መኢአድ ፓርቲውን በፕሬዝዳንት እና በምክትል ፕሬዝዳንትነት የሚመሩ አዲስ አመራሮችን መረጠ
የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ትላንት እሁድ ጥር 25፤ 2017 ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ፤ የፓርቲው ተቀዳሚ ፕሬዝዳንት የነበሩትን አቶ አብርሃም ጌጡን ፓርቲውን እንዲመሩ መረጠ። ፓርቲው በዚሁ ጉባኤው፤ በመተዳደሪያ ደንቡ ላይ ማሻሻያ አድርጓል።
በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነምግባር አዋጅ መሰረት በምርጫ ቦርድ ተመዝግበው ህጋዊነት ያገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች፤ ቢያንስ በሶስት ዓመት አንድ ጊዜ ጠቅላላ ጉባኤ ማካሄድ አለባቸው።
ሀገር አቀፍ ፓርቲ የሆነው መኢአድ፤ በትላንትናው ዕለት ያካሄደው መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ለ10ኛ ጊዜ የተካሄደ ነው።
በአዲስ አበባ ቴዎድሮስ አደባባይ አካባቢ በሚገኘው የመኢአድ ዋና ጽህፈት ቤት በተካሄደው በትላንትናው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ 550 ገደማ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።
በዚሁ ጉባኤ ላይ በተደረገው የአመራር ምርጫ፤ መኢአድን ስድስት ለሚጠጉ ዓመታት ሲመሩ በቆዩት አቶ ማሙሸት አማረ ምትክ አቶ አብርሃም ጌጡ የፓርቲው ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል።
አቶ አብርሃም በአቶ ማሙሸት የኃላፊነት ዘመን የፓርቲው ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው አገልግለዋል። አዲሱ የፓርቲው ፕሬዝዳንት ይዘው የቆዩትን የተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንትነት ቦታ በጉባኤው ምርጫ የተረከቡት አቶ ሰማኝ አብርሃም ናቸው።
🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/14987/
@EthiopiaInsiderNews
የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ትላንት እሁድ ጥር 25፤ 2017 ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ፤ የፓርቲው ተቀዳሚ ፕሬዝዳንት የነበሩትን አቶ አብርሃም ጌጡን ፓርቲውን እንዲመሩ መረጠ። ፓርቲው በዚሁ ጉባኤው፤ በመተዳደሪያ ደንቡ ላይ ማሻሻያ አድርጓል።
በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነምግባር አዋጅ መሰረት በምርጫ ቦርድ ተመዝግበው ህጋዊነት ያገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች፤ ቢያንስ በሶስት ዓመት አንድ ጊዜ ጠቅላላ ጉባኤ ማካሄድ አለባቸው።
ሀገር አቀፍ ፓርቲ የሆነው መኢአድ፤ በትላንትናው ዕለት ያካሄደው መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ለ10ኛ ጊዜ የተካሄደ ነው።
በአዲስ አበባ ቴዎድሮስ አደባባይ አካባቢ በሚገኘው የመኢአድ ዋና ጽህፈት ቤት በተካሄደው በትላንትናው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ 550 ገደማ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።
በዚሁ ጉባኤ ላይ በተደረገው የአመራር ምርጫ፤ መኢአድን ስድስት ለሚጠጉ ዓመታት ሲመሩ በቆዩት አቶ ማሙሸት አማረ ምትክ አቶ አብርሃም ጌጡ የፓርቲው ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል።
አቶ አብርሃም በአቶ ማሙሸት የኃላፊነት ዘመን የፓርቲው ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው አገልግለዋል። አዲሱ የፓርቲው ፕሬዝዳንት ይዘው የቆዩትን የተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንትነት ቦታ በጉባኤው ምርጫ የተረከቡት አቶ ሰማኝ አብርሃም ናቸው።
🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/14987/
@EthiopiaInsiderNews