የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፤ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ ትምህርቶች ይተላለፉበታል፡፡
ለአስተያየት: ጥቆማና ጥያቄ በዚህ ያግኙን ☞ @Ethiopian_Orthodox_bot

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


በገድለ አቡነ ሀብተ ማርያም ላይ ተጽፎ የሚገኝ አንድ መንፈሳዊ ታሪክ አለ፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን የእመቤታችን የድንግል ማርያም በዓል በሚከበርበት ዕለት ቅዳሴ ለመቀደስ የተዘጋጁ አንድ ካህን ነበሩ፡፡ እኚኽ አባት ማታ ተኝተው ሳለ አንድ ጋኔን በሴት አምሳል አብሯቸው በማደር ሕልመ ሌሊት እንዲያገኛቸው አደረገ፡፡ ከመኝታ ሲነቁም ቅዳሴ መግባት የማያስችል እንቅፋት እንደገጠማቸው ስላወቁ በእርሳቸው ቦታ ጻድቁ አቡነ ሀብተ ማርያም ተተክተው ቅዳሴውን አከናውነዋል፡፡ የገድላቸው መጽሐፍም የእመቤታችን ፈቃድ ቅዳሴውን አቡነ ሀብተ ማርያም እንዲቀድሱት ነበረ በማለት በግልጽ ይተርካል፡፡
ይህ ሁኔታ የተፈጸመው ስለ አቡነ ሀብተ ማርያምም ክብር ሲባል ነው። አቡነ ሀብተማርያም በእመቤታችን በድንግል ማርያም ዘንድ ምን ያህል ተወዳጅ እንደሆኑ ያሳያል:: ከዚህ አልፎ ግን “ያኚኽ ካህን ምን በደል ቢገኝባቸው ነው» ማለት አይቻልም፡፡ እንዲህ ማለት በሰው መፍረድ ነውና፡፡ መጽሐፈ ገድሉም ካህኑ እንደዚህ ያለ በደል ነበረባቸው ብሎ የሚጠቅሰው ምንም ነገር የለም፡፡ ያልተጻፈውንና የማናውቀውን መናገር በእግዚአብሔር ሥራ ገብቶ እንደ መተቸት ይቆጠራል፡፡ ይህ ታሪክ በሕልመ ሌሊት በሚፈተኑ ሰዎች ላይ እንዳንፈርድ ይልቁኑም በሌላ አቅጣጫ ማየት የሚገባን ነገር እንዳለ ያስረዳል፡፡

በቀጣይ «ዝንየት»ና መንፈሳዊ ሥርዓቱ ይቀጥላል....

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox


ከሥራ ብዛት ሕልም እንደሚታይ ጠቢቡ ሰሎሞን «ሕልም በሥራ ብዛት ይታያል» በማለት የተናገረው ቃል ያስረዳል፡፡ መክ5፥3 እንደዚሁም ሁሉ ከምኞት ብዛትም ሕልም ሊከሠት ይችላል:: ክፉ ምኞት በሕልምም ቢሆን ማርከሱ አይቀርም፡፡ ሐዋርያው ይሁዳ «እያለሙ ሥጋቸውን ያረክሳሉ» በማለት የጻፈው መልእክት እዚህ ቦታ ላይ ሊጠቀስ ይችላል፡፡ ይሁዳ 1፥ (ቁ8) እንደሚታወቀው ነፍስ እንደ ሥጋ አትተኛም እንቅልፍም በእርሷ ዘንድ የለም:: ስለዚህ ነፍስ በእንቅልፍ ልቤ ነው በማለት ማመካኘት አትችልም፡፡ ነፍስ በረከሠ ሕልም ምክንያት ከተጠያቂነት ነፃ መሆን የምትችለው ሥጋ ከእንቅልፍ ውጭ በሚሆንበት ጊዜ ተግባረ ዝሙትን በመቃወምና በመጥላት ከእግዚአብሔር ጋር መሆኗን ስታስመሰክር ብቻ ነው፡፡
ሌላው ሕልመ ሌሊትን እንደ ኃጢአት የሚያስቆጥረው ሁኔታ አብዝቶ መመገብ ነው:: ጾም ለጽድቅ ሥራ ሁሉ መሠረት እንደሆነ እንደዚሁ አብዝቶ መመገብም የኃጢአት ሁሉ መሠረት ነው:: ተብሏልና፡፡ ሰው ሁሉ ለቁመተ ሥጋ ያህል መመገብ ያሻዋል፡፡ መዝ103፥15 ሆኖም ለልዩ ልዩ የምግብ ዓይነቶች መጐምጀትና ከዚያም አልፎ አብዝቶ መመገብ ነፍስን ለሥጋ ማስገዛት ነው:: ይህ ደግሞ ገዥዋን ተገዥ ማድረግ በመሆኑ ግፍ ነው፡፡ ሊቀ ጳጳስ ለዐቃቢት እንደመገዛት ያህል ነውና፡፡
   ለሥጋ መገዛት የሚያሻውንም ሁሉ ጥሮ ግሮ ማቅረብ የገዛ ሰውነትን ማምለክ ነው፡፡ ሐዋርያው «ሆዳቸው አምላካቸው ነው፡፡» በማለት የተናገረው «እንብላ እንጠጣ ነገ እንሞታለን» በማለት ከሞት በኋላ ተከትሎ የሚመጣባቸውን ወቀሳና ፍርድ ችላ ላሉ ሰዎች ነው፡፡ በአዳምና በሔዋን ሊነገር የማይችል ውርደትና ጉስቁልና ያመጣባቸው ለሆዳቸው መገዛታቸው ወይም ለመብል መሳሳታቸው መሆኑ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ ፊልጽ3፥19፣ 1ቆሮ 15፥32፡ ዘፍ3፥ 1-24
ወጣቶች ይልቁኑም በዝሙት ሥራና ሐሳብ በእጅጉ የሚፈተኑ ስዎች በሚገባ መጾም አለባቸው:: በሰውነት ላይ የዝሙት ፆር ጸንቶ ሳለ አብዝቶ መመገብ የሚቃጠል ክርን ሰም እንደ መመገብ (መቀባት) ነው:: ሰም ክሩን የበለጠ እንደሚያቀጣጥለው አብዝቶ መመገብም የዝሙት ፍላጐትን የበለጠ እንዲበረታ ያደርገዋል፡፡ መጽሐፈ መነኮሳትም ይህን ሲገልጽ ይላል:: «እንጀራን መጥገብ›› ኃጢአት መባሉን ተመለከትክን? ሕዝ16:49 ስለዚህ በልክ ተመገብ እንጂ ለስስት አትሽነፍ፡፡
    ሳይጠነቀቅ ቀርቶ አብዝቶ ከመመገቡ የተነሣ ሕልመ ሌሊት ያገኘው ሰው እንደ ኃጢአት ይታሰብበታል፡፡ ምክንያቱም አብዝቶ መመገብ ኃጢአትን እንደሚወልድ እያወቀ ችላ ብለሎ በመመገቡ ነው፡፡ መጽሐፈ መነኮሳት አብዝቶ ከመመገብ የተነሣ ሕልመ ሌሊት ስለሚከሠትበት ሰው እንዲህ በማለት ይተርካል፡፡ «ወመንጸፈ ኅርትምናሁስ ወልብሱ ወትፍግዕተ ሥጋሁ ኩለንታሁ ርሱሕ፡፡ በእንተ ብዝኀ ውኂዝ ርኵስ ዘይውኅዝ እም ሥጋሁ ከመ ዐይነ ማይ አኮ በሌሊት ባሕቲቱ ዘይመጽእ ዝንቱ እስመ ሥጋ ያውኀዝ ወትረ ወያረኩሶ ለሕሊና›› ወደ አማርኛ ሲመለስ «ከሰውነቱ እንደ ምንጭ የሚነቃ ርኩስ ዘር በዝቶ ስለ ፈሰሰ ጎስቋላ ምንጣፉ፣ልብሱ፣በዝሙት ደስ የተሰኘ ሥጋው ሁለንተናው የረክሰ ነው:: ሥጋ ሁልጊዜ ያነቃዋልና ዘሩ የሚፈሰው በሌሊት ብቻ አይደለም፡፡ ሕሊናውንም ያረክሰዋል›› ማለት ነው፡፡ ይህም ለምግብ ከመሳሳትና አብዝቶ ከመመገብ የተነሣ የሚመጣ ሕልመ ሌሊት እንዴት ሰውን እንደሚያረክስና ኃጢአት ሆኖ እንደሚቆጠርበት ያስረዳል:: ማር.ይስ. አን.20 ምዕ.2

አንድ ሰው በንቁ ልቡና ሳለ ወደ ኃጢአት የሚየመሩትን ነገሮች ተግቶ እየተቃወመ ነገር ግን በተኛና ባንቀላፋ ጊዜ ዝንየት ቢያገኘው በተራክቦ፣ ዘር በማፍሰስ ያያት ሕልሙ ዕዳ ሆና አትቆጠርበትም፡፡ መሐሪ የሆነ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰውዬው ተቃወማት እንጂ ወዶ ወደ እርሷ እንዳልተሳበ ያውቃልና፡፡ አንቀላፍቶ ላለ ዘሩ ቢወርድ ፈልጎ አለመጣውምና ዕዳ አይሆንበትም፡፡ ነገር ግን ተቃውሞ ለማራቅ አልተቻለውም:: ይህ ከዚህ በላይ የሰፈረው ሐሳብ በግዕዙ እንዲህ ይነበባል።
ኃጢአትን ከልቡ በሚቃወምና በሚጠላ ሰው ላይ ሕልመ ሌሊት እንደ ኃጢአት እትቆጠርበትም፡፡ ይህን ለማስረዳት አረጋዊ በፊልክስዮስ መጽሐፍ እንዲህ የሚል ሐተታ አስፍሯል፡፡ ሰይጣን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን:- የኔን ወገኖች አጋንንትን ባንተ ወገኖች ላይ አሰለጥናቸዋለው፣ ነገር ግን ወገኖቼ የአንተን ወገኖች አይችሏቸውምና ድል ይሆናሉ:: እነርሱ ምንም ባይችሏቸው እኔ ግን «በሕልመ ሌሊት አስሕቶሙ» «በሕልመ ሌሊት አስታቸዋለሁ።» አለው:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ ለሰይጣን እንዲህ ሲል መለሰለት


በዐፍላ ጉርምስና ወቅት ፈጣን ዕድገት ከሚያሳዩና ከሚለጠጡ የሰውነት ክፍሎች መካከል የድምፅ ጅማቶች ስለሚገኙበት አንዳንድ ጊዜ ሳይታሰብ «ቀጭን» ድምፅ ማውጣትና የድምፅ መጎርነን እንደ ጉርምስና ምልክት ይታያሉ፡፡ የአዳም ፍሬ በመባል የሚታወቀው ‹‹ማንቁርትም» ማደግና መታየት የሚጀምረውም በዚሁ ጊዜ ነው፡፡

ከዚህም ሌላ ብዙ ወንዶች ብጉር የሚያበጉሩ ሲሆን፣ በብብት፣ በደረትና በብሽሽት (በአባለ ዘርዕ) አካባቢ ፀጉር ማብቀል ይጀምራሉ፡፡ እንደዚሁም ከራስ እስከ ጽሕም በግራና በቀኝ የሚወርድ ለጊዜው ለስለስ ያለና ስስ ጠጉር ወይም ሪዝ ማቆጥቆጥ ይጀምራል፡፡ ይህንን ጽሕም (ሪዝ) መከርከምና መቀነስ እንጂ ሴት እስኪመስሉ ድረስ ሙሉ በሙሉ ልጭት አድርጐ ማንሣት የሚገባ አይደለም፡፡ ይህን በተመለከተ ፍትሐ ነገሥት መንፈሳዊና ዲድስቅልያ የተሰኙ መጻሕፍት እንዲህ ብለዋል፡፡ «ወባሕቱ ኢመፍትው ለነ ንላጺ ጽሕመነ ወኢንወልጥ ፍጥረተ ብእሲ ውስተ ካልዕ ግዕዝ - ነገር ግን ጽሕማችንን ልንላጭ የወንድነት መልካችንን ወደ ሌላ ማለትም ሴት ወደ መምሰል እንለውጥ ዘንድ አይገባንም::›› ማለት ነው:: ዲድ.አን.1፤ ፍት.መን.አን .11 የጉልምስና ምልክት የሆነው የዚህ ጠጉር ብዛት ከሰው ሰው ይለያያል:: ሆኖም ምን ያህል መሆንን አመልካች አይደለም:: ሌለቹ የዐፍላ ጉርምስና ምልክቶች ደግሞ የሰውነት ጠረን መለወጥ፣ የዘር ፍሰት ወይም ሕልመ ሌሊት ማየት መጀመር ናቸው፡፡

«ሕልመ ሌሊት» ምንድር ነው?
በዐፍላ የጉልምስና ወቅት አባለ ዘርዕ ወደ ሙሉ የዕድገት ደረጃ መድረስ ብቻ ሳይሆን መሥራትም ይጀምራል:: በዚህ ጊዜ ከንዑስ መሌሊት (ኀፍረተ አካል) ዘርዓ ብእሲ የሚባል የአፍንጫ ዛሕል (ንፍጥ) የሚመስል ፈሳሽ ነገር ይወጣል፡፡ ወንድና ሴት ግንኙነት በሚያደርጉበት ጊዜ ወደ ሴቲቱ ማኅፀን በመግባት ፅንስ እንዲፈጠር የሚያደርገው ይህ ፈሳሽ ንጥረ ነገር ነው፡፡
የወንድ ወጣቶች ሰውነት ይነስም ይብዛ በየጊዜው ከላይ ‹‹ዘርዓ ብእሲ›› ወይም «የወንድ ዘር» ተብሎ የተጠቀሰውን ፈሳሽ ንጥረ ነገር ያስወጣል፡፡ ለዘር የበቁ ወጣቶች ዘር የሚከፍሉት ወይም የሚወጣቸው በልዩ ልዩ መንገድ ሲሆን አብዛኛውን ጊዜ ግን ተኝተው ሳለ በጠለቀ እንቅልፍ ሆነው ሕልም በሚያልሙበት ወቅት ነው፡፡ ይህ ሲሆን እንደ ጤናማ የተፈጥሮ ሂደት ይቆጠራል። የዚህ ዓይነቱን ሕልም መጽሐፈ መነኮሳት በአንድ ስፍራ «ሕልመ ጽምረት» በሌላ ቦታ ደግሞ «መስቆርርት ሕልም» ሲለው ይገኛል:: ሕልሙን ያየው ሰው ደግሞ «ዝንየት መታኝ» ወይም «ሕልመ ሌሊት» አገኘኝ ይላል፡፡ ይህ በቤተ ክርስቲያን ልጆች ዘንድ የተለመደና በቀላሉ የሚያግባባ የቃል አጠቃቀም ነው::
ወደ አቅመ አዳም እየደረሱ ባሉ ልጆች ላይ ይህ «የዘር ፍሰት» ባልጠበቁት ጊዜ ሲከስት በጣም ሊረብሻቸው ይችላል፡፡ ይልቁኑም ልጆቹ ከዚህ አስቀድሞ ስለ ጉዳዩ በተለያየ መንገድ በቂ ግንዛቤ ያላገኙ ከሆኑ መረበሻቸው በእጅጉ ይጨምራል፡፡ እነዚህ ታዳጊዎች እንዳይረበሹና ስለ ጉዳዮ የተሳሳተ ሐሳብ ይዘው እንዳያድጉ ለነገሩ በቂ ግንዛቤ እንዲያገኙ ከማድረግ ጋራ እንደ አስደሳች ተግባር በመውሰድ እያወቁ ዘራቸውን በራሳቸው እጅ ማፍሰስ እንዳይጀምሩ የነአውናንን በዚህ ተግባራቸው መቀሠፍ እየጠቀሱ ኃጢአትነቱን ኣጥብቆ ማስረዳት ያስፈልጋል::
መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እና በአጠቃላይ ስላለበት ሰው በዝርዝር ይናገራል፡፡ ዘሌ.15፥16፡ 15፥1-33  ይህንን ጨምሮ የወንድ ዘርን የሚመለከት ሐሳብ የያዙ መንፈሳዊ መጻሕፍቶችን ማንበብ ለወጣቶች የተሻለ ግንዛቤ ይሰጣቸዋል፡፡ ይህን በመሳሰሉ ፆታዊ ጉዳዮች ላይ ወጣቶች ጥያቄ ሲኖራቸው ከማን ጋር መወያየት የተሻለ እንደሚሆን ሊለዩ ይገባል፡፡ ልጆች የሚጓዙበት ተፈጥሮአዊ የሕይወት ጐዳና በሙሉ ጤናማ ወላጆች የተጓዙበት ስለሆነና ሌሎችም ብዙ ተሞክሮዎች ስላሏቸው ለልጆች ፆታዊ ችግር ጉዳት የሌለበት የመፍትሔ ሐሳብ ማቅረብ ይችላሉ፡፡ ካህናትና መምህራነ ቤተ ክርስቲያንንም ማማከር ለወጣቶች መንፈሳዊውን ሥርዓት እንዲያውቁ ይረዳቸዋል፡፡ እኩዮችንና ሌሎች ወጣቶችን ወይም የእግዚአብሔርን ቅዱስ ቃል መሠረት ያላደረጉ ጽሑፎችን መስማትና ማንበብ ጥቂት እውነትና ብዙ የፈጠራ ወሬ ያለበትን የተሳሳተ መረጃ በመስጠት ወጣቶችን ወደ ተሳሳተ አቅጣጫ ሊመሯቸው ይችላሉና ሊጠነቀቁባቸው ይገባል፡፡

«ሕልመ ሌሊት» ኃጢአት ነውን?
በጠለቀ እንቅልፍ ላይ ሳሉ የሚከሠት ሕልመ ሌሊትን እንደ ኀጢአት እንዲቆጠርና እንዳይቆጠር የሚያደርጉ የተለያዩጨሁኔታዎች አሉ:: ስለዚህ ሕልመ ሌሊትን በጥቅሉ ኀጢአት ነው ወይም አይደለም ማለት አይቻልም፡፡ ነገር ግን እንደ ኀጢአት እንዲቆጠር የሚያደርጉ ሁኔታዎችን በመጠኑ መዘርዘር ይቻላል፡፡

ሀ. አጋንንት የሰው ልጆችን በልዩ ልዩ መንገድ ክፉኛ ይዋጓቸዋል፡፡ የሰው ልጆች ሲያንቀላፉ አጋንንት ግን ለቅጽበት እንኳን እያሸልቡም፡፡ ያንቀላፋውን ሰው እስኪነቃ ድረስ እንኳን አይጠብቁትም: አጋንንት የሰውን ልጅ በተኛበት ክፉ ክፉ ሕልም በማሳየት ይፈትኑታል፡፡ አንድ ጊዜ የተራቆተ የሴት ገላ፣ በሌላ ጊዜ ደግሞ እንደ ወንድና ሴት አለሌና ባዝራ እየሆኑ ሲጨዋወቱና ሲደራረጉ በምትሐት ያሳዩታል፡፡ በዚህ ጊዜ እርሱም በዝሙት ሐሳብ ይሳብና በሕልሙ ዝሙት ሲፈጽም ያድራል፡፡ በዚህ መልኩ የተከሠተ ሕልመ ሌሊት «ጸዋግ» ወይም «ኅሡም» ሕልም ይባላል፡፡ ክፉ ወይም ጥፉ ሕልም ማለት ነው:: በዚህ መልኩ አጋንንት ሰውን እንደሚዋጉት በመጽሐፈ መነኮሳት እንዲህ ተጽፏል፡፡ «ይትቃተልዎ ሰይጣናት በመዓልት በሕሊናት እኩያት ወበሌሊት በአሕላማት ኅሡማት» በአማርኛ «ሰይጣናት የሰውን ልጅ ቀን ቀን ክፉ ሐሳብ በማሳሰብና በማሠራት በሌሊት ደግሞ ዝሙት የሞላበት አስጸያፊ ሕልም በማሳየት ይዋጉታል» ማለት ነው፡፡ በዚህ መልኩ ሰይጣናት ያቀረቡለትን ረቂቅ ፈተና ከመቃወም ይልቅ
ደስ እያለው የሚያጣጥም ማለትም ከመጸጸትና ከመቆጨት ይልቅ በደስታ ስለ ዝሙት የሚያሰላስል፣ የሚዳራ፣ የሚዛለል፣ ወደ ዝሙት ከሚያመሩ ማናቸውም ነገሮች የማይሸሽ ሰው እነዚህ ነቅቶ ሳለ ያልተቃወማቸውን ተግባራት በሕልሙ በሚፈጽማቸው ጊዜ በተግባር እንደፈጸማቸው ያህል ኃጢአት ሆነው ይቆጠሩበታል:: ይህን የሚያስረዳ እንዲህ የሚል የመጻሕፍት ቃል ይገኛል:: «ዘይትቄበል በመዓልት ስሕተታተ ፍትወት ውስተ ልቡ ወኢይከሥታ ወለዝንቱ ሕሊናቲሁ ወአሕላማቲሁ ወፍትወታቲሁ ርኩሰት ትትሐሰብ ሎቱ ኃጢአተ» ይህም ‹‹በቀን ነቅቶ ሳለ ኃጢአትን ወዶ የሚቀበልና ገልጾ የማይናዘባት ለዚያ ሰው የረከሰች ሐሳቡ፣ ሕልሙ ኃጢአት ሆና ትቆጠርበታለች፡፡» ማለት ነው፡፡
በተጨማሪም


.                      ምዕራፍ ሦስት
             የዐፍላ ጉልምስና ምልክቶች

    ዐፍላ የጉርምስና ወቅት የጉልምስናን የመጀመሪያ ወቅት ይሸፍናል፡፡ ጉልምስናና ጉርምስና የሚሉት ቃላት አንድ ናቸው። የዘይቤ እንጂ የምስጢር ልዩነት የላቸውም፡፡ ይህ ወቅት በፆታ የመብሰል ምልክቶች የሚታዩበት ዕድሜ ነው፡፡ ከላይ እንደተጠቀሰው ጉልምስና የሚጀምርበት ዕድሜ እንደየሰዉ ሁኔታ ከፍና ዝቅ ሊል ስለሚችል የኔ ፈጥኗል የኔ ደግሞ ዘግይቷል በማለት ሊጨነቁበት የሚገባ አይደለም፡፡ የሆነው ሆኖ አንድ ሰው በጉልምስና ወቅት ሊከሠቱ ከሚችሉ የአካል ለውጦች ጋር ተያይዘው የሚከሠቱ ሌሎች ለውጦችንበሚገባ ሊያውቃቸውና ሊጠብቃቸው ይገባዋል:: እነዚህም ለውጦች በአጭሩ ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል፡፡

  በጉልምስና ወቅት ከሚከሠቱ የአጥንቶች ዕድገትና የጡንቻዎች መለጠጥ የተነሣ በወጣቶች ላይ የመፍዘዝና የቅንብር ጉድለቶች ይስተዋላሉ:: በዚህ ምክንያት ለአደጋ መጋለጥ እንዳይኖር ተጨማሪ ጥንቃቄ ቢያስፈልግም ይህ ዓይነቱ የመቅዘዝና ቅስስ የማለት ሁኔታ ጊዜውን ጠብቆ ያልፋልና የሚያሳስብ ጉዳይ አይደለም:: ወጣቶች በብዙኀኑ ዘንድ የሚታወቁበት ገጽታ ንቁነትና ቀልጣፋነት ቢሆንም በአፍላ የጉልምስና ወቅጥ መፍዘዝና ቅስስ የማለት ሁኔታ መከሠቱን ማወቅ ለሚያሳዩት ባሕርይና ያልተለመደ እንቅስቃሴ ሌላ ትርጓሜ ከመስጠት እንድንቆጠብ ይረዳል፡፡






ምኩራብ
የዐብይ ጾም ሦስተኛ እሑድ(ሳምንት)


ሦስተኛው ሰንበት ምኩራብ ተብሎ የተሰየመበት ምክንያት በዚሁ ዕለት የሚዘመረው ጾመ ድጓ ከዋዜማው ጀምሮ እስከ ሰላሙ ድረስ በዕለተ ሰንበት «ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ» «ምኩራብ» ማለትም ቀጥተኛ ፍችው ኮረብታ፣ ተራራ የሚያኸል ታላቅ ሕንጻ ማለት ነው፡፡

ከዚህም የተነሣ የአይሁድ ቤተ ጸሎት ወይም ቤተመቅደስ ማለት ይሆናል፡፡ ዐቢይ ፍሬ ቃሉ ግን ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ድውያነ ሥጋን በትምህርቱ፣ ድውያነ ነፍስን በታምራቱ ሲፈውስ በምኩራብ እየተገኘ የፈጸመውን የማዳን ሥራ በኀሊና እያሳሰበ የሚያስተምር ሦስተኛ ሳምንት ነው፡፡

ዮሐ. 2:12 «ኢየሱስ በሰንበት ቀን ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ» እያለ ኢየሱስ በአይሁድ ምኩራብ ማስተማሩን እየጠቃቀሰና እያነሣሣ ስለሚዘምር ይህን ሰንበት ለዚህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ እየገባ ለማስተማሩና በምኩራብ የሚሸጡ የሚለውጡ ነጋዴዎችን ለማስወጣቱ ቤተ መቅደሱን ለማስከበሩ መታሰቢያ ሳምንት ነው።

የዕለተ ሰንበት መዝሙር (ከጾመ ድጓ)
ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት ወይቤሎሙ ምጽዋተ አበድር እመሥዋዕት አነ ውእቱ እግዚኣ ለሰንበት ወአቡሃ ለምሕረት እግዚኣ ውእቱ ለሰንበት ወልደ እጓለ እመሕያው ኢትግበሩ ቤተ አቡየ ቤተ ምስያጥ ቤትየሰ ቤተ ጸሎት ይሰመይ ቦአ ምኩራቦሙ ወገሠፆሙ ያርምሙ አንከሩ ምህሮቶ ሞገስ ቃሉ ወጣዕመ ነገሩ ወሣዕሣዓ አፉሁ፡፡

ትርጉም:-
ጌታችን ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ፤ የሃይማኖት ቃልን አስተማረ፤ ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን እወዳለሁ፤የሰንበት ጌታዋ የምሕረት አባቷም እኔ ነኝ፤ የሰው ልጅም የሰንበት ጌታዋ ነው ፡፡ያባቴን ቤት የንግድ ቦታ አታድርጉት፤ቤቴስ የጸሎት ቤት ይባላል (እያለ የሃይማኖትን ቃል አስተማራቸው፡)፡ ወደ ምኩራባቸውም ገብቶ ዝም ይሉ ዘንድ ገሠፃቸው፤ እነርሱም ትምህርቱን፣ የቃሉን ግርማ፣ የአነጋገሩን ጣዕምና፣ የአንደበቱን ቅልጥፍና አደነቁ።

ምስባኩም፦ መዝ ፷፰፥፱
"እስመ ቅንዐት ቤትከ በልዐኒ ትዕይርቶሙ ለእለይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ"
"የቤትህ ቅናት በልቶኛል የሚሰድቡህም ስድብ በላዬ ወድቆብኛልና ነፍሴን በጾም አስመረርኳት"

በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ ጥቅሶች
-ቆላ ፪፥፲፮ እስከ ፍጻሜ
-ያዕ ፪፥፲፬ እስከ ፍጻሜ
-የሐዋ ሥራ ፲፥፩-፱

ወንጌሉም፦ ዮሐ ፪፥፲፪ እስከ ፍጻሜ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox


በዕፀ መስቀሉ
በዕፀ  መስቀሉ የተከፈለልኝ
የኢየሱስ ፍቅር  ምንኛ ማረከኝ
ከፍቅርም በላይ ሆነና መሠጠኝ
ከመስቀል ሥር ሁኜ ፊቱን እያየሁኝ

ዓለምን በፍቅሩ ያሸነፈ ጌታ
የጸብን ማዕበል በፍቅሩ የገታ
ሕይወቴን ጸጥ አድርጎ ይምራት በምልሐቱ
እኔ ምን አለፍኝ አልደክምም በከንቱ
አዝ.....
ደሙ ከወዙ ጋር ተዋሕዶ ሲወርድ
በእኔ በደል ጌታዬ ቀረብልኝ ለፍርድ
ሀጥያቴን በጫንቃዉ ተሸክሞልኛል
በደሌን ደምሥሶ ንፁሕ አድርጎኛል
አዝ......
የቀራንዮ ግፍ በአንተ ላይ የሆነዉ
ሰይጣንን ጠርቆ ከመንገድ አወጣዉ
እሾሕ አሜኬላዉ ተደምስሶልናል
የንጹሕ በግ ደም አዳምን ታድጓል
አዝ......
ይኽንን ሥጋዬን ብሉ ይላችሁዋል
ይኽንን ደሜንም ጠጡ ይላችሁዋል
ከመስቀል ሥር ሆነን ደሙን እንቀበል
ሥጋዉን እንብላ ሠዉ ሆይ ችላ አንበል

ሊቀመዘምራን ይልማ ኃይሉ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox




መጋቢት ፲
በዓለ ቅዱስ መስቀል


መጋቢት አስር በዚህች እለት የክብር ባለቤት ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል የተገለጠበትና የተገኘበት ነው። የዚህም የከበረ ዕፀ መስቀል መገለጡና መገኘቱ ሁለት ጊዜ ሆኗል።

መጀመሪያ የፃድቁ ንጉስ የቆስጠንጢኖስ እናት በሆነች በንግስት እሌኒ እጅ ነው።
እርሷ ለእግዚአብሄር ተስላ ነበርና ልጇ ቆስጠንጢኖስ ወደ ክርስቲያን ሀይማኖት ቢገባ ወደ ኢየሩሳሌም ሄዳ መስቀሉን እስከ አገኘችው ድረስ ልትፈልግው በኢየሩሳሌም ያሉ ቅዱሳት መካናትንና አብያተ ክርስቲያናትን ልታንፃቸው ነው።

ከዚህ በኋላ ልጇ አምኖ የክርስትና ጥምቀትን በተጠመቀ ጊዜ እሌኒ ቅድስት ወደ ኢየሩሳሌም ሄደች ከእርሷ ጋርም ብዙ ሰራዊት ነበር ደርሳም ስለ ከበረ መስቀል መረመረች የሚያስረዳት አላገኘችም የአይሁድ ወገን የሆነ አንድ ሽማግሌ ሰው አስራ በርሀብና በጥማት አስጨነቀችው።
በተጨነቀም ጊዜ ለንግስት እሌኒ "የጉልጎታን ኮረብታ አስጠርጊ" ብሎ ነገራት እርሷም ይጠርጉ ዘንድ አይሁድን አዘዘቻቸው።

ቤቱን የሚጠርግ ሰው ሁሉ ጥራጊውን በውስጡ የከበረ መስቀል በአለበት በጌታችን መቃብር ላይ እንዲጥል አይሁድ አስቀድመው አዝዘው ነበርና ንግስት እሌኒ እስከደረሰችበት ጊዜ ከሁለት መቶ አመት በላይ ጥራጊያቸውን ሲጥሉበት ኖሩ ኮረብታም ሆነ። አይሁድም በጠረጉ ጊዜ ሶስት መስቀሎች ተገለጡ የክብር ባለቤት ክርስቶስ የተሰቀለበት የትኛው እንደሆነ አላወቁም።
የሞተ ሰውም አግኝተው አመጡ። አንዱንም መስቀል አምጥተው በሞተው ሰው ላይ አኖሩት አልተነሳም ደግሞ ሌላውን መስቀል አምጥተው በሙቱ ላይ አኖሩ አሁንም አልተነሳም ከዚህም በኋላ ሶስተኛውን መስቀል አምጥተው በሙቱ ላይ አደረጉት ያንጊዜ የሞተው ሰው ተነሳ እሌኒም የክርስቶስ መስቀል እንደሆነ አውቃ ሰገደችለት የክርስቲያንም ወገኖች ሁሉ ሰገዱለት።

ለልጇ የላከችው ይህ መስቀል ነው የሚል በሌላ መፅሀፍ ይገኛል የቀረው ግን ግንዱ በውስጡ ተተክሎበት የነበረው ከእርሱም እኩሌታውን ከቅንዋቱ ጋራ ወደ ልጅዋ የላከችው ነው።

ከዚህም በኋላ ስርዓታቸውና የህንፃቸው ነገር በመስከረም ወር በአስራ ሰባት ተፅፎ የሚገኝ አብያተ ክርስቲያናትንና የከበሩ ቦታዎችን አነፀች።

ሁለተኛው በሮሙ ንጉስ በህርቃል ዘመን የሆነው ሲሆን የፋርስ ሰዎች በግብፅ አገር ሳሉ ወደ አገራቸው ሊመለሱ ወደዱ። ከሹማምንቶቻቸው አንዱ የጦር መኰንን ተነጥሎ ወደ ኢየሩሳሌም አልፎ ደረሰ ወደ ከበረ መስቀል ቤተ ክርስቲያንም ገባ። መስቀሉም በላዩ በተተከለበት ግንድ ፊት ታላቅ ብርሀን ሲበራ አይቶ ሊያነሳው እጁን ዘረጋ። እሳትም ወጥታ እጁን አቃጠለችው።

ከክርስቲያን በቀር ማንም ሊነካው እንደማይችል የመስቀልን የክብሩን ነገር ሰዎች ነገሩት። ሁለት ዲያቆናትንም ይዞ የከበረ መስቀልን እንዲሸከሙ አዘዛቸው ከኢየሩሳሌምም ብዙ ሰዎችን ማርኮ ወደ አገሩ ተመለሰ።

የፋርስ ሰዎች ኢየሩሳሌምን እንዳጠፏት ብዙዎች ሰዎችንም እንደማረኩና የከበረ የክርስቶስንም መስቀሉን እንደወሰዱ የሮም ንጉስ ህርቃል በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ። ስለርሱም እንዲፆሙ ምእመናንን አዝዞ ወደፋርስ ዘምቶ ወጋቸው ብዙዎችንም ገደላቸው የከበረ እፀ መስቀልንም እየፈለገ በሀገራቸው ሁሉ ዞረ ግን አላገኘውም።

ያ ዲያቆናቱና መስቀሉን የወሰደ መኰንን ከቦታዎች በቤቱ አንፃር ባለ በአንድ ቦታ ላይ ወስዷቸው ጥልቅ ጉድጓድ እንዲቆፍሩ አዝዞ በዚያ የከበረ መስቀልን አስቀበረ እነዚያንም ዲያቆናት ገደላቸው።

ነገር ግን ያ መኰንን የማረካት የካህናት ወገን የሆነች በእርሱ ቤት የምትኖር አንዲት ብላቴና ነበረች። እርሷም የከበረ መስቀልን ሲያስቀብርና ሁለቱን ዲያቆናት ሲገድላቸው በቤቱ ውስጥ ሁና በመስኮት ትመለከት ነበር ወደ ንጉስ ህርቃልም ሂዳ መኰንኑ ያደረገውን ሁሉ ነገረችው።
ይህም ንጉስ ሰምቶ እጅግ ደስ አለው ያቺ ብላቴናም መራችው ከእርሱም ጋራ ብዙ ሰራዊት ሆኖ ኤጲስቆጶሳትና ካህናትም ነበሩ ።ወደ ቦታውም እስከምታደርሳቸው ያቺን ልጅ ተከተሏት ቆፍረውም የከበረ እፀ መስቀልን አገኙት ከአዘቅቱም አወጡት ንጉሱና ሰራዊቱም ሰገዱለት።

በልብሰ መንግስቱም አጎናፀፈው ታላቅ ክብርንም አከበረው ከሰራዊቱም ጋር እጅግ ደስ አለው። የዚህም መስቀል ሁለተኛ የተገለጠበትና የተገኘበት በዚች ቀን በመጋቢት አስር ነው፡፡ ከዚህ በኋላ ንጉሱ የከበረ እፀ መስቀልን ተሸክሞ ወደ ቁስጥንጥንያ ከተማ ወሰደው፡፡

የመድኃኒታችን የመስቀሉ በረከት ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን።

©ስንክሳር

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox


ጐርፍና ነፋስ ምን ዓይነት ትርጓሜ እንዳላቸው ከላይ ተብራርቷል። የተባለ ግን የእግዚአብሔር ቃል ነው። ስለዚህ ወጣቶች በቤት የተመሰለ ሕይወታቸው እንዳይናጋና እንዳይፈርስ ኑሮአቸውን መመሥርት ያለባቸው በምክረ ካህን በፈቃድ ካህን ላይ ነው:: ካህናት ወጣቶችን የሚመክሩበት የእግዚአብሔር ቃል እውነተኛ የ ነውና፡፡
  ወጣቶች ከፈቀዱ በእግዚአብሔር ቃል ላይ መመሥረት ብቻ ሳይሆን ቃሉ ከውስጣቸው እንዳይጠፋ ማድረግ ይችላሉ፡፡ ምክንያቱም ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ በማለት የተናገረው ከአረጋውያንና ከባልቴቶች ይልቅ የእግዚአብሔርን ቃል በልቡና መያዝ ለወጣቶች የሚቻል ነገር ስለሆነ ነው፡፡ 1ዮሐ2፥14
        ወጣቶችና ፆሮቻቸው(ፈተናዎቻቸው)
  በቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ አስተምህሮ መሠረት ምዕመናን በአምስት መደብ ይመደባሉ። ይህም መደብ ይባላል፡፡ አምስቱ ፆታ ምእመናን የሚባሉት ካህናት፤ መነኮሳት፣ አዕሩግ(አረጋውያን)፣ ወራዙት(ወንድ ወጣቶች)፣ እና አንስት(ሴት ወጣቶች) ናቸው።
  አምስቱም ፆታ ምእመናን በየራሳቸው የሚቸገሩበት ዓቢይ ፈተና አለ፡፡ በመባል የሚታወቀው ይህ ዓቢይ ፈተና ነው:: የካህናት ፆራቸው ትዝኅርት (ትዕቢት) ነው:: የመነኮሳት ፆር ስስት ሲሆን የአረጋውያን ደግሞ ፆራቸው ፍቅረ ንዋይ ነው። ቀሪዎቹ ወጣት ወንዶች ሲሆኑ ዐቢይ ፆራቸውም ዝሙት ነው:: የወጣት ሴቶች ዓቢይ ፆር ደግሞ ትውዝፍት(የምንዝር ጌጥን መውደድ) ነው።(ዮሐ 5፥4 ትርጓሜ)
  ይህ ማለት ግን ዋና ዋና ፈተናቸውን አንጓሎ ለመናገር ነው እንጂ እያንዳንዱ ፆታ ምእመን የሚፈተነው በአንድ ነገር ብቻ ነው ማለት አይደለም። እንዲሁ በዋና ፈተናው ድል የተደረገ ምእመን ሌሎች ጥቃትን ፈተናዎች ይረባረቡበታል። ነገር ግን ዋናውን ፆሩን ድል ካደረገ የሚመጡበትን ሌሎች ፈተናዎች በቀላሉ ድል ለማድረግ ይቻለዋል።
  ወጣቶች ልዩ ልዩ ፆር(ፈተና) እንዳለባቸው ነገር ግን ዕድሜያቸው እየገፋ በመጣ ቁጥር ወጣትነታቸው ሲያልፍ የወጣትነት ፈተናቸውም አብሮ እንደሚያልፍ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ሲህ ተናግሯል:: ይህ ንባብ ወደ አማርኛ ሲመለስ ማለት ነው:: ዮሐ.አፈ.ተግ.7

ምዕራፍ ሦስት ይቀጥላል...

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox


             የወጣቶች ምኞት
  የሰው ልጆች ከልጅነት ወደ ወጣትነት በሚሸጋገሩባቸው ወራትና ዓመታት አካላቸው እንደሚደረጅና አእምሮቸው እንደሚዳብር ሁሉ ምኞታቸውም በዓይነትና በመጠን እየሰፋና እየጨመረ ይሄዳል፡፡ ይህ የወጣቶች ምኞት በአመዛኙ ከመንፈሳዊነት ጋር የሚቃረንና ሥጋዊ በመሆኑ «እኩይ ፍትወት» ይባላል፡፡
  ከዚህም በተጨማሪ በጎልማሶችና በኮረዶች ላይ የሚከሠተውን ምኞት ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በማለት የክርስትና ልጁን ጢሞቴዎስን በመከረበት ጊዜ ይህንን የወጣትነት ምኞት «ክፉ የወጣትነት ምኞት>> ብሎ ሲጠራው እናነባለን፡፡
  በእርግጥ በወጣትነት ዘመን የሚገኝ ምኞት እጅግ ክፉ ነው:: ወጣትነት የሚሠራበት ዘመን እንጂ የሚመኙበት ዘመን አይደለምና። በተጨማሪም በዚህ ዘመን የሚከሠት ምኞት በወጣቶች አእምሮ ክፉነቱ ሊደረሰበት የማይችልና አታላይ ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ «ሰው ራሱ በገዛ ምኞቱ ሲሳብና ሲታለል ይፈታናል::>> በማለት እንደተናገረው በወጣትነት ዘመን የሚገኝ ምኞት ከመጠን በላይ ወደ ጥፋት የሚስብ፥ የሚጐትትና ነው፡፡
  በተለይም የሚለው ቃል ምኞት ከፍተኛ ጉልበት እንዳለው ይጠቁማል፡፡ በወጣትነት ዘመን ምንም አእምሮ የበሰለ ቢሆን ከዚያ የሚበረታው ግን ምኞት ነው፡፡በወጣቶች ላይ ከዕውቀታቸው ይልቅ ምኞታቸው መበርታቱን ለማስረዳት ወጣትነት ይመሰላል፡፡
  ኦሪት ከመሠራቷ በፊት ያለው ዘመን የሕገ ልቡና ዘመን ይባላል:: በዘመኑ ምንም ሕግና ሥርዓት ባለመኖሩ ሰው በልቡናው እንደ መሰለው ይኖር ነበር። እንዲሁም ሁለ ሕፃናት በልቡናቸው እንዳሰቡት ስለሚኖሩ በሕገ ልቡና የሚኖሩ ሰዎችን ይመስላሉ:: በዘመነ ኦሪት ደግሞ በመስፍኑ ሙሴ አማካኝነት ለእስራኤላዊያን ሕግ ተሰጠ:: ዘመኑም ዘመነ ኦሪት ተባለ፡፡ ሕገ ኦሪት በዘመኗ ክፉና ደግን ለመለየት አስችላለች:: እንደዚሁም ሁሉ ወጣትነት ከሕፃንነት ዘመን ይልቅ ክፉና ደግን ለመለየት የሚቻልበት ዕድሜ በመሆኑ በዘመነ ኦሪት ይመሰላል፡፡ ሆኖም ምንም ዕውቀት ቢገኝ በዘመነ ኦሪት የሰው ባሕርይ በኃጢአት የጐሰቆለ ስለ ነበር ሕጉን ፈጽሞ ለመጽደቅ አልተቻለም ነበር። በተመሳሳይ መልኩ ወጣቶች ዕውቀታቸው እየጨመረ ቢመጣም ምኞታቸውም የዛኑ ያህል ስለሚበረታና ስለሚስባቸው ዕውቀታቸውን ተጠቅመው የሚያጸድቃቸውን ጐዳና ለመከተል ይቸግራሉ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ሮሜ7፥23 በማለት የተናገረው በወጣቶች ዘንድ ምኞት ምን ያህል ወጥመድ እንደሆነ ሲገልጽ ነው፡፡
  ቅዱስ አባ ሕርያቆስም ስለ እመቤታችን ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም አስተዳደግ በተናገረበት የቅዳሴ መጽሐፍ እንዲህ ብሏል “አኮ ድንግል ወራዙት ስፉጣን ዘናዘዙኪ አላ መላእክተ ሰማይ ሓወጹኪ፤ ድንግል ሆይ የሚያታልሉ ጕልማሶች ያረጋጉሽ አይደለሽም:: የሰማይ መላእክት ጎበኙሽ እንጂ>> ይህ አገላለጽ ወጣቶች በወጣትነት ምኞት እንደሚታለሉ ከመግለጹም ባሻገር እነርሱ በምኞታቸው ተሸንግለው ሌላውን ለማታለል እንደሚያባብሉ ይናገራል፡፡ እመቤታችን ግን በሰማይ መላእክት ተጎበኘች እንጂ በሚያታልሉ ጐልማሶች አልተጽናናችም፡፡
   በውስጣችን እንዲኖርና እንዲያድግልን የምንንከባከበው ነገር መሆን የለበትም:: ምኞት ተስፋ አይደለምና፡፡ ኃጢአተኛ ሰው ምኞት ያበዛል። በማለት ጠቢቡ ሰሎሞን የተናገረው ለዚህ ነው፡፡ ምኞት ተጭኖን እንዳንሞት ምኞታችንን መወሰን ጥረትን ግን ማብዛት መልካም ነው።
   «ምኞት። አስደሳችና ጣፋጭ ነገር ትመስል ይሆናል እውነቱ ግን እንዲህ አይደለም፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ምኞት እንዲህ ይላል፡- ይህም ማለት ነው፡፡ ምኞትን ማብዛት ልፋትን ወይም ተስፋ መቁረጥን ማብዛት ነው። ምክንያቱም ምኞትን ለማሳካት ብዙ መድከም ከማስፈለጉም በላይ ብዙ ምኞት ካልተሳካ የሚያስከትለው ተስፋ መቁረጥም እንደዚሁ ብዙ ይሆናል።
  ብዙ ወጣቶች የሚመኙት ጉዳት የሚያስከትልባቸውንና ከጥቂት ጊዜ በኋላም በብርቱ የሚያስቀጣቸውን ነገር ነው፡፡ ከሁሉ የሚደንቀው ደግሞ ጓጉተው ይፈልጉት እንጂ ሲያገኙት ወዲያው የሚሰለቹት ወይም የሚጸጸቱበት መሆኑ ነው:: አሁን ሀብታም ከመሆን በላይ ምንም የምፈልገው ነገር የለም ትላለህ:: ሀብታም ስትሆን ግን ይህ ከንቱ እንደሆነና ሌላ የሚቀርህ ብዙ ነገር እንዳለ ይሰማሃል። ይህ የሚሆነው ሁሉንም ነገር የተሟላና ፍጹም የሚያደርገው የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር በመሆኑ ነው። ፈጣሪን ሳይጠጉ ምንም ነገር በቂና አርኪ መሆን አይችልም:: ስለዚህ መመኘትና ለማግኘት መጣር ብቻ ሳይሆን አስቀድመህ ፈጣሪህን መጠጋት ይኖርብሀል።
  በወጣትነት የሚከሠት ምኞት አንድ ብቻ አይደለም:: ወጣቶች ሁሉም ያምራቸዋል። ከዚህ የተነሣ በአንድ ነገር ላይ መርጋትና መጽናት አይሆንላቸውም:: ተምሮ በማዕርግ መሠረቅ፣ አጭቶ ማግባት፣ ሀብታም ነጋዴ መሆን፣ ትልቅ ባለሥልጣን መሆን ጊዜ ሰጥተን በተራ ብንኖርባቸው ጊዜ ጠብቀው ይሳካሉ፡፡ እነዚህን ነገሮች በአንድ ጊዜ ለማሳካት ብንጥር ይሳካሉን? አበው እንደሚለት ይሆንና አንዱም ላይሳካልን ይችላል:: ስለዚህ ወጣቶች አንድን ነገር መጀመር ሳይሆን በእርጋታ ሆኖ እስከ መጨረሻ መፈጸም እንደሚኖርባቸው ማወቅ አለባቸው::
  ከዚህም ሌላ ወጣቶች ምኞቶቻቸው ብዙ ከመሆናቸው የተነሣ ሁለት የማይጣጣሙ ነገሮችን በአንድ ላይ የሚመኙበት ጊዜ አለ፡፡ ሙሽራ ሲያዩ ማግባትንና መውለድን ይመኙና በዚያው ጊዜ ደግሞ ልቡናቸው በመንፈሳዊ ነገር ተነክቶ መመንኮስና መመነንን የሚመኙበት ጊዜ አለ። ታዲያ እነዚህን ሁለት የሚጻረሩ ፍላጐቶች በአንድ ሰው ሕይወት ውስጥ እንዴት ማስኬድ ይቻላል:: ይህ መታወክ ነው።  እንዲህ ያለ ነገር ሲከሰት ወጣት ከመሆናችን የተነሣ እሳታዊና ነፋሳዊ ባሕሪያችን እየተሟገቱ ፈተና ላይ መውደቃችንን ተረድተን ብንታገሥ እንዲህ ያለ ፈተና ከጊዜ ብዛት ራሱ ይርቃል።
  በማቴዎስ ወንጌል ማቴ 7፥25 ተብሎ የተጻፈው ኃይለ ቃል ሲተረጐም የተባለው የወጣት ሕይወት ነው፡፡ ማለት የአጋንንት ፈተና በወጣቱ ላይ ተነሣበትና ከሴት ርቆ ንጽሕናውን ጠብቆ እንደ እንጦንስና እንደ መቃርስ ለመኖር እንዲመኝ አደረገው ማለት ነው ይለናል፡፡ ማለት ደግሞ ያንኑ ወጣት እንደ እንጦንስና እንደ መቃርስ መኖር አይቻለኝም ባይሆን እንደ ኢዮብና እንደ አብርሃም አግብቼ ልጆች ወልጄ በሕግ ጸንቼ ልኑር አሰኘው ማለት ሲሆን ማለት ደግሞ በመጨረሻ ተስፋ በመቁረጥ ሁሉንም አልችልም እስኪል ድረስ አደረሰው ማለት ነው፡፡ ለመመነንም ሆነ ለማግባት መመኘት መልካም ነገር ሆኖ ሳለ በማይሆን ጊዜና በስሜታዊነት የሚወሰን ግን አይደለም:: ወጣቶችን እንዲህ ያለ መንፈሳዊ የሚመስል የሰይጣን ፈተና ሊያውካቸው ስለሚችል በግብታዊነት ከመወሰን ይልቅ በምክረ ካህን በፈቃደ ካህን መኖር ይኖርባቸዋል፡፡ ያ ቤት ነፋስ ነፍሶበት ጐርፍ ጐርፎበትና ዝናብ ዘንቦበት አልወደቀም፡፡ ምክንያቱም ስለ ተመሠረተ ነው። ዝናብ፣


  አረጋዊ ዮሴፍ ሽማግሌ ሲሆን በብዙ ጎዳና መልካምነቱ ተመስክሮለት አማናዊት ታቦት ድንግል ማርያምን ለማገልገል ተመርጧል:: እመቤታችንን በአደራ እንዲጠብቃት ለአረጋዊ ዮሴፍ ተሰጠች። እንደዚሁም ሁሉ ወንጌላዊ ዮሐንስ ምንም ወጣት ቢሆን በቅቶ ስለተገኘ ለአረጋዊ ዮሴፍ የተሰጠችው ድንግል ማርያምን ለማገልገል እንደ ዮሴፍ ሁሉ እርሱም ከመስቀሉ ሥር በመገኘት በአደራ ተቀዘላት፡፡ ይህ ጸጋን ለመቀበል በቅቶ መገኘት እንጂ ዕድሜ ወሳኝ አለመሆኑን ያስረዳል። ዮሐ19፥26-27 ማቴ 1፥18-25
  ወንጌላዊ ዮሐንስ ለኛ ለወጣቶች መመኪያችን ነው:: በወጣትነት ድንግል ማርያምን አስተናግዷልና። በክርስትና እምነት ከድንግል ማርያም ጋር የሚመሳሰልና የሚተካከል ሀብትም ጸጋም የለም፡፡ ታዲያ ድንግል ማርያምን ለመቀበል የበቃ ሌሎች ነገሮችን ከመቀበል ምን ያግደዋል፡፡ ይህን ሲባል ግን በቅቶ ከተገኘ እንጂ ካልበቃ ሊሆን አይችልም:: በአረጋዊ ዮሴፍ ዘመን ብዙ አረጋዊያን ነበሩ ነገር ግን በትሮቻቸው ተሰብስቦ ቢጸለይበት የቅዱስ ዮሴፍ በትር እንደ አሮን በትር ለምልማ በመገኘቷና በላይዋም «ኦ! ዮሴፍ ዕቀባ ለማርያም : ዮሴፍ ሆይ ማርያምን ጠብቃት» የሚል ጽሑፍ ተገኝቶ ድንግል ማርያምን ወደ ቤቱ ወስዷታል፡፡ (የሕዝቅኤል ትርጓሜ) በዮሐንስ ወንጌላዊም ዘመን ብዙ ወጣቶች ነበሩ ነገር ግን እመቤችንን እንደ ዮሐንስ በአደራ ለመቀበል አልታደሉም። እንዲሁም በዘመናችን ብዙ ወጣቶች አሉ ሁሉም ለቁርባን፣ ለተክሊልና ለክህነት አይበቁ ይሆናል:: ነገር ግን ለዚህ ሁሉ ግን የሚበቁ ወጣቶች መኖራቸው መዘንጋት የለበትም፡፡
  ጸጋ እግዚአብሔር በዕድሜ የሚሰጥ ቢሆን ኖሮ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም «ከሴቶች መካከል ተለይታ የተባረከች» ለመሆን እንዴት ትችል ነበር? ነገር ግን ጸጋ እግዚአብሔር በዕድሜ ባለመሆኑ ምልዕተ ጸጋ ለመሆን በቃች። ምንም እንኳን በዕድሜ ትንሽ ብላቴና ብትሆን መጽሐፈ መነኮሳት እንዳለ «ብፅዕት ማርያምን በዕድሜ ትንሽ መሆኗ ከሴቶች መካከል ተለይታ ቡርክት ለመሆን አልከለከላትም» ፊል ክፍል4 ተስ47 በዚህም ምክንያት ድንግል ማርያም «ምክሐ ደናግል» ብቻ ሳይሆን «ኃይለ ወራዙት»ም ትባላለች፡፡ ድንግል ማርያም «ኃይለ ወራዙት» ናት ማለት ለወጣቶችም ሆነ ለአረጋዊያን የወጣትነታቸው ኃይል እርሷ ናት ማለት ነው:: (መልክዐ ቁርባን)
  እንዲሁም ወጣቶች በሚገባ ከኖሩ ከአረጋዊያን ተሽለው ሊገኙ ይችላሉ:: ይህም «ወራዙትኒ እመኒ ሕፃናት እሙንቱ ወተጸምዱ ለሥርዓተ ንጽሕ ይኄይሱ ፈድፋደ እም አዕሩግ፤ ወጣቶች ምንም ታዳጊዎች ቢሆኑ ንጽሕናን ጠብቀው ከኖሩ ፈጽመው ከአረጋዊያን ይበልጣሉ» በማለት ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በተናገረው ቃል ይታወቃል፡፡ ትንሽ ዘመን ኖሮ በብዙ ዘመን የሚገኝ ዕውቀትን ገንዘብ ያደረገ ብልህ ወጣት ብዙ ዘመን ኖሮ ዕውቀት በማጣት እንደ ሕፃን ከሚኖር ሽማግሌ እንደ ምን አይበልጥ?
  ቅዱሳት መጻሕፍትም በዚህ ሐሳብ ተስማምተዋል። ጠቢቡ ሰሎሞን «ክብረ ርእስ አኮ በብዝኃ መዋዕል ፤ መከበር በዘመን ብዛት አይደለም» በማለት ሲናገር ፤ ሲራክ ደግሞ


.                   ምዕራፍ ሁለት
                     የልጅ ዐዋቂ

  ወጣቶች በመልካም አኗኗር ከኖሩ የልጅ ዐዋቂ ይባላሉ፡፡ ወጣቶች ከፈቀዱ አረጋዊ መሆንና አረጋዊ ከደረሰበት ጸጋና ክብር መድረስ ይችላሉ:: ወጣት የሽማግሌ ሥራ መሥራት ይቻለዋልን? የሚል ቢኖር ከሽማግሌዎች ወገን የወጣቶችን ሥራ በመሥራት ጸንተው የሚኖሩ ብዙ እንዳሉ ሁሉ ፣ የሚል መልስ ተጽፎ ይገኛል፡፡ ተግሣጽ ዘዮሐ አፈ 7
  ነጭ ጉተና (ፀጉር) ከመኮነን እንደማያድን ሁሉ በክርስትና መልካም ሥራን እንጂ ነጭና ጥቁር ፀጉርን ማበላለጥ የለም። አረጋዊም ሆነ ወጣት በቅተው ከተገኙ ለማንኛውም ክብር ይበቃሉ፡፡


"ቅድስት"
በዲያቆን ዘማሪ ቀዳሜጸጋ ዮሐንስ

በኩር ናት የበዓላት
ኑ ከፍ ከፍ እናድርጋት
በእርሷ ደስ ይበለን
በሰንበተ ክርስቲያን

አዝ...
በዝማሬ እንበርታ በገናውን እንያዝና
መልካም ስራ ሚሠራባት ሰንበት ቅድስት ናትና
ከጨለማ ብርሀን ከመገዛት ነጻነት
እግዚአብሔር ይህን ሰጠን ደስ ይበለን በሰንበት

አዝ...
ለአብርሃም ተገልጣለች ለሙሴም በደብረ ሲና
በነቢያት የታወቀች ሰንበት ደሀራዊት ናትና
በሳምንቱ ሠለጠነች ተሰበከች በሀዋሪያት
ሀሌሉያ እለተ ሰንበት ተሰጠችን ልናርፍባት

አዝ...
በእልልታ እንሞላ እንደነቢዩ አሳፍ
በከበረች የሰንበት ቀን ኑ ለቅኔ እንሰለፍ
በመቅደሱ ናቸውና ቅዱስነት እና ግርማ
ቅዳሴአችን ይሰማልን ከምድር እስከ ኢዮር ራማ

አዝ...
እግዚአብሔር አብ የባረካት እግዚአብሔር ወልድ የቀደሳት
ከእለታት ሁሉ መርጦ መንፈስ ቅዱስ ከፍ ያረጋት
በእርሧ ሀሴት እናድርግ እናክብራት እንድንከብር
ከደጀ ሰላሙ ታዛ ከመቅደሱ እንሰብሰብ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox




፣በዕዳ የሚጠየቅም ሆነ የሚጠይቅ ሁለቱም በአንድነት ቅዱስ ቃሉን ሲሰሙ ዋሽቶ የሰው ዕዳ ያልከፈለውም ተጸጽቶ ይክሳል ወራት ብሶበት ቀን ጥሎት መክፈል ላልቻለውም ምህረት ይቅርታ እንዲያገኝ ቅዱስ ቃሉ ጸሎቱ ምክንያት ይሆነዋል ። በዚህም የተነሳ ሁለቱም ወገኖች በክፉ ከመፈላለግ ይልቅ የይቅርታ የምህረት ሰዎች ይሆናሉ። በዚህች በኵረ በዓላት በምትሆን በቅድስት በዕለተ ሰንበት የምእመናን መንፈሳዊ ሕይወት ይባረካል ይቀደሳል በዚህ ታሳቢነት ዕለቱም ዕለተ ቅድስና መሆኑን ለማጠየቅ ቅድስት ተብሏል ።

ቅድስና የተፈቀደልን ብቻ ሳይሆን የታዘዝነውም ጭምር ነው “እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ቅዱስ ነኝና እናንተ ቅዱሳን ሁኑ” (ዘሌ.፲፱፥፪) በዚህ ኃይለ ቃል ውስጥ ቅድስና እንደ ፈቃድም እንደ ትእዛዝም ሆኖ ተሰጥቶናል፤ እግዚአብሔር ያልፈቀደውን ነገር አድርጉ ሁኑ ብሎ አያዝም።የቅድስና ሕይወት መሰረቱ የእግዚአብሔር ፈቃድና ትእዛዝ ሆኖ ሳለ ለመቀደስ የእኛ መሻት መፈለግ ዝንባሌም ወሳኝ ነው። ለዚህም ነው ሐዋርያው እንዲህ ሲል የጻፈልን “ትቀደሱም ዘንድ ፈልጉ፥” (ዕብ. ፲፪፥፲፬) ምንም አንኳን ቅድስና የተፈቀደና የታዘዘ ቢሆንም የውዴታ እና የነጻ ፈቃድ ውጤት እንጂ የምንገደድበት አይደለም፡፡እግዚአብሔር ፍቅሩ ገብቶን ወደን እና ፈቅደን በፈቃዱ እና በትእዛዙ ስንመራ ያስደስተዋል እንጂ ተገደን ፈርተን ተንቀጥቅጠን እንድንገዛለት አይወድም፡፡

ወደ ቀደመ ነገራችን ስንመለስ ዕለተ ሰንበትም ቅድስት መባሏ ከላይ ያብራራነውን መሰረታዊ ሃሳብ በተከተለ መልኩ ነው። ዕለቲቱ ቅድስት መባሏ ዋና ዓላማ በሰዎች እና በእግዚአብሔር መካከል ለቅድስና ሕይወት ምልክት ማስታወሻ እንድትሆን ነው። በባህሪው ቅዱስ የሆነ አምላክ ዓለምን የማዳን ስራውን የጀመረበትን ጽንሰቱን እንዲሁም የማዳን ስራውም አጠናቆ ሙስና መቃብርን አጥፍቶ ዘላለማዊ ሕይወትን ያበሰረበትን ትንሳኤውን የምናስብበት በመሆኑ የዕለቱ ቅድስና የፈጣሪን ቅዱስ ተግባር የምናደንቅበት ከማንኛውም የሥጋ ሥራ ተለይተን የዋለልን ውለታ ከፍ ከፍ እያድረግን እርሱን የምናመሰግንበት ዕለት ነው። ይህም እኛን ወደ በለጠ የቅድስና ሕይወት የሚያሸጋግረን ከመሆኑም በላይ የእግዚአብሔርን ጥልቅ ፍቅር በየጊዜው እንድናስብና በፍቅሩም እንድንኖር ያግዘናል፡፡
©ተሚማ

ምስባኩ፦ መዝ ፺፭፥፭
"እግዚአብሔርሰ ሰማያተ ገብረ አሚን ወሠናይት ቅድሜሁ ቅድሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ"
"እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ሠራ ምስጋና ውበት በፊቱ ቅዱስነትና ግርማ በመቅደሱ ውስጥ ናቸው"

በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ መልእክታት
-፩ኛ ተሰ ፬፥፩-፲፫
-፩ኛ ጴጥ ፩፥፲፫ እስከ ፍጻሜ
-የሐዋ ሥራ ፲፥፲፯-፴

ወንጌሉም፦ ማቴ ፮፥፲፮-፳፭

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox


ቅድስት
የዐብይ ጾም ሁለተኛ እሑድ(ሳምንት)


ቅድስት የሚለው ቃል ግሱ “ቀደሰ” ሲሆን "ለየ፣ አከበረ፣ መረጠ" የሚል ትርጉም ይይዛል።
ቅድስት ማለት የተለየች፣ የተመረጠች፣ የከበረች ማለት ነው። ቅዱስ የሚለው ቃል እንደየአገባቡ ለፈጣሪም ለፍጡርም ያገለግላል። ለፈጣሪ ሲነገር እንደ ፈጣሪነቱ ትርጉሙ ይሰፋል ይጠልቃል ለፍጡር ሲነገር ደግሞ እንደ ፍጡርነቱ እና እንደ ቅድስናው ደረጃ ትርጉሙ ሊወሰን ይችላል።

እግዚአብሔርን ቅዱስ ስንል የባህሪይው የሆነ፣ ኃጢአት የማይስማማው ፣ ለቅድስናው ተወዳዳሪ ተፎካካሪ የሌለው፣ ወደር የማይወጣለት፣ ዘለዓለማዊ የሆነ ማለታችን ሲሆን ፍጡራንን ግን ቅዱሳን ስንል ቅድስናቸው የጸጋ የሆነ፤ ከእግዚአብሔር ያገኙት፤ እንደነጭ ልብስ ጽድቁም ኃጢአቱም እንደ ዝንባሌአቸው የሚስማማቸው፤ ለቅድስናቸው ማዕረግ ደረጃ የሚወጣለት እንደ ገድል ትሩፋታቸው መጠን ሊጨምርም ሊጎድልም የሚችል ማለታችን ነው። ከፍጡራን መካከል ለእግዚአብሔር የተለዩ ሁሉ በጸጋ የቅድስናው ተሳታፊ ሊሆኑ ይችላሉ። መላእክት፣ ሰዎች፣ መካናት፣ ዕለታት፣ አልባሳት፣ ንዋያት ሁሉ ለእግዚአብሔር እስከተለዩ ድረስ ከቅድስናው በረከት ይሳተፋ እንደየደረጃቸው ቅዱሳን ተብለው ይጠራሉ።

በዚህ ዕለት ስለ ቅድስና እንዲሁም ዘወትር በዕለተ ሰንበት ከሌሎች ቀናት በተለየ ሁኔታ ለጽድቅ ስራ እንድንበረታ፣ ለቅድስና እራሳችንን እንድንለይ ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ይሰበካል ይነገራል። የሚዘመረውም መዝሙር “ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ ወንግርዎሙለአሕዛብ ምግባሮ ሀቡ ስብሐተ ለስሙ አክብሩ ሰንበተ ተገበሩ ጽድቀ ዝግቡ ለክሙ መዝገበ ዘበሰማያት ኀበ ፃፄ ኢያማስኖ ወኢይረክቦ ሰራቂ ድልዋኒክሙ ንበሩ ዘበላዕሉ ጸልዩ ኀበ ሀሎ ክርስቶስ፤ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ስሙንም ጥሩ፤ ሥራውንም ለአሕዛብ ንገሯቸው፤ ለስሙም ምስጋናን አቅርቡ፤ ሰንበትን አክብሩ፤ እውነትንም አድርጉ፤ ብል የማያበላሸው ሌባም የማያገኘው በሰማያት ያለ መዝገብን ለእናንተ ሰብስቡ፤ ተዘጋጅታችሁም ተቀመጡ፤ ክርስቶስ ወዳለበት ወደላይ አስቡ፡፡”

በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶ ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ እንደ ዘመረልን በተለይ ሰንበት ነገረ እግዚአብሔር በተለየ ሁኔታ የሚዘከርባት፤ ኅሊናችን ከምድራዊው ሃሳብ ወጥቶ ወደ ሰማይያዊው የሚነጠቅባት፤ ለቅድስና የተለየች ቅድስት ዕለት መሆኗን ይጠቁማል። በቅዱስ መጽሐፍም “የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ” (ዘፀ. ፳፥፰) ተብሏል፡፡ የሰንበትን ቀን አስቀድሞ የቀደሰ የባረከ እራሱ እግዚአብሔር ነው "እግዚአብሔርም ሰባተኛውን ቀን ባረከው ቀደሰውም እግዚአብሔር ሊያደርገው ከፈጠረው ሥራ ሁሉ በእርሱ ዐርፎአልና"(ዘፍ.፪፥፫) እንግዲህ “የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ” የተባለው እግዚአብሔር አስቀድሞ የባረከውን የቀደሰውን እኛ ድጋሚ የምንቀድስ የምንባርክ ሆነን ሳይሆን በዕለተ ሰንበት እራሳችንን በተለየ ሁኔታ ለቅዱስ ተግባር እንድንለይ ለሥጋችን ከምንፈጽማቸው ተግባራት ይልቅ ለተግባረ ነፍስ እንድናደላ ያስረዳናል። ምንም እንኳን ለስጋችን ስንባክን ጊዜ ቢያጥረን በዕለተ ሰንበት ግን ቅዳሴ ከማስቀድስ ቅዱስ ቃሉን ከመስማት ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ከመቀበል እንዳናስታጉል በሥርዓት ቤተ ክርስቲያን ታዝዘናል፡፡

ሊቃውንቱ በፍትሐ ነገሥት "ተጋብኡ ኩሎ ዕለት ኀበ ቤተ ክርስቲያን ወፈድፋደሰ በዕለተ ሰንበት ወበበዓላት ወበዕለተ ትንሣኤ ዘውእቱ ዕለተ እሑድ፤ ሁልጊዜ በቤተ ክርስቲያን ተሰብሰቡ፤ ይልቁንም በዕለተ እሑድ፣ በዕለተ ቀዳሚት፣ በጌታ በዓላት ወደ ቤተ ክርስቲያን ተሰብሰቡ፡፡” (ፍትሐ ነገሥት ገጽ ፪፻፶፬) ብለው ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ከሌሎች ቀናት በተለየ ሁኔታ ትኩረት የምንሰጥበት የምንቀደስበት ዕለት ቅድስት ሰንበት እንደሆነች ተናግረዋል። ሐዋርያዊው ቅዱስ አትናቴዎስም በቅዳሴው ላይ ሰንበት የተቀደስች እና ሕይወታችን እንዲቀደስባት የተለየች ቀን መሆኗን ሲያስረዳ እንዲህ ይላል፡፡ “ወንበል ዛቲ ዕለት እንተ ገብረ እግዚአብሔር ንትፈሣሕ ወንትሐሰይ ባቲ፤ ይህች ዕለት እግዚአብሔር የሠራት ያከበራት ዕለት ናትና በእርሷ ፈጽሞ ደስ ይበለን” ሰንበት ለክርስትያኖች ለመንፈሳዊ ደስታ የተለየች ቀን ናት። የመንፈሳዊ ደስታ ምንጩ በነፍስ የሚገኝ መንፈሳዊ በረከት ነው። ሰው የኃጢአትን ሸክም በንስሃ ሲያራግፍ፤ ነፍሱ በጸጋ እግዚአብሔር ስትቃኝ የሚሰማውን ደስታ በሌላ በምንም መንገድ ሊያገኘው አይችልም። ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ሰንበት ቅድስትና ለቅድስና የተለየች ቀን መሆኗን ያስተማረን አስቀድሞ በነብያት ትንቢት ያናግር የነበረ መንፈስ ቅዱስ አነሳስቶት ነው።

ስለ ሰንበት መለየትና መቀደስ እንዲሁም የመንፈሳዊ ሐሴት ቀን ለመሆኗ ነቢዩ ቅዱስ ዳዊት መዝሙሩ እንዲህ ብሎ ነበር “እግዚአብሔር የሠራትቀን ይህች ናት፤ ሐሤትን እናድርግ፥ በእርስዋም ደስ ይበለን።” (መዝ. ፻፲፯፥፳፬) ቅዱስ ዮሐንስም ራእዩ ሰንበት የጌታ ቀን ስለመሆኗ እንዲህ ይላል “በጌታ ቀን በመንፈስ ነበርሁ” (ራእ. ፩፥፲) ሰንበት የእኛ ቀን ሳትሆን ለጌታችን የምንሰራባት የምንለይባት ፣ የምንቀደስባት፣ ነገረ እግዚአብሔርን የምንዘከርባት የጌታ ቀን ናት። ለቅድስና የተለየች ቅድስት ቀን ናት ። በተለይ የክርስቲያን ሰንበት እሑድ “በኵረ በዓላት” ትባላለች በኵር ታላቅ እና መጀመርያ ማለት ነው፤ የመዳናችን መሰረት የተወጠነባት የጌታ የጽንሰቱ ቀን ዕለተ ሰንበት ናት፤ የመዳናችን ማረጋገጫ፣ የእምነታችን መሰረት ፣ የበዓላት ሁሉ ዓቢይ ትንሳኤው የተፈጸመው በዕለተ ሰንበት ነው። እንግዲህ በዚች ቅድስት ዕለት፥ ለቅድስና በተለየች ዕለትስ ሥጋውንም ነፍሱንም በሚያርያረክስ ተግባር የተሰማራስ ለነፍሱ ምን ዋስትና ይኖረዋል?

ቅድስት በተባለች በሰንበት እሑድ ማንም በምንም ምክንያት ወደ ቤተ እግዚአብሔር ከመሄድ እንዳያስታጉል በስርአተ ቤተክርስትያን ተቀምጦልናል። ሌላው ቀርቶ በዕዳ በብድር በቀረጥ በግብር በአስራት በበኩራት ይሉኝታ ፈርቶ ማንም ቅድስት በምትባል በእሑድ ሰንበት ቅዳሴ እንዳያስታጉል ማንም ማንንም በዚህች ቅድስት ዕለት ምንም አይነት እዳ እንዳይጠይቅ ታዟል።

“ወኢይኅሥሥ መኑሂ በይእቲ ዕለት ንዋዮ እምካልኡ ወኢይጽሐቅ አሐዱሂ እምእመናን በእንተ ኃሥሠ ዕዳ ። አው ተጻልኦ አው በዘይመስሎ ለዝንቱ። ወይሑሩ ቦቱ ኩሉሙ ሰብእ ኀበ ቤተ ክርስቲያን ወይምጽኡ ኲሉ ለለ ፩ ፩ እምእመናን ኅቤሃ በንጽሕ ወበትህትና ዘእንበለ ፍርሃት እምነ መኮንን ወእም በዓለ ዕዳ አው እምፈታሒ አው ዘይመስሎ። ወእመሰ ተሀበለ ፩ሂ ክርስቲያን ምክዕቢተ ይፍዲ፤ ከምእመናን ወገን አንድስ እንኳ በእሑድ ቀን ለገንዘብ መትጋት፤ገንዘቤን አምጣ ብሎ መጣላት፣ ዋስ መያዝ አይገባውም ። ሁሉም ምእመናን ወደ ቤተክርስቲያን በንጽሕና በትሕትና ሆነው ይምጡ እንጂ ። ዳኛ ግብሬን፣ አበዳሪ ብድሬን ፣ኤጲስቆጶስ ዐሥራት በኵራት ፣ ነጋ ድራስ ቀረጥ አምጡ ይሉናል ብለው ሳይፈሩ ይምጡ። ከነጋድራሶች አንዱ እንኳ ወደ ቤተክርስትያን ከሚሄዱ ሰዎች ቀረጥ ይቀበል ዘንድ የድፍረት ሥራ የሠራ ቢሆን እጽፍ አድርጎ ይክፈል።” (ፍትሐ ነገሥት ገጽ ፪፻፶፰-፪፻፶፱) ቅድስት ቤተክርስቲያን ይህን ያህል ጥንቃቄ የምታደርገው ሰዎች በተለያየ ምክንያት ከቤተ እግዚአብሔር እንዳይርቁ ከዛም አልፎ ተበዳይም ሆነ በዳይ


ይትበሃሉንና ቃሉን አነበብነው:
ሐተታውንና ምሥጢሩን ተማርነው:
በቅዱሳን ህይወት ወንጌሉን አየነው።[፪]


@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox



Показано 20 последних публикаций.