መቋሚያ
ብዙውን ከእንጨት የሚዘጋጅ እንደ በትር ዘለግ ያለ ከወደ ጫፉ መስቀል ቅርጽ ያለው ነው፤ በአሁኑ ጊዜ በአብዛኛው የ "ፐ" ቅርጽ ያለው አሊያም ድቡልቡል የሆነ ነው፤ ከወደ ጫፉ የሚደረገው ነገር የብር ፣የነሐስ ፣የወርቅ፣ የብረት፣ የቀንድ ና የእንጨት ሊሆን ይችላል
አገልግሎቱም
መደገፊያ ፣ መሞርኮዧ ና መዘመሚያ ሲሆን ይህም ከከበሮ እና ጸናጽል ጋር እንዲሁም ብቻውን ከማህሌት ላይ በዝማሜና በሽብሸባ ያገለግላል
ምስጢሩ
መቋሚያ የአዳም ተስፋና ከእመቤታችን ተወልዶ በዕጸ መስቀል ላይ የተሰቀለው የጌታችን የአምላካችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው።
👉 አንድም መቋሚያ ያዕቆብ ትምህርተ መስቀል ያለበት በትር በፊቱ እያቆመ ይሰግድና ይጸልይ የነበረበት ምሳሌ ነው
👉ካህናት መቋሚያን በትከሻቸው አድርገው ወዲህ ወዲያ ማለታቸው አይሁድ በዕለተ አርብ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ መመውሰዳቸው
ዝማሜ ሚመሰለው በህማማተ ክርስቶስ ነው። መቋሚያው በመስቀል ይመሰላል።ካህናቱ መቋሚያቸው ከዜማ ጋር አስማምተው በዝማሜ ወቅት መቋሚያውን ወደ ግራ ወደ ቀኝ ማድረጋቸው አይሁድ ኢየሱስን አንዴ ወደግራ አንዴ ወደቀኝ ከነመስቀሉ ማንገላታታቸውን ለማስታወስ ነው። ከዛ ወደታች መሬቱን መምታታቸው ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ ግርፋቱ ሲበዛበት መሬት ላይ መውደቁን ያሳያል።
ጽናጽል
ከብር ከነሐስ-ከሌላም ብረት የሚሰራ፤ እንዲሿሿ ከብረት ቅጠል የሚደረግበት ሲሆን አገልግሎቱም ለእግዚአብሔር ክብር ይዘመርበታል። ጽናጽል ከከበሮ ጋር አብር የሚሄድ የዜማ መሳሪያ ነው
የብረት ቅጠሎቹ ሲያንሱ 5 ሲበዙ 7 ይሆናሉ። 5 ሲሆን አምስቱ አዕማደ ሚስጢር 7 ሲሆን በሰባቱ ሰማያት ይመሰላል።
👉2 የብረት ዘንጎች(የብረት ቅጠሎቹን የሚይዙት) ላይ ከታችኛው ላይ 2 የብረት ቅጠሎች የሚኖሩ ሲሆን ይህም ጌታችን ልደቶች ማለትም ቅድመ ዓለም ያለ እናት ከአብ ፤ ድህረ ዓለም ደግሞ ያለ አባት ከእመቤታችን መወለዱ ምሳሌ ነው
👉 የብረት ቅጠሎቹ 3 መሆን የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌ ነው
👉ድምጹ ያማረና መልካም መሆኑ በመላእክት ዜማ ይመሰላል (ሰብሕዎ በጽናጽል ዘሠናይ ቃሉ እንዲል መዝሙረኛው ዳዊት በመዝሙር 150)
👉ጽናጽል ወዲህ ወዲያ ማለቱ ጌታችን የመንገላታቱ ምሳሌ ነው
ከበሮ
ከእንጨት ተዘጋጅቶ በጠፍርና በቆዳ የሚለጎም የዜማ መሳሪያ ነው።
ለክብረ በዓል ለበዓል ለበዓለ ንግሥ ዕለት ለእግዚአብሔር ክብር የሚመታ የሚመዘመርበት ነው
በከበሮ ወበመዝሙር ይዜምሩ ሎቱ እንዲል መዝሙረኛው ዳዊት በመዝሙር 149
ምስጢሩ-
አፉ ሁለት ነው፤ ጠባብ እና ሰፊ
ሰፊው- ቁመት ደረት ምሉዕ በኩለሄ/እግዚአብሔር በሁሉ ሙሉ መሆኑን ሲሆን
ጠባቡ- ደግሞ ወልድ በአጭር ቁመት መወሰኑን የሚያመለክት የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው
እንጨቱ ከቆዳ የተለጎመበት ጠፍር- ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አይሁድ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ስልሳ ስድስት ጊዜ የገረፉበት የግርፋቱ (የገላው ሰንበር) ምሳሌ ነው
ከበሮ የሚለብሰው ሱቲ ጌታችን የለበሰው ቀይ ግምጃ ምሳሌ ነው
የከበሮ አመታት ምስጢር
መጀመሪያ ከበሮ ተቀምጦ ቀስ እየተባለ ነው የሚመታው።
👉በመሬት መመታቱ ጌታችን አይሁድ በመሬት እየጎተቱ መምታታቸውን
👉በግራ እና በቀኝ ሲመታ ከቀኝ ሲመታ ወደ ግራ ከግራ ሲመታ ወደ ቀኝ ማዘንበሉን ለማስታወስ ነው
👉ከበሮ በትከሻ ተደርጎ ሲመታ ከወደቀበት እንደመቱት ፤በፍጥነት ሲመታ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሊሰቀል ሲቃረብ በፍጥነት መምታታቸውን ያስታውሰናል
የማሕሌት ተወዛዋዦች
ዛሬ ለወጉ ማሕሌት አንቀርም ፣ ቸብቸቦ ይጀመራል ፣ ወጣቶች ከበሮውን ለማንሳት ሪከርድ በሚያሻሽል ፍጥነት የከበሮውን ገመድ ከጀርባቸው ያዋሕዱታል (እንዲያው ወጣቶች ስንል በእድሜ ማለታችን አይደለም ቆብ የደፉ መስቀል የጨበጡ ቀጣይ በምናየው መልኩ የሚሳተፉትንም የሚገልጽ ቃል ነው እንጅ ) : አፍታም ሳይቆይ እንደ አሎሎ ወርዋሪ መሽከርከር ይጀመራል : አንድ እጅ ተዘርግቶ እስክስታው ይቀልጣል: ሁለት እግር ከፍ እያለ መዝለል ይጀመራል : አሁን በአንደበት የሚነገረው ስብሐተ እግዚአብሔር ነው መሬት ላይ ደግሞ ኅብረ ብሔራዊ ጭፈራ ሁኗል : ነፍስ ምን እየተካሄደ እንዳለ ዘንግታለች : ስጋ ግን እየተንቀጠቀጠ ነው : የስሜት እሳት ተቀጣጥሏል : እሽሽሽሽሽሽ የሚል ማጀቢያ መሆኑ ነው ከአንደበት አትጠፋም : የሙቀቱ መጠን ከቁጥጥር እየወጣ ነው : ወደ ሴቶች ጉዞ ይጀመራል : አሁን ሴቶች በቅርበት እየተመለከቱ ነው ከበሮው ላይ ብትሩ ይበረታል : የዝላዩ ከፍታ ይጨምራል : ጿጿጿጿጿ የሚል የጽናጽል ድምጽ የሚያሰማ ቢኖርም ፈገግ ተብሎ ታልፎ ጭፈራው ይደራል : ሊቃውንቱ ቢናገሩም የተጠሉ ይሆናሉ : ነፍስ ከተኛች ቆይታለች ከዱካካዋ ልትነቃ አልቻለችም : ከጎን ከበሮ የሚመታው ጓደኛ በመቺው ትዕዛዝ አመታቱን እየቀረጸ ነው : Tik Tok ቀጣዩ የቪዲኦው መሰራጫ መድረክ ነው : የታይታ ክርስትና ! እንደ ፈሪሳውያን ሰው እንዲያይ ብሎ መዘመር ! ተቃራኒ ጾታ እያዩ መስፈንጠር ! በከበሮ ትዳር አይፈለግም ! መዝለል ፣ መሽከርከር ፣ መስፈንጠር፣ መንቀጥቀጥ ፣ እሽሽሽሽሽ ማለት ፣ ወደ ተቃራኒ ጾታ አንጋጦ መዞር ይቁሙ !
ሁለት እጅ ስላለህ እና መምታት ስለቻልክ ብቻ ከበሮ አትሸከም ምስጢሩን ተረዳ ያኔ ሲገባህ ዕንባህ ከዐይንህ ያለማቋረጥ ጉንጮችህን መወረጃ አድርጎ ሲጎርፍ ይታወቅሀል : ያኔ ልብህ እንጅ እግርህ አይዘልም : ያኔ የምትንቀጠቀጠው እግዚአብሔርን በመፍራት ይሆናል: ያኔ ስትዘል አፍአዊ ላብ ሳይሆን ሕሊናህ ይሆናል በተመስጦ የሚያልበው : ያኔ እንደ መላእክት የሰማይ የመቅደሱ በር እስኪከፈት እንዲዘምሩ አንተም የልቦናህ በር ተከፍቶ ለምስጋና ትታትራለህ ። አየኋት : አወቅኳት : ወደድኳት ብሎ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ የመላዕክትን ዝማሬ ሰምቶ መጦ ባቀናት ቤተክርስቲያን ምድራዊ ተወዛዋዦች ገብተናልና ወደ ልቦናችን እንመለስ ።
በወንዶች ብቻ የሚቆም ግብር አይደለም በአንስቶችም ተመሳሳይ ፍሬ አፍርቶ ተንዠርቅቆ እናገኘዋለን : በሰንበት ትምህርት ቤት እንዲሁ በአደባባይ በዓላት ቁጥራቸው ትቂት ያልሆኑ በከበሮ ላይ መከራ አጽንተው በመከራ ድር ተተብትበው ይኖራሉ : አንቲ ተቃራኒ ጾታሽ እንዲያይሽ ካልሆነ ምን ያሽከረክርሻል ? ምን ያዘልልሻል ? ወደ እነማን ፊትሽን ዙረሽስ ትመቻለሽ ? ወደፊት ወደ ኋላ ስትይ የክርስቶስን መገፋት ታስቢያለሽ ወይስ ወደፊት ሄደሽ ልብሽ የወደደውን ትፈቅጃለሽ ? ከንቱ ውዳሴን ሽተሽ በሰፈሩ የከበሮ አመታትሽ እንዲወራ ከሆነ እኅቴ ሆይ የገሀነም ደጃፍ ላይ ነሽና ሳትገቢ ተመለሽ! በአደባባይ ምድርን የሚያበራ እሳት ከማቀጣጠል በሕሊና መቅረዝ ትቂት መንፈሳዊ ማኅቶት ማብራት ይሻላል ! በእውነት እናስተውል ! እነ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት እኮ በዝማሬያቸው ሕሙም ይፈውሱ ነበር በእኛስ? ዘመርን ብለን እራሳችን ሕሙም ሆነን እንመለሳለን ! ወደ እነእንተና ለይቶልን በኅብረ ብሔራዊ ጭፈራ እግዚአብሔር ቢመለክ ምን ችግር አለው ብለን የኅብረት ዘፋኞች ከመሆናችን በፊት ለብው ! አምላከ ያሬድ ወዳዊት ወእዝራ የቀናውን መንፈስ ያድለን ! የቅዱሳኑ ዝማሬ ወላዲተ ቃል ድንግል ማርያም በረድኤት አትለየን
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
ብዙውን ከእንጨት የሚዘጋጅ እንደ በትር ዘለግ ያለ ከወደ ጫፉ መስቀል ቅርጽ ያለው ነው፤ በአሁኑ ጊዜ በአብዛኛው የ "ፐ" ቅርጽ ያለው አሊያም ድቡልቡል የሆነ ነው፤ ከወደ ጫፉ የሚደረገው ነገር የብር ፣የነሐስ ፣የወርቅ፣ የብረት፣ የቀንድ ና የእንጨት ሊሆን ይችላል
አገልግሎቱም
መደገፊያ ፣ መሞርኮዧ ና መዘመሚያ ሲሆን ይህም ከከበሮ እና ጸናጽል ጋር እንዲሁም ብቻውን ከማህሌት ላይ በዝማሜና በሽብሸባ ያገለግላል
ምስጢሩ
መቋሚያ የአዳም ተስፋና ከእመቤታችን ተወልዶ በዕጸ መስቀል ላይ የተሰቀለው የጌታችን የአምላካችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው።
👉 አንድም መቋሚያ ያዕቆብ ትምህርተ መስቀል ያለበት በትር በፊቱ እያቆመ ይሰግድና ይጸልይ የነበረበት ምሳሌ ነው
👉ካህናት መቋሚያን በትከሻቸው አድርገው ወዲህ ወዲያ ማለታቸው አይሁድ በዕለተ አርብ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ መመውሰዳቸው
ዝማሜ ሚመሰለው በህማማተ ክርስቶስ ነው። መቋሚያው በመስቀል ይመሰላል።ካህናቱ መቋሚያቸው ከዜማ ጋር አስማምተው በዝማሜ ወቅት መቋሚያውን ወደ ግራ ወደ ቀኝ ማድረጋቸው አይሁድ ኢየሱስን አንዴ ወደግራ አንዴ ወደቀኝ ከነመስቀሉ ማንገላታታቸውን ለማስታወስ ነው። ከዛ ወደታች መሬቱን መምታታቸው ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ ግርፋቱ ሲበዛበት መሬት ላይ መውደቁን ያሳያል።
ጽናጽል
ከብር ከነሐስ-ከሌላም ብረት የሚሰራ፤ እንዲሿሿ ከብረት ቅጠል የሚደረግበት ሲሆን አገልግሎቱም ለእግዚአብሔር ክብር ይዘመርበታል። ጽናጽል ከከበሮ ጋር አብር የሚሄድ የዜማ መሳሪያ ነው
የብረት ቅጠሎቹ ሲያንሱ 5 ሲበዙ 7 ይሆናሉ። 5 ሲሆን አምስቱ አዕማደ ሚስጢር 7 ሲሆን በሰባቱ ሰማያት ይመሰላል።
👉2 የብረት ዘንጎች(የብረት ቅጠሎቹን የሚይዙት) ላይ ከታችኛው ላይ 2 የብረት ቅጠሎች የሚኖሩ ሲሆን ይህም ጌታችን ልደቶች ማለትም ቅድመ ዓለም ያለ እናት ከአብ ፤ ድህረ ዓለም ደግሞ ያለ አባት ከእመቤታችን መወለዱ ምሳሌ ነው
👉 የብረት ቅጠሎቹ 3 መሆን የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌ ነው
👉ድምጹ ያማረና መልካም መሆኑ በመላእክት ዜማ ይመሰላል (ሰብሕዎ በጽናጽል ዘሠናይ ቃሉ እንዲል መዝሙረኛው ዳዊት በመዝሙር 150)
👉ጽናጽል ወዲህ ወዲያ ማለቱ ጌታችን የመንገላታቱ ምሳሌ ነው
ከበሮ
ከእንጨት ተዘጋጅቶ በጠፍርና በቆዳ የሚለጎም የዜማ መሳሪያ ነው።
ለክብረ በዓል ለበዓል ለበዓለ ንግሥ ዕለት ለእግዚአብሔር ክብር የሚመታ የሚመዘመርበት ነው
በከበሮ ወበመዝሙር ይዜምሩ ሎቱ እንዲል መዝሙረኛው ዳዊት በመዝሙር 149
ምስጢሩ-
አፉ ሁለት ነው፤ ጠባብ እና ሰፊ
ሰፊው- ቁመት ደረት ምሉዕ በኩለሄ/እግዚአብሔር በሁሉ ሙሉ መሆኑን ሲሆን
ጠባቡ- ደግሞ ወልድ በአጭር ቁመት መወሰኑን የሚያመለክት የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው
እንጨቱ ከቆዳ የተለጎመበት ጠፍር- ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አይሁድ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ስልሳ ስድስት ጊዜ የገረፉበት የግርፋቱ (የገላው ሰንበር) ምሳሌ ነው
ከበሮ የሚለብሰው ሱቲ ጌታችን የለበሰው ቀይ ግምጃ ምሳሌ ነው
የከበሮ አመታት ምስጢር
መጀመሪያ ከበሮ ተቀምጦ ቀስ እየተባለ ነው የሚመታው።
👉በመሬት መመታቱ ጌታችን አይሁድ በመሬት እየጎተቱ መምታታቸውን
👉በግራ እና በቀኝ ሲመታ ከቀኝ ሲመታ ወደ ግራ ከግራ ሲመታ ወደ ቀኝ ማዘንበሉን ለማስታወስ ነው
👉ከበሮ በትከሻ ተደርጎ ሲመታ ከወደቀበት እንደመቱት ፤በፍጥነት ሲመታ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሊሰቀል ሲቃረብ በፍጥነት መምታታቸውን ያስታውሰናል
የማሕሌት ተወዛዋዦች
ዛሬ ለወጉ ማሕሌት አንቀርም ፣ ቸብቸቦ ይጀመራል ፣ ወጣቶች ከበሮውን ለማንሳት ሪከርድ በሚያሻሽል ፍጥነት የከበሮውን ገመድ ከጀርባቸው ያዋሕዱታል (እንዲያው ወጣቶች ስንል በእድሜ ማለታችን አይደለም ቆብ የደፉ መስቀል የጨበጡ ቀጣይ በምናየው መልኩ የሚሳተፉትንም የሚገልጽ ቃል ነው እንጅ ) : አፍታም ሳይቆይ እንደ አሎሎ ወርዋሪ መሽከርከር ይጀመራል : አንድ እጅ ተዘርግቶ እስክስታው ይቀልጣል: ሁለት እግር ከፍ እያለ መዝለል ይጀመራል : አሁን በአንደበት የሚነገረው ስብሐተ እግዚአብሔር ነው መሬት ላይ ደግሞ ኅብረ ብሔራዊ ጭፈራ ሁኗል : ነፍስ ምን እየተካሄደ እንዳለ ዘንግታለች : ስጋ ግን እየተንቀጠቀጠ ነው : የስሜት እሳት ተቀጣጥሏል : እሽሽሽሽሽሽ የሚል ማጀቢያ መሆኑ ነው ከአንደበት አትጠፋም : የሙቀቱ መጠን ከቁጥጥር እየወጣ ነው : ወደ ሴቶች ጉዞ ይጀመራል : አሁን ሴቶች በቅርበት እየተመለከቱ ነው ከበሮው ላይ ብትሩ ይበረታል : የዝላዩ ከፍታ ይጨምራል : ጿጿጿጿጿ የሚል የጽናጽል ድምጽ የሚያሰማ ቢኖርም ፈገግ ተብሎ ታልፎ ጭፈራው ይደራል : ሊቃውንቱ ቢናገሩም የተጠሉ ይሆናሉ : ነፍስ ከተኛች ቆይታለች ከዱካካዋ ልትነቃ አልቻለችም : ከጎን ከበሮ የሚመታው ጓደኛ በመቺው ትዕዛዝ አመታቱን እየቀረጸ ነው : Tik Tok ቀጣዩ የቪዲኦው መሰራጫ መድረክ ነው : የታይታ ክርስትና ! እንደ ፈሪሳውያን ሰው እንዲያይ ብሎ መዘመር ! ተቃራኒ ጾታ እያዩ መስፈንጠር ! በከበሮ ትዳር አይፈለግም ! መዝለል ፣ መሽከርከር ፣ መስፈንጠር፣ መንቀጥቀጥ ፣ እሽሽሽሽሽ ማለት ፣ ወደ ተቃራኒ ጾታ አንጋጦ መዞር ይቁሙ !
ሁለት እጅ ስላለህ እና መምታት ስለቻልክ ብቻ ከበሮ አትሸከም ምስጢሩን ተረዳ ያኔ ሲገባህ ዕንባህ ከዐይንህ ያለማቋረጥ ጉንጮችህን መወረጃ አድርጎ ሲጎርፍ ይታወቅሀል : ያኔ ልብህ እንጅ እግርህ አይዘልም : ያኔ የምትንቀጠቀጠው እግዚአብሔርን በመፍራት ይሆናል: ያኔ ስትዘል አፍአዊ ላብ ሳይሆን ሕሊናህ ይሆናል በተመስጦ የሚያልበው : ያኔ እንደ መላእክት የሰማይ የመቅደሱ በር እስኪከፈት እንዲዘምሩ አንተም የልቦናህ በር ተከፍቶ ለምስጋና ትታትራለህ ። አየኋት : አወቅኳት : ወደድኳት ብሎ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ የመላዕክትን ዝማሬ ሰምቶ መጦ ባቀናት ቤተክርስቲያን ምድራዊ ተወዛዋዦች ገብተናልና ወደ ልቦናችን እንመለስ ።
በወንዶች ብቻ የሚቆም ግብር አይደለም በአንስቶችም ተመሳሳይ ፍሬ አፍርቶ ተንዠርቅቆ እናገኘዋለን : በሰንበት ትምህርት ቤት እንዲሁ በአደባባይ በዓላት ቁጥራቸው ትቂት ያልሆኑ በከበሮ ላይ መከራ አጽንተው በመከራ ድር ተተብትበው ይኖራሉ : አንቲ ተቃራኒ ጾታሽ እንዲያይሽ ካልሆነ ምን ያሽከረክርሻል ? ምን ያዘልልሻል ? ወደ እነማን ፊትሽን ዙረሽስ ትመቻለሽ ? ወደፊት ወደ ኋላ ስትይ የክርስቶስን መገፋት ታስቢያለሽ ወይስ ወደፊት ሄደሽ ልብሽ የወደደውን ትፈቅጃለሽ ? ከንቱ ውዳሴን ሽተሽ በሰፈሩ የከበሮ አመታትሽ እንዲወራ ከሆነ እኅቴ ሆይ የገሀነም ደጃፍ ላይ ነሽና ሳትገቢ ተመለሽ! በአደባባይ ምድርን የሚያበራ እሳት ከማቀጣጠል በሕሊና መቅረዝ ትቂት መንፈሳዊ ማኅቶት ማብራት ይሻላል ! በእውነት እናስተውል ! እነ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት እኮ በዝማሬያቸው ሕሙም ይፈውሱ ነበር በእኛስ? ዘመርን ብለን እራሳችን ሕሙም ሆነን እንመለሳለን ! ወደ እነእንተና ለይቶልን በኅብረ ብሔራዊ ጭፈራ እግዚአብሔር ቢመለክ ምን ችግር አለው ብለን የኅብረት ዘፋኞች ከመሆናችን በፊት ለብው ! አምላከ ያሬድ ወዳዊት ወእዝራ የቀናውን መንፈስ ያድለን ! የቅዱሳኑ ዝማሬ ወላዲተ ቃል ድንግል ማርያም በረድኤት አትለየን
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot