በትግራይ ክልል “አስቸኳይ ምርጫ” እንዲደረግ አሊያም “የመማክርት ምክር ቤት” እንዲቋቋም ኢህአፓ ጠየቀ
በትግራይ ክልል “አስቸኳይ ምርጫ” እንዲደረግ የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፖርቲ (ኢህአፓ) ጠየቀ። የትግራይ ህዝብ “በመረጣቸው እንደራሴዎች እስኪወከል ድረስ “፤ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ሁሉንም “ህጋዊ” የፖለቲካ ፓርቲዎች ያካተተ “የመማክርት ምክር ቤት” እንዲቋቋም ፓርቲው ምክረ ሃሳብ አቅርቧል።
ፓርቲው ይህን ያስታወቀው ዛሬ ረቡዕ ጥር 14፤ 2017 አዲስ አበባ ካዛንቺስ አካባቢ በሚገኘው ዋና ጽህፈት ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው። በኢህአፓ የትግራይ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የተጠራው የዛሬው መግለጫ፤ በክልሉ በቅርቡ በተከሰቱ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር።
የትግራይ ክልል በፌደራል ምክር ቤቶች ያለው የውክልና ጉዳይም በዛሬው መግለጫ ላይ ተነስቷል። ከጥቅምት 2013 ዓ.ም. ጀምሮ ለሁለት ዓመት የቆየው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ከመካሄዱ አስቀድሞ ካሉት ወራት ወዲህ፤ ክልሉ በህዝብ ተወካዮችም እና በፌዴሬሽን ምክር ቤቶች ያለው ውክልና ተቋርጧል።
“የትግራይ ህዝብ እንደ ፌዴሬሽን አባልነቱ በኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 38 ወንበሮች ያሉት ቢሆንም፤ ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ተወክሎ አያውቅም” ሲል ኢህአፓ በዛሬው መግለጫው አስታውሷል። ፓርቲው በዚሁ መግለጫው “ባለፉት አራት ዓመታት በፓርላማው እና በፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የሚተላለፉ ውሳኔዎች፤ የትግራይ ህዝብን ፍላጎቶች ያካተቱ አልነበሩም” ብሏል።
🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/14869/
🔴 የኢህአፓን መግለጫ እና ለጥያቄዎች የተሰጡትን ምላሾች በቪዲዮ ለመመልከት ➡️ https://youtu.be/3gxeQtoadn4
@EthiopiaInsiderNews
በትግራይ ክልል “አስቸኳይ ምርጫ” እንዲደረግ የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፖርቲ (ኢህአፓ) ጠየቀ። የትግራይ ህዝብ “በመረጣቸው እንደራሴዎች እስኪወከል ድረስ “፤ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ሁሉንም “ህጋዊ” የፖለቲካ ፓርቲዎች ያካተተ “የመማክርት ምክር ቤት” እንዲቋቋም ፓርቲው ምክረ ሃሳብ አቅርቧል።
ፓርቲው ይህን ያስታወቀው ዛሬ ረቡዕ ጥር 14፤ 2017 አዲስ አበባ ካዛንቺስ አካባቢ በሚገኘው ዋና ጽህፈት ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው። በኢህአፓ የትግራይ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የተጠራው የዛሬው መግለጫ፤ በክልሉ በቅርቡ በተከሰቱ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር።
የትግራይ ክልል በፌደራል ምክር ቤቶች ያለው የውክልና ጉዳይም በዛሬው መግለጫ ላይ ተነስቷል። ከጥቅምት 2013 ዓ.ም. ጀምሮ ለሁለት ዓመት የቆየው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ከመካሄዱ አስቀድሞ ካሉት ወራት ወዲህ፤ ክልሉ በህዝብ ተወካዮችም እና በፌዴሬሽን ምክር ቤቶች ያለው ውክልና ተቋርጧል።
“የትግራይ ህዝብ እንደ ፌዴሬሽን አባልነቱ በኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 38 ወንበሮች ያሉት ቢሆንም፤ ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ተወክሎ አያውቅም” ሲል ኢህአፓ በዛሬው መግለጫው አስታውሷል። ፓርቲው በዚሁ መግለጫው “ባለፉት አራት ዓመታት በፓርላማው እና በፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የሚተላለፉ ውሳኔዎች፤ የትግራይ ህዝብን ፍላጎቶች ያካተቱ አልነበሩም” ብሏል።
🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/14869/
🔴 የኢህአፓን መግለጫ እና ለጥያቄዎች የተሰጡትን ምላሾች በቪዲዮ ለመመልከት ➡️ https://youtu.be/3gxeQtoadn4
@EthiopiaInsiderNews