በግልጽ በማይታይ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ሲገለገሉ በነበሩ ከ1ሺህ በላይ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን ፖሊስ አስታወቀ‼️
በተደመሰሰ፣ በታጠፈ፣ በተፋፋቀ፣ በደበዘዘ እና በማይታይ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ቁጥር ሲገለገሉ በተገኙ 1 ሺህ 587 ደንብ ተላላፊ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
አግባብነት ካለው አካል የተሰጠን የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ቁጥር በሚታይና ግልፅ በሆነ መልኩ በተሽከርካሪው አካል ላይ መለጠፍ እንደሚገባ በአዋጅ መደንገጉን የገለጸው ፖሊስ፤ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል አሽከርካሪዎች ለዕይታ ግልፅ ያልሆነ ሰሌዳን በመጠቀም ደምብ ሲተላለፉ ቆይተዋል ብሏል፡፡
አንዳንዶቹም ደምብ መተላለፉን እንደ ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ወንጀል ሲፈፅሙ የተገኙ ተይዘው ምርመራ እየተጠራባቸው መሆኑንም ፖሊስ ባወጣው መረጃ አስታውቋል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ከየካቲት 16 እስከ የካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም በሁሉም ክፍለ ከተሞች በቀንንና በማታ ባደረገው ቁጥጥር የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ቁጥርን ያለ አግባብ ሲገለገሉ በተገኙ 1 ሺህ 587 ደንብ ተላላፊዎች ላይ በትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብ መሰረት እርምጃ መውሰዱን ነው የገለጸው፡፡
ፖሊስ በደንብ ተላላፊዎች ላይ እያደረገ ያለውን ቁጥጥር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጾ፤ የተሽከርካሪ ባለ ንብረቶችም ሆኑ አሽከርካሪዎች በተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ቁጥር አጠቃቀም ዙሪያ ተገቢውን ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባም አሳስቧል፡፡
@Esat_tv1
@Esat_tv1
በተደመሰሰ፣ በታጠፈ፣ በተፋፋቀ፣ በደበዘዘ እና በማይታይ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ቁጥር ሲገለገሉ በተገኙ 1 ሺህ 587 ደንብ ተላላፊ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
አግባብነት ካለው አካል የተሰጠን የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ቁጥር በሚታይና ግልፅ በሆነ መልኩ በተሽከርካሪው አካል ላይ መለጠፍ እንደሚገባ በአዋጅ መደንገጉን የገለጸው ፖሊስ፤ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል አሽከርካሪዎች ለዕይታ ግልፅ ያልሆነ ሰሌዳን በመጠቀም ደምብ ሲተላለፉ ቆይተዋል ብሏል፡፡
አንዳንዶቹም ደምብ መተላለፉን እንደ ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ወንጀል ሲፈፅሙ የተገኙ ተይዘው ምርመራ እየተጠራባቸው መሆኑንም ፖሊስ ባወጣው መረጃ አስታውቋል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ከየካቲት 16 እስከ የካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም በሁሉም ክፍለ ከተሞች በቀንንና በማታ ባደረገው ቁጥጥር የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ቁጥርን ያለ አግባብ ሲገለገሉ በተገኙ 1 ሺህ 587 ደንብ ተላላፊዎች ላይ በትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብ መሰረት እርምጃ መውሰዱን ነው የገለጸው፡፡
ፖሊስ በደንብ ተላላፊዎች ላይ እያደረገ ያለውን ቁጥጥር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጾ፤ የተሽከርካሪ ባለ ንብረቶችም ሆኑ አሽከርካሪዎች በተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ቁጥር አጠቃቀም ዙሪያ ተገቢውን ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባም አሳስቧል፡፡
@Esat_tv1
@Esat_tv1