት አመት ስለማይበልጥ። በፊት ያለ ምንም ማንገራገር ስትጠራው ወዲያውኑ "አቤት" ስትልከው ወዲያውኑ "ወዴት" ይል የነበረው የያዘው ፍቅር እየነዳው ነበር። አሁን ፍቅሩ ለቆታል። (በተለምዶ "ፀባዩ/ይዋ መለወጥ ጀመረ።" የሚባለው እዚህኛው ደረጃ ላይ ሲደረስ ነው።)

በፊት እንደሚፈቀሩ እርግጠኛ የነበሩ ሰዎች አሁን ቅር ቅር እያላቸው ይመጣል። እንደዚህ ከተሰማቸው ያሉት አማራጮች ሶስት ናቸው። የበፊቶቹ ትውልዶች ፍቅር ባይሰማቸውም፣ ደስተኛ ባይሆኑም (አንዳንዶቹ ለልጆቻቸው ሲሉ) ተቻችሎ መኖር። እንደ ባል ሳይሆን እንደ ደባል። የአሁኑ ትውልድ ደግሞ ደስተኛ ሳይሆን ሲቀር ቶሎ ወደ መለያየት። አሁን አሁን ሰዎች ልጆች ቢኖራቸውም በፍቅር ህይወታቸው ደስተኛ ካልሆኑ ይለያያሉ።

ጥሩ ዜና አለ! ከሁለቱ የተለየ ሶስተኛ አማራጭ አለ። የዘለቂ የፍቅር ቁልፍ የሆኑትን አምስቱን የፍቅር ቋንቋዎች ማወቅና መናገር። አንዳንድ ሰዎች ለፍቅራቸው ሲሉ ብዙ ነገር አድርገውም ምንም ውጤት አይኖረውም። ለዚህ ምክኒያቱ እነሱ በሚያውቁት የፍቅር ቋንቋ ፍቅራቸውን በደንብ እየገለፁ ነው። ነገር ግን አጋራቸው የሚሰማው ሌላ የፍቅር ቋንቋ ነው። ስለዚህ የነሱ ጥረት ውጤት የሌለው ይሆናል። ልክ ጃፓንኛ ብቻ ለሚሰማ ሰው በፈረንሳይኛ ቅኔ እየዘረፍሽ፣ ውብ ግጥም እየገጠምሽ ፍቅርሽን ብትገልጭለት ለሱ ትርጉም የለውም። እንደውም ሊያናድደው ሁሉ ይችላል።

"የዘላቂ ፍቅር ሚስጥር" መፅሀፍ ላይ የራሳችንን እንዲሁም የአጋራችንን የፍቅር ቋንቋ በመለየትና አነጋገሩን በማወቅ ዘላቂ የፍቅር እንዲኖረን አዲስ ምልከታ ያሳያል።

መልካም ንባብ
ዶ/ር ዮናስ ላቀው

✈️@Enmare1988
✈️@Enmare1988

4.9k 0 31 13 63

ስታሸንፍ/ ስታገኝ ትእቢትህን እና እብሪትህን መቆጣጠር ከቻልክ

.

ስትሸነፍ/ ስታጣ አስተሳሰብህን እና ምላስንህ መቆጣጠር ከቻልክ

👇🏾

አለም የአንተ ናት !!

🙌🏼❤️


✈️@Enmare1988
✈️@Enmare1988

5.4k 0 27 2 136

"...'እውነት አታብዛ'........አይደል ያሉት ጋሽ ስብሀት....እስኪ ሞክረው....ወጥ ሰው ሆነህ ሞክረው....እውነትን ብቻ ብትላበስ ከአንዳንድ ሰዎች ጋር መኖር ያቅትሀል....ውሸትን ብቻ ብትላበስ ደግሞ ከራስህ ጋር መኖር አትችልም....ሰው ድብልቅልቅ ነው....ሰው ቡናውን ወይም ወተቱን ብቻ አይደለም....ሰው እንደ ማክያቶ ነው....የቡናው መራራነት ሊያርቅህ ሲል የወተቱ ለስላሳነት ደግሞ ይመልስሀል....ሰው መራራውም ጣፋጩም ነው....ማማረርህን ትተህ መራራውን በጣፋጩ እያረከስክ መኖሩ ይሻላል....."

"እንዴት...."

"የሰውን መጥፎነቱን ብቻ ሳይሆን መልካምነቱንም አጉልቶ የሚያሳይ ፍቅር የበዛበት አይን ስጠኝ እያልክ የፈጠረህን በመጠየቅ...."

"እስከመቼ...."....ጠየቀኝ...

"ወደመጣንበት እስክንሄድ...."




✍Shewit



https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka


“ስለእንስሳት ባህሪ እና ሕክምና አላጠናሁም። ነገር ግን ክርክር ከመጀመሬ በፊት አህያው የቱ እንደሆነ የማወቅ ብቃት አለኝ።” 😌

             ―ማርክ ትዌይን

Credit አርምሞ

✈️@Enmare1988
✈️@Enmare1988

6.2k 0 39 3 157

"ለምንድን ነው የማትወጂውን ወተት አይንሽን ጨፍነሽ የምትጠጭው...."

"አንድ ጓደኛዬ ውስጡ ስላለው nutrient ነግራኝ....".....ሳውቃት ለራሷ እንደነገሩ ነበረች....ካልሞረሞራት አትበላም....በባዶ ሆዷ ውስኪ ስትጨልጥ ለጉበቷ አታዝንለትም ነበር....ፍቅር ከጀመርን በኃላ ነው ስለ organዎቿ አብዝታ መጨነቅ እና መጠንቀቅ የጀመረችው.....


"ቶሎ እንዳላረጅብህ....አሮጊት አገባ እንዳትባልብኝ....".....ስትለኝ እድሜዬን ጠላሁት....የሰባት አመት ታላቄ ናት....እያወቅኩ ነው ያፈቀርኳት......እኔ ስመረቅ ስል እሷ ደግሞ ታናሽ እህቷን ስታስመርቅ ነው የተዋወቅነው....እውነቱን ለመናገር እድሜዋን ካላስታወሰችኝ በቀር ትዝ ብሎኝ አያውቅም....ስሜ እስኪጠፋኝ አፈቅራታለሁ...

አንድ የምፈራው አባባል አለቻት...."ተፈጥሮ ባለጌ ነው....ለወንድ ያደላል....".....ትላለች...."ይብራራ" ብያት ነበረ...

"እድሜያችሁ ሲጨምር ይበልጥ የሚያምርባችሁ ነገር አለ....ያናዳል...."....ብላ ሳቅ አለች....

"አቤት ምቀኝነት....".....አብረን ሳቅን....

"እስከመቼ ትወደኛለህ" ላለቺኝ የመለስኩላት "እስከዘላለም".... ነበር....."እስከዛሬ እስከአሁን እወድሻለሁ" ነው ሚባለው ብላ አረመችኝ እንጂ....

"ነገን አታምኚው....እንዴት አምነሽ ነው የምትጠብቂኝ...."....ብያት አውቃለሁ....

"ተይዤ....".....መልሷ ነው....

እሷን በፍቅር ማሰር...በእሷ መፈቀር ምን ያሀል ደስ እንደሚል....እንደመጠበቅ ያለ እድለኝነት አለ.....?....በመጠበቅ ውስጥ መታመን አለ....መታመን ደግሞ ደስ ይላል...በተለይ በእሷ መታመን....ታምነኛለች....


በሀያ ስምንት አመቴ ድል ባለ ሰርግ አገባኃት...."ታላቁ ሳትሆን አትቀርም....".....ተባለላት....."እናቱን አገባ...."...ተባለልኝ...."አሳድጋው ነው ያገባችው መቼስ....".....ተባለላት...."እንደው ትወልድ ይሆን...."....ያለችው እናቴ ናት....."ለብሯ ብሎ ነው አሉ...."....ያለም አልጠፋም.....እነዚህን ሁሉ ሰዎች በአመቱ ክርስትና ጠራናቸው.....


በድጋሚ ፍቅር ውሎ ይግባ....


✍Shewit



https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka

6.7k 0 26 6 170



የመጨረሻ ልጅ ነኝ ቤተሰቦቼ ሲያዩኝ የኖሩት ቀዳዳዬን ሊሰፉ ፣ የጎደለኝን ሲሞሉልኝ ነው ። ዝምታዬ ቦታ አለው ይታይም ነበር ።

አደኩኝ እና ከአለም ተቀላቀልኩ!

የተወደድኩ ከመሰለኝ perfect man ለመምሰል መጣር አቆማለሁ ተራራ ጫፍ ቆሜ ጀርባዬን እሰጣለሁ ። እድሜልክ የሚያስፈርድብኝ ጉዳይ ለማንም አታውሩ ሳልል አጋራለሁ ...

እንደማምናቸው የሚያምኑኝ ይመስለኛል ስህተቴን በፋይል በፋይል የሚያደራጁት አይመስለኝም ።

አስቤ ያልጨረስኩትን ያላለቀ ሃሳቤን አጋራለው ። ተሳክቶልኝ እና ወድቄ የተሰሙኝ ስሜቶች እንደወረደ እተርካለሁ

የኔ ያልኳቸው መጉደሌ የሚያርቃቸው አይመስለኝም ። ለፍርድ የሚያቀርቡኝ የሚወስኑብኝ የሚያስፈርዱብኝ አይመስለኝም !

እነሱ ላይ መጨከን ስለማልችል የሚጨክኑብኝ አይመስለኝም ።

አለም አወቃቀሩ እንደ ቤተሰብ አይነት አለመሆኑን ለማወቅ ስንት የሃዘን ጅራፍ እላዬ ላይ እንዳረፈ !!

ጅራፉ የፈጠረብኝ ማንነት እንዴት ፈሪ እንዳደረገኝ... ማመኔ የወለደው ጥርጣሬ ብዛት መዓት ሆነ ። ውልቃቴ ንቅናቄ እንዳይኖረው እንዴት በጥንቃቄ እንደምራመድ ።

አረማመዴ ላይ የሚሰጡ አስተያየቶች እንዴት ጉዳዬ እንደማልላቸው ። አለምን እንዴት እንደማላምናት !

እንደ ዘበት የሰማሁት ተረተረት እንዴት አንደፍልስፍና መቁጠር እንደጀመርኩ
።ቃላቸውን ከበሉ ለቃላቸው እረጅም ርቀት የሚሄዱ ሲገጥሙኝ እንዴት እንደምደነግጥ !! በድያቸው አፀፋውን ከመለሱ እንዲሁ የተውኝ እንዴት እንዳሳመሙኝ!!

እኔ ብሆን ኖሮ ፣እኔ ማለት ፉከራ እና ሽለላ መኖር እንዴት እርግፍ አድርጎ እንዳስተወኝ ።
ቅዱስ ነኝ ከሚሉ ሌቦች ሌባነኝ የሚሉ ሌቦች እንዴት እንደማይጎረብጡኝ ። ለመወዳጀነትም አልፀየፋቸውም ።

በርግጥ ችግሩ የመጨረሻ ልጅ መሆን አይደለም ።🙌

© Adhanom Mitiku


ከአንድ ወዳጄ አንድ ስጋ ቤት ፊት ለፊት እዚያው መኪናችን ውስጥ ራት አስመጥተን እየበላን ነው

👇🏾

በጨዋታችን መካከል የመኪናውን መስኮት ለመድረስ የሚጣጣር አንድ ህጻን ልጅ "አባ እርቦኛል" ሲል ሰማነው: ልጁ በግምት አምስት አመት ቢሆነው ነው

"እርቦኛል አባ"

ጨዋታችንን አቋርጬ :አንድ ጉርሻ ጠቀለልኩና "ና በዚህ በኩል ላጉርስህ: ከእኛ ጋር እንብላ" አልኩት የያዝኩትን ጉርሻ እያሳየሁት

"አይ አልጎርስም :ይቅርብኝ" አለኝ

"እርቦኛል አላልክም እንዴ? ና እንጂ" ስለው

"አይ እኔ ሙስሊም ነኝ" አለኝ : ፊቱ ላይ ያለው ስሜት ይገርማል

👇🏾

ረሃብ የፈተነው አንጀት vs የእምነት ጽናት !

እኛ የዕለቱን እራት በራሱ እምነት መገብነው: ያመነው አምላክ ደግሞ ቀሪውን እንዲመግበው ተመኘንለት !!

❤️🙌🏼

Zamalik Endris

7.2k 0 24 3 286

Linkdin ከ 30በላይ Follow ያላችሁ

በአሪፍ ዋጋ እየገዛን እንገኛለን

ከተከፈተ 2 አመት መሙላት አለበት

✔️ክፍያ : 🏦 🏦 🏦 🏦 🏦 🏦 🏦

ለመሸጥ ምትፈልጉ  inbox
👉

✈️@Kiya988
✈️@Kiya988


🎙መድረሻህን ሳታልም ጉዞ አትጀምር ፤
#መኖርህን_ሳታውቅ_አትሙት። 🤙🤝

እኛ፤ ሰዎችና የፈጣሪ ልጅ ፍጡሮች ነን፣ በዘመን መካከል የተገኘን፤ ዘር ሲያራርቀን፣ ሃይማኖት ሲለያየን፣ ሀብት ሲመዳድበን፣ ፖለቲካ ሲከፋፍለን፥ ሕይወትም ስንፈልጋት ስትጠፋ፣ ሳንፈልጋት ስትበዛ፣ ስንከተላት ስታመልጠን፣ ስንተዋት ስትከተለን እየባከንን የምንኖር።

ሕይወት፤ የመዘጋጃና የመኖሪያ ዕድሜ የሌላት፣ ከአፈር ለተሠራ ሰው የተሰጠች ስጦታ ነች። የሰው ልጅም ከተፈጠረ ጀምሮ ሕይወትን በውስጡ ለማሰንበት በትግል የሚኖር፣ ሲያጣትም እጅግ ጠሊቅ ሐዘን ውስጥ የሚገባ ፍጡር ነው።

ሰው የራሱንና የሚወዳቸውን እስትንፋስ ለማቆየት፤ ከሰከንድ እስከ ሰዓታት ከዛሬው እየተበደረ ለማያውቀው ነገ ሲገብር፣ ለማያውቀው ነገ ደስታ ዛሬ ሲያለቅስ፣ ለማያውቀው ነገ ጥጋብ ዛሬ ሲራብ ሲታረዝ፣ ለማያውቀው ነገ ተበድሮ ዛሬ ሲጨነቅ የሚኖርና መኖሩን ሳያውቅ የሚሞት ፍጡር ...።

... የተሸከሙትን ለሕይወት የሚረባ ፍሬ፣ ዱር እንደበቀለና ሰው እንደማያገኘው መልካም ፍሬ የሚነካው ቀርቶ የሚያየው ሳይኖር ያፈራውን ተሸክሞ የሚኖር ዛፍ ዓይነት ሰዎች ምንኛ ያሳዝናሉ! ...

ሜሎሪና - ስውር ጥበብ
✍ ናሁሰናይ ፀዳሉ አበራ


"የተበቀለኝ ምንም ማድረግ የማልችልበትን ጊዜ መርጦ ነው....የታሰርኩበትን ጊዜ ጠብቆ ቀጣኝ....".....አለችኝ....

"እንዴት....".....

"ስተሳሰር ጠብቆ የፈሪ ዱላውን አቀመሰኝ....የፈሪ ዱላ ያማል....የቀመሰ ነው የሚያውቀው....ባለቀ ሰአት ነው ዱላውን ያነሳው....ባለቀ ሰአት ነው ሁሉም ነገር ውሸት እንደነበር የገባኝ....".....ፊት ለፊቷ ያለውን መጠጥ በአንድ ትንፋሽ ፀጥ አድርጋው ቀጠለች....

"ለስድስት ሰአት ቀጠሮ ዘጠኝ ሰአት ስደርስ በትዕግስት ሲጠብቀኝ ትዝ ይለኛል....ያኔ ብዙ አማራጭ ነበረኝ....'እገሌን ከእገሌ' እያልኩ የማወዳድር ሴት ነበርኩ....ትዕግስቱን ከሌሎች ጋር አወዳደርኩት....በለጣቸው....ትዕግስተኛ ሳይሆን ጊዜ ጠባቂ እንደነበር የገባኝ ዘግይቶ ነው...

'ግን በምን በለጥካቸው....'....ብለሽ የምትዘፍኚለት ሰው አልነበረም....በሁሉም ይበልጣቸው ነበር....

ከራሴ ጋር ጊዜ ማሳለፍ ያስደስተኝ ነበር....ለብቻ መጠጣት....ለብቻ ወክ ማድረግ....ለብቻ ማሰብ....ከራሴ ጋር  ለመሆን ብዬ ጊዜ እነፍገው ነበር....አሁን ከሌሎች ጋር ለመሆን ብሎ ጊዜ ይነፍገኝ ጀመር....

ያኔ ስራዬን አሳምኖኝ ከመልቀቄ በፊት አምሽቼ ስገባ እራት ሰርቶ በረንዳ ላይ እንደ ቲያትረኛ እየተንጎራደደ የሚጠብቀኝ ሰው የለም.....አሁን ቤቱን ለቤርጎነት ብቻ ነው የሚጠቀመው....


የማጠፋው ጥፋት የልጅ ነበር....እሱ እንደአባት ይቅር ይለኝ ነበር....ለዛ እኮ ነው አባት ብዬ እጠራው የነበረው....አሁን አምስተኛ ልጄ ሆኖ አረፈው.....

ራሴን ከጣልኩበት በኃላ ተንሸራተተ...ለመንሸራተት ግን ጊዜ ጠብቋል....እግሬን አራት ልጆች ከጠፈረኝ በኃላ ፈቀቅ አለ....


ከረፈደ ነቃሁ....በመጨረሻም እስከዛሬ ያመንኩት በሙሉ ውሸት መሆኑን ደረስኩበት...".....ብላኝ ጨረሰች።


✍Shewit



https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka




✅️“አድናቆት ሙዚየም ውስጥ ባለው ውብ ሥዕል ፊት ለፊት ለአምስት ሰዓታት ያህል መቆም ነው፤ ነገር ግን ፍቅር ማለት ለአምስት ደቂቃ ያህል ቆሞ መሄድ ከዚያ እስከሚመሽ ጠብቆ ለመስረቅ መመለስ።”

Imagination_officially

✈️@Enmare1988
✈️@Enmare1988


💲💲
✅ጥራታቸውን የጠበቁ like human
hair & human hair to MMP
እናቀርባለን

መግዛትም ሆነ ማከፋፈል የምትፈልጉ📞📞 0945808500 ይደውሉ መስመር ያናግሩን



🌸Price ተመጣጣኝ ዋጋ


ለተጨማሪ  የቴሌግራም Channel

✈️https://t.me/marakihai
✈️https://t.me/marakihai


መስፈርቷ

ልጅ እያለሁ አብረን መርካቶ ያደግን ታየች የምትባል የልብ ጓደኛ ነበረችኝ። የሆነ ጊዜ ላይ ራጉኤል ጋር የነበረው የአባቷ ጨርቃ ጨርቅ ሱቅ በጣም ታዋቂ ሆነ። ከዛ ብዙም ሳይቆይ አለፈላቸውና መርካቶን ለቀው ኦልድ ኤርፖርት የሚባል ሰፈር ቤት ሰርተው ገቡ። እኔ እዛው መርካቶ ጭቃ ላይ እየተራገጥኩ አንበጣ ሳባርር ታየች ቢኪኒ የሚባል ጡት ማስያዣ ተገዝቶላት መዋኝት ተማረች። አልፎ አልፎ ቤታቸው ስጋበዝ ምቾቷ ይጋባል። የእማማ ራድያ የሽንት ቤት ፍሳሽ በግቢዬ የሚያልፈው እኔ፣ የእነ ታየች ግቢ ውስጥ ያለው ጋርደን ላይ ተንጋልዬ መጽሐፍ እያነበብኩ ስታይ፣ አይ ውበት። አመሻሽ ላይ ወደ መርኬ ለመመለስ ገብሬል ጋር ያለው ታክሲ ውስጥ ስገባ፣ መጽሐፌን ጭብጥ እድርጌ ይዤ ከስፊው ህዝብ ጋር ስገፋፋ፣ ጎበዝ ለካስ ምቾት ይተንናል
!።

ጥቂት አመታት አልፈው እኔ በ"ክልክል" አጥር ውስጥ፣ ፍቅርኛ መያዝ በማይፈቀድልኝ አስተዳደግ ውስጥ ስዳክር ታየች ሳምሶን የሚባል እንደሷ
በምቾት የሚንሳፈፍ የከንፈር ወዳጅ ያዘች። ህልምና መጽሐፍን የሰጠኝ እግዚያር ግን ደግ ነው። አሁን ደሞ ቸርነቱ በዝቶ የእኔ ከንፈር እንኳ በእውን ባይሳም የጓደኛዬ የታየች ከንፍር ሲሳም ሊያሳየኝ! እሱ ምን ይሳነዋል!

አንድ ቅዳሜ ታየች ደወልችልኝና ግራ የሚያጋባ ጥያቄ ሰነዘርች። "ቲጂዬ ዋና ትችያለሽ?".. ከሳምሶን ጋር ጊዮን ሆቴል ሊዋኙ ተቀጣጥረው ኖሮ አብሬያቸው እንድዝናና መጋበዝዋ ነበር። ምቾቷ አሳውሯት ነው እንጂ የት ነው እኔ መርካቶ ውስጥ ዋና የምማረው? ታደለች የምትቸረችረው የከሰል ሐይቅ ውስጥ? ወይስ ወ/ሮ የሻረግ ጠላ ቤት ያለው ማሰሮ ውስጥ? ታየች ፌዝ ተማረች። ታየች ዋና ተማረች። ከመርካቶ ቦይ በኮንጎ ጫማ ተንደርድራ በቢኪኒ ጊዮን ሆቴል የውሃ ገንዳ ውስጥ ተጠመቀች።

እሁድ ጠዋት የከንፈር ወዳጆቹን አጅቤ እነሱ ሊዋኙ እኔ ፎጣ ልጠብቅ ጊዮን ሆቴል ደረስን። ጁስና ኬክ ታዞልኝ እነሱ ውሃ ውስጥ ሲንሳፈፉ እኔ በእነሱ አለም ውስጥ ስንሳፈፍ፣ እንሱ በአራት ነጥብ የታጠሩ ደማቅ አርፍተ ነገሮች። እኔ ገና ያልተብራራው ተከፍቶ ያልተዘጋ ቅንፍ። ውሃ ሲረጫጩ ደስ ሲሉ። ይጎነታተላሉ። ኦ ቢኪኒዋ! አረንጓዴ ባለአበባ። ሳምሶን ከጀርባዋ ቆሞ እሷ ጸጉሯን ወደ ላይ ሰብስባ የላላውን የብኪኒዋን ገመድ እያሰረላት ሲጠጋት እሷ እየሳቀች ከወሲብ እንፋሎቱ ስትሸሽ። ሲያስቀኑ። በቀረብልኝ በጥቂት ደቂቃዎች ነው ኬኩንም ጁሱንም የሰለቀጥኩት። እንዲህ ያለው ምግብ በነጻ ሲገኝ ሰጪው ሃሳቡን ሳይቀይር ቶሎ ማውደሙ ከልምድ የመጣ ነው። የመርካቶ ቅደም ተከተሉ መጀመርያ ረሃብ ማስታገስ ከዛ ስለ ታየች የከንፈር ዕጣ ፈንታ ማሰላሰል።

በጨረፍታ እያየኋቸው ደስታቸው ተጋባብኝ። ያሽካካሉ። ፊታቸው ያብረቀርቃል። ሳምሶን ብዙ ሳምሶኖች ቢሆን፣ እኔን ጎትቶ ውሃ ውስጥ የሚያጠልቀኝ ሌላ ሳምሶን ከዚህኛው ላይ ተቆርሶ ቢመጣ። ሮዝ ቢኪኒ ቢኖረኝ። የቢኪኒዬ ገመድ ቢላላ፣ ሳምሶን ሊያስርልኝ ቢጠጋኝ፣ በወሲብ እንፋሎቱ እጠመቅ ነበር። መጣበቅ፣ መጠመቅ፣ አንድ መሆን። ታየች ለምን ሸሸች?

ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ያላሰብኩት ክስተት ተፈጠረ። ታየች እየተጣደፈች ከገንዳው ስትወጣ አየኋት። ፊቷ ላይ ብስጭቷ ይነበባል። ዞር ብዬ ሳምሶንን ቃኝሁት። ግራ ገብቶት ፈዞ ያያታል። አጠገቤ ስትደርስ በፍጥነት ፎጣዋን አንስታ ገላዋን እያደራረቀች "ቲጂ ቶሎ መሄድ አለብን ተነሽ" ብላኝ ሳትጠብቀኝ ወደ ልብስ መቀየሪያው ክፍል አመራች። "ይህ ቀዥቃዣ ወሲባም ምን አድርጓት ይሆን?" ብዬ እያሰላሰልኩ ተከተልኳት። ለባብሳ ወደ ታክሲ ስናመራ የሳምሶን አብሮን አለመሆን ግራ እንደገባኝ ስታውቅ "የኔ እና የእርሱ ነገር አብቅቷል" ብላ በረጅሙ ተነፈሰች።

እንዴ? ይህ የተመቸው ቦንቦሊኖ የመሰለ ልጅ፣ ለመላው የመርካቶ ኮረዳ ኬክና ጁስ የመግዛት አቅም ያለው ሳቂታው የሃብታም ልጅ፣ ቢኪኒዋን ወሲብ በተሞላበት ርህራሔ ያሰረላት ስሱ ሳምሶን ምን አድርጓት ይሆን? ልምድ ያካበቱ የሚመስሉ ከንፈሮች እንዲሁ በዋዛ ሊቀሩ?
"ምን እንዳደረገ ታውቂያለሽ?" አለች እየተብከነከነች። "የውሃው ገንዳ ውስጥ፣ እዛ የምንዋኝበት ገንዳ ውስጥ፣ አፍንጫውን ጨምቆ፣ በሃይል እንፍፍፍፍፍ ብሎ ንፍጡን ስቦ ካወጣ በኋላ እዛው ውሃ ውስጥ አይወረውረው መሰለሽ? ከዛ ደሞ እጁን መለቃለቁ! አይኑን ማየት አልፈልግም" ብላ አስረግጣ ነገረችኝ።

✅ ወንድሜ ሆይ፣ የታየች መስፈርት ግልጽ ነው። መርሴዲስ ቢኖርህ፣ ተጫዋች፣ አማላይ፣ ሳቂታ አፍቃሪ ብትሆን፣ ነገር ግን ንፍጥህን በየቦታው የምታዝረከርክ ከሆነ፣ ከታየች ጋር እድል አይኖርህም። የህዋ ተመርማሪ ብትሆን፣ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ብትሆን፣ ምን አለፋህ የሮም ከተማን የቆረቆርከው መሃንዲስ አንተ ብትሆን፣ ግን ህዝብ የሚዋኝበትን የውሃ ገንዳ በንፍጥህ የምትበክል ዝርክርክ ከሆንክ የታየች አጸያየፍ ከእግዚያር ፍጥረት ሁሉ የረቀቀ ነው።

ትግስት ሳሙኤል

9.3k 0 38 17 272

Репост из: Story's from my diary📝
ለምን??......ትጮሀለች..... ትቆጣለች..... እብድ ትሆናለች ብላ ስትጠብቅ ይሄንን ነበር የጠየኳት..... ... ምክንያቷን ብቻ ነበር ማወቅ የፈለኩት..... ይቅር እንድላት... እሷም እንደሌላው ሰው ናት ብዬ እንዳላስባት..... እንዳልጠላት... ለምን ብዬ ጠየኳት.... ለምትወደው.... የኔ በምትለው ሰው ....ላይ ያለን መብት ድርጊታቸው አይደለም ምክንያታቸው ነው.... ጥለውን ቢሄዱ.... ቢያረፍዱ.... ባይደውሉ.... ባይመጡ.... ያ አይደለም የኛ መብት....... የኛ መብት ምክንያታቸው ነው....... ያረፈዱበት ምክንያት.... የቀሩበት ምክንያት..... የከዱበት ምክንያት.... ያ ነው ለኛ ያላቸው ቦታ የሚገልፀው ምክንያታቸው ነው... ለሁሉም እንደዛ ነው የዓለም ትልቅ ጥፋት መግደል ቢሆን እንኳን የሚያስፈርድብክ መግደልክ ሳይሆን የገደልክበት ምክንያት ነው.... እራስን ለመከላከል ከሆነ በነፃም ልትለቀቅ ትችላለህ.... ለዛ ነው የጠየኳት ለሷ ያለኝን ቦታ እንዳላጣ.... ለራሴም ሌላ የልብ ስብራት እንዳልጨምር .....እንዳልጠላት.... እንዳልርቃት.... እንዳልተዋት ነው የጠየኳት....መብቴን ነው የጠየኳት....ለምን??..

✍️kalkidan


http://t.me/storyweaver36
http://t.me/storyweaver36
http://t.me/storyweaver36


Linkdin ከ 100 በላይ Follow ያላችሁ

በአሪፍ ዋጋ እየገዛን እንገኛለን

ከተከፈተ 2 አመት መሙላት አለበት

✔️ክፍያ : 🏦 🏦 🏦 🏦 🏦 🏦 🏦

ለመሸጥ ምትፈልጉ  inbox
👉

✈️@Kiya988
✈️@Kiya988


ከዕለታት በአንዱ ከዶ/ር መሠለ ተሬቻ ጋር ቡና እየጠጣን " What do you think of the future?" በሚል ስጠይቀው የመለሰልኝ ነገር ትዝ ይለኛል

🌟አንደቀልድ "አሁን ቻሌንጆችን እንደ ሶስተኛ ወገን ነው እያየህ ያለኸው፤ በጥቂት ዓመታት ውስጥ ቤትህ ድረስ ይመጣልኻል!" ነበር ያለኝ።

ከ7/8 ዓመት በፊት ከመገናኛ ተነስቶ እየተንፏቀቀ ወደ ጉርድሾላ መስመር የሚያመራ አካል ጉዳተኛ ነዳይ "ስንት ሰዓት ይደርስ ይኾን?" የሚለው ያሳስበኝ ነበር።

አሁን ለራሴ ነው የማስበው።

✅ከ አምስት ዓመት በፊት፤ ንባብን ባሕሉ ያደረገ፤ ያለፈውን ተምሮበት ፊቱን የሚሰራ ወጣት ይፈጠራልና ለዚያ ማዋጣት በየዕለቱ የሚያጓጓኝ  ነገር ነበር።

አሁን ራሴን ነው የማስበው።

✅ የዛሬ አራት ዓመት ሐኪምና መምህራን በዚህ የአገልግሎት ክፍያ ከዚህ በላይ ይሔንን ሕዝብ እንዴት ሊያገለግሉት ይችላሉ? ማነው ፈራጅ? በሚል ራሴን እፈትን ነበር።

አኹን ራሴን ነው የማስበው።

✅ ከሶስት ዓመት በፊት ሐረርጌ ጫፍ ያየኹትን "ተፈናቃይ" ጨቅላ ደጋግሜ አስበው ነበር። ዛሬ ከትውስታዬ ደብዝዟል።

አሁን ራሴን ነው የማስበው።

✅ ከኹለት ዓመት በፊት የዘመቻ ጥሪን ተከትሎ ከመደበኛ ሥራው ላይ ለጦርነት ወጥቶ፤ አይነስውር ሆኖ በመመለስ ወደስራው እንዳይመለስ ለዘመቻ ያበረረታተቱት አሰሪዎቹ "ላንተ ቦታ የለንም" ስላሉት ወጣት በየጊዜው እያሰብኩ እቆዛዝም ነበር።

አሁን ራሴን ነው የማስበው።

✅ ያለፉት ክረምቶች በመንገድ ዳር በቆሎ እሸት ጠብሳ የምትሸጥ ልጅ የያዘች እናት ወደቤቴ ሳመራ እያየኹ ዘወትር በቆሎ የሚግጥ ልጇ ሲያድግ እንዴት በቆሎን አምርሮ ይጠላ ይኾን? የሚል ሀሳብ ሰርክ ውል ይልብኝ ነበር።

አሁን ለራሴ ነው የማስበው።

✅✅ ራስ ወዳድ ሆኜ ነው ወይ?  እንደዛ አይደለም። አንተም በነዚህና ከዚህ ባለፉ ነገሮች ውስጥ ሐሳብህ ተመላልሶ ይኾናል።

ራስወዳድ ኾነህ አይደለም — Brother.

✅ ራሳችንን ሳናስብ ነበር ከባቢውን ስናጤን የነበረው። ጌዜ ደግሞ ግሩም መምህር ነው።  ነገሮችን ከረባብቶ በሰው ያስተዋልናቸውን ኹሉ ከእጃችን አዋለልን።

{እና አኹንስ? }

[  ] የጌቶች "ሜጋሎሜኒያ" ዲስኦርደር ያስገርምሀል ወይስ የራስህ Psychic Disintegration ያሳስብኃል?
[  ] የጃዋር መሐመድ አለመፀፀት ያንገበግብኃል ወይስ ራስህን ታያለህ?
[  ] የፋሲለደስ ኖራ ቀለም ያበሳጭኃል ወይስ ቀለም ዓልባ ሕይወትህ ያሳስብሀል?
ሌላም። ሌላም።

✅ ለራሱ ያልበቃና ፓወር ፖዘዝ ያላደረገ ግለሰብ ዙሪያው ላይ በሚሆነው ነገር አንዳች ፈቃድ የለውም።

የግላቸውን ጣጣና ጦስ ያረቁ የተወጡ፤ በተስፋ ዓልባ ምድር ሪዚሊየንት ሆነው መትረፍ የቻሉ ግለሰቦች ናቸው ሐገር የሚሰሩት።

✅ ደንቆሮ የማይበልጠው፤ ጅል የማያሞኘው፤ አላፊ አግዳሚ ረግጦ የማይሰብረው ሰብዕና ካልገነባህ በቀር ተፈጥሮ እንድትሰለቅጥህ የሚያስገድድ ማህበራዊ ቼይን ውስጥ ነህና ትጠፋለህ።

{እና…}

ምንም በማያሸነጋግል ሁኔታ You are in a hopeless land.

✅እዚህ ተስፋ አልባ ምድር ውስጥ "ላለመጥፋት ምን ማድረግ አለብኝ?" ነው ዋናው ቁም ነገር። ሀቂቃ ልንገርህ ፈጣሪም ፍጡርም ማንም አያድንህም። ብቸኛ መዳኛህ ራስህ ነህ።

በዚህ ኹሉ ውስጥ— አሁን — ራስህን አስብ። በማህበራዊ ሥርዓት ሠንሠለቱ ከላይ ለመቆየት ጣር።

🌟"Get gold, humanely if possible — but at all hazards, get gold." እንዲል የስፓኙ ጄንራል። 😊

9.4k 0 41 15 96
Показано 20 последних публикаций.