ባለፉት ስድስት ወራት የተከሰተው የወባ ወረርሽኝ፤ አምና በተመሳሳይ ጊዜ ከነበረው “በሁለት እጥፍ” ጨምሯል ተባለ
የወባ ወረርሽኝ ስርጭት፤ ተፈናቃይ ዜጎች በሰፈሩባቸው አካባቢዎች እንዲሁም የመስኖ ስራ እና የስንዴ ልማት ባሉባቸው ቦታዎች ላይ “በእጅጉ መጨመሩን” የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ድጉማ ገለጹ።
በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ባለፈው ስድስት ወራት የተከሰተው የወባ ወረርሽኝ፤ ከአምናው ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ሲነጻጸር “በሁለት እጥፍ” መጨመሩም ተነግሯል።
ይህ የተገለጸው ዛሬ ረቡዕ ጥር 28፤ 2017 በተካሄደ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ ነው። የፓርላማው የጤና፤ ማህበራዊ ልማት፣ ባህል እና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የዛሬውን መድረክ ያዘጋጀው፤ የጤና ሚኒስቴርን የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ለማዳመጥ ቢሆንም በስብሰባው የቀረበው ግን የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሪፖርት ብቻ ነው።
የኢንስቲትዩቱ የመንፈቅ ዓመት ሪፖርት በዋነኛነት ያተኮረው፤ በኢትዮጵያ ከ2016 ዓ.ም አጋማሽ ጀምሮ በወረርሽኝ ደረጃ በተከሰተው በወባ በሽታ ስርጭት ላይ ነው።
በተቋሙ ሪፖርት መሰረት፤ ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ 658 ሰዎች በወባ ወረርሽኝ ህይወታቸው አልፏል። በዚሁ ጊዜ ውስጥ በወባ በሽታ የተጠቁ ሰዎች ብዛት ሰባት ሚሊዮን ገደማ እንደሆነም በሪፖርቱ ላይ ሰፍሯል።
በመንፈቅ ዓመቱ ከፍተኛው የወባ ህመምተኞች የተመዘገቡበት ክልል ኦሮሚያ ነው። ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ በኦሮሚያ ክልል በወረርሽኙ የተጠቁ ሰዎች ብዛት 3.2 ሚሊዮን መድረሱን የኢንስቲትዩቱ ሪፖርት አመልክቷል።
🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15011/
@EthiopiaInsiderNews
የወባ ወረርሽኝ ስርጭት፤ ተፈናቃይ ዜጎች በሰፈሩባቸው አካባቢዎች እንዲሁም የመስኖ ስራ እና የስንዴ ልማት ባሉባቸው ቦታዎች ላይ “በእጅጉ መጨመሩን” የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ድጉማ ገለጹ።
በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ባለፈው ስድስት ወራት የተከሰተው የወባ ወረርሽኝ፤ ከአምናው ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ሲነጻጸር “በሁለት እጥፍ” መጨመሩም ተነግሯል።
ይህ የተገለጸው ዛሬ ረቡዕ ጥር 28፤ 2017 በተካሄደ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ ነው። የፓርላማው የጤና፤ ማህበራዊ ልማት፣ ባህል እና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የዛሬውን መድረክ ያዘጋጀው፤ የጤና ሚኒስቴርን የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ለማዳመጥ ቢሆንም በስብሰባው የቀረበው ግን የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሪፖርት ብቻ ነው።
የኢንስቲትዩቱ የመንፈቅ ዓመት ሪፖርት በዋነኛነት ያተኮረው፤ በኢትዮጵያ ከ2016 ዓ.ም አጋማሽ ጀምሮ በወረርሽኝ ደረጃ በተከሰተው በወባ በሽታ ስርጭት ላይ ነው።
በተቋሙ ሪፖርት መሰረት፤ ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ 658 ሰዎች በወባ ወረርሽኝ ህይወታቸው አልፏል። በዚሁ ጊዜ ውስጥ በወባ በሽታ የተጠቁ ሰዎች ብዛት ሰባት ሚሊዮን ገደማ እንደሆነም በሪፖርቱ ላይ ሰፍሯል።
በመንፈቅ ዓመቱ ከፍተኛው የወባ ህመምተኞች የተመዘገቡበት ክልል ኦሮሚያ ነው። ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ በኦሮሚያ ክልል በወረርሽኙ የተጠቁ ሰዎች ብዛት 3.2 ሚሊዮን መድረሱን የኢንስቲትዩቱ ሪፖርት አመልክቷል።
🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15011/
@EthiopiaInsiderNews