ምዕራፍ ስምንት
ድንግልና ምንድር ነው?
ድንግል የሚለው ቃል «ተደንገለ፤ ተጠበቀ» ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙ «መጠበቅ» ማለት ነው፡፡ እንደ አገባቡም ፍቺው ሊለያይ ይችላል፡፡ ለምሳሌ:- ድንግል የሚለውን ቃል ለዕቃ የሰጠን እንደ ሆነ ገና ከማምረቻ የወጣ፣ ምንም ያልተሠራበት፣ ያላደፈ ያልጎደፈ፣ ያላረጀ ያላፈጀ፣ ያልተቀላቀለ ማለት ይሆናል፡፡ ድንግል መሬት ሲባል ደግሞ ለምነቱ እንደ ተጠበቀ ያለ፣ ለእርሻ ያልዋለ ወይም ያልታረሰ፣ ያልተቆፈረ፣ ዘር ያላረፈበት እንደ ተፈጠረ ያለ መሬት ማለት ነው፡፡
ድንግል የሚለው ቃል ለሰው ሲነገር ደግሞ ወንድ የማታውቅ (ከወንድ ጋር ሩከቤ ፈጽማ የማታወቅ)፣ ጥብቅ፣ ልጃገረድ ሴት ወይም ሴትን በምንጣፍ ተገናኝቶ የማያውቅ ወንድ ማለት ይሆናል፡፡ በተጨማሪም የተፈጥሮ ንጽሕናቸውን የጠበቁ ንጽሐ ጠባይ ያላደፈባቸው ወንድና ሴት ማለት ነው:: ዘፍ24፥16፣ ራእይ14፥4
ብዙ ጊዜ ይህ ቃል ሲፈታና በዐረፍተ ነገርም ሲገባ የምንመለከተው የመጨረሻውን አስተያየት በመያዝ ወንዶችና ሴቶች የሰው ልጆችን ወክሎ ነው፡፡ ስለዚህ ከላይ በተሰጠው ትንታኔ መሠረት ድንግልና ንዑስ ሕዋስን ወይም አካልን ብቻ ሳይሆን አንድ ድርጊት መፈጸም አለመፈጸሙን የሚያመለክት ቃል ይሆናል ማለት ነው፡፡
በተጨማሪም ይህ ቃል ለመንግሥታት፣ ለሕዝብ፣ ለሀገር፣ ለምእመናን ምሳሌ በመሆን በመጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ጊዜ ተጠቅሷል፡፡ ኢሳ 23÷12 ፣37÷22፣47÷1፣አሞ 5÷2፣ኤር 18÷13፣2ኛ ቆሮ 11÷2
ድንግልናና ማኅተመ ድንግልና
በሰው ልጆች ዘንድ ሩካቤ ካለ ዘር መቀበል፣ ማቀበልና ሰስሎተ ድንግልና (የድንግልና መወገድ) መኖሩ የታወቀ ነው:: ሆኖም ይኽ ስለ ታወቀ ብቻ ሩካቤ ከተፈጸመ ማኅተመ ድንግልና አይኖርም ድንጋሌ ሥጋ ካለ ደግሞ ሩካቤ አልተፈጸመም በማለት ድምዳሜ ላይ መድረስ አይቻልም፡፡ ምክንያቱም ብዙ ጊዜ ሩካቤ አድርገው ድንጋሌ ሥጋቸው ያልተወገደ እንደውም ማኅተመ ድንግልናቸው ሳይገሠሥ እስከ መፅነስ የደረሱ ብዙ ሴቶች ስላሉ ለዚህ ምስክር ናቸው። ከዚህም በተጨማሪ ተፈጥሮአዊ ጽንዐ ድንግልናቸው በሩካቤ ብቻ ሊገሠሥ የማይቻል እየሆነ በቀዶ ጥገና ሕክምና ማኅተመ ድንግልናቸው እንዲወገድ የሚደረግላቸው ብዙ ሴቶች አሉ፡፡
ይህ ከሆነ ድንግል የሚለው ቃል ብቻውን የአንዲት ሴትን ትክክለኛ ድንግልነት ላይገልጽ ይችላል ማለት ነው፡፡ የሚገልጽ ቢሆን ኖሮ ያለ ምንም ተጨማሪ ቃላት ለእመቤታችን በተነገረ ነበር፡፡ ነገር ግን ስለ እመቤታችን አምላክን መፅነስና መውለድ ሲነገር በድንግልና ፀንሳ ወለደችው ከማለት በተጨማሪ «ያለ ሩካቤ፣ ያለ ዘር፣ ያለ ሰስሎተ ድንግልና›› ፀንሳ ወለደችው ማለት በብዙ መጻሕፍት የተለመደ አገላለጽ ነው፡፡ ለምሳሌ፡- «ወይእቲ ንጽሕት እምነ ሠለስቱ ግብራት ዘውእቶሙ ዘርዕ፣ ወሩካቤ፣ ወስስሎተ ድንግልና እለ ሥሩዓን በዕጓለ እመ ሕያው ወእሙራን ቦሙ» - «እርሷም በሰው ልጆች ዘንድ ከታወቁት ከሦስቱ ግብራት የተጠበቀች ናት እነርሱም ሩካቤ ዘር መቀበልና፣ የድንግልና መወገድ ናቸው፡፡» ይላል፡፡ (ትርጓሜ ውዳሴ ማርያም) ስለዚህ ሩካቤና ሰስሎተ ድንግልና የተለያዩና ራሳቸውን የቻሉ ተግባራት ተደርገው መታየት አለባቸው። አንዲትን ሴት ማኅተመ ድንግልና ስላላት ብቻ «ሩካቤ አድርጋ አታውቅም» ወይም ሩካቤ ስላደረገች «ማኅተመ ድንግልና ሊኖራት አይችልም» ብሎ ድምዳሜ ላይ መድረስ አለመቻሉን እንረዳለን፡፡ እመቤታችን ግን «ድንግል» የሚለው ቃል ከሚገልጸው በላይ «ፍጽምት» መሆኗን ተያይዘው በተጠቀሱት ተጨማሪ ቃላት እንረዳለን፡፡ ድንግል ማርያም በሕሊናዋም በሥጋዋም ፍጹም ድንግል የሆነች «ምክሐ ደናግል>> ናት፡፡
ማኅተመ ድንግልና በሩካቤ ሥጋ ጊዜ የሚጠፋ እንደ መሆኑ መጠን በቀጥታ በሥጋ ድንግል ከመሆንና ካለመሆን ጋር መዛመዱ ግልጽ ቢሆንም አንዳንድ ጊዜ ግን ከላይ ከተጠቀሰው በተጨማሪ ማኅተመ ድንግልናን «ከድንግልነት» ጋር ለይተን ለመመልከት የምንገደድበት ሁናቴ ይኖራል፡፡
ለምሳሌ ወንዶች እንደ ሴቶች ተጨባጭና ጉልህ የድንግልና ምልክት ስለሌላቸው ከሴት ጋር ሩካቤ ፈጽመው የማያውቁ ሆነው ሳለ ደናግል አይደሉም ለማለት አይቻልም:: እንደዚሁም ሁሉ ሩካቤን ፈጽመው የማያውቁ ሴቶች ሲወለዱ ጀምሮ ማኅተመ ድንግልና የሌላቸው ሊሆኑ ይችላሉ:: ወይም ከጊዜ በኋላ በክባድ የአካል እንቅስቃሴ፣ በአደጋ፣ በሕክምና ወይም በዕድሜ ብዛት ምክንያት ማኀተመ ድንግልና ሊፈርስባቸው ይችላል:: እንዲህ ያሉ ሴቶች ማኅተመ ድንግልናቸውን ቢያጡም ሩካቤ ፈጽመው እስካላወቁ ድረስ ደናግል መባላቸው የተጠበቀ ነው:: ምክንያቱም ድንግልናና ማኅተመ ድንግልና በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ ተለያይተው ስለሚታዩ ነው::
በሌላ አቅጣጫ ስንመለከት ወንዶች ሩካቤ ፈጽመው ሳለ እንደ ሴቶች የሚገሠሥ ማኅተመ ድንግልና ስለሌላቸው ድንግልናቸው አልፈረሰም እንደማይባል ሁሉ ሴቶች ሩካቤ ሥጋ እየፈጸሙ በልዩ ልዩ ምክንያት ማኅተመ ድንግልናቸው ባይገሠሥም መደበኛ ሩካቤ እስከ ፈጸሙ ድረስ ደናግል ሊባሉ አይችሉም:: ለምሳሌ:- የሚያይ የሚመስል ዓይን እያላቸው በመፍዘዙ ምክንያት የማያዩ ሰዎች የዓይን ምልክታቸው (ዓይን የሚባው ሕዋስ ወይም መልክ) ጨርሶ ስላልጠፋ ብቻ ዓይን አላቸው ይባላልን? እንደዚሁም ሁሉ ሩካቤ ፈጽመው ሳለ ማኀተመ ድንግልናቸው ባለመጥፋቱ ብቻ ደናግል ሊባሉ አይቻልም፡፡
አንዲትን ሴት ድንግል የሚያሰኛት ሥራዋና ዝንባሌዋ ብቻ ነው:: ማኅተመ ድንግልናዋ ስላልተወገደ ብቻ ወይም እርሷ ድንግል መሆን ስለምትፈልግ ወይም «ጳጳስ››ም ሆነ «ባሕታዊ» ጸሎት ስለ ደገመላት ድንግል መሆን አትችልም:: ከዚህ በታች የተጠቀሰው ኃይለ ቃል ይህንን ሐሳብ የሚያጎላ ነው፡፡ ‹‹ወኢያንብር ዕደ ላዕለ ድንግል አላ ምሥጢራ ባሕቲታ ትሬስያ ድንግለ›› የዚህ ዐረፍተ ነገር ትርጓሜ ‹‹ድንግል ናት ብሎ በአንብሮተ ዕድ አይሹማት (ድንግልና) ሾሜሻለው አይበላት:: ፈቃዷ ብቻ ድንግል ያደርጋታል እንጂ የሰው ፈቃድ ድንግል አያደርጋትምና፡፡» የሚል ነው፡፡ (ፍትሐ ነገሥት መንፈሳዊ)
የማኅተመ ድንግልና ስያሜዎች
ማኅተመ ድንግልና ሴት ከወንድ ጋር ሩካቤ አድርጋ አለማወቋን የሚያስረዳ የሥራዋ መገለጫ የእኗኗሯ መታወቂያ ልዩ የተፈጥሮ ምልክትና የድንግልናዊ ኑሮዋ ዘውድ ነው:: ይህ መለኮታዊ ማኅተም በሴቶች አፈ ማኅፀን ቀለበት በሚመስል ስስ ሥጋነት በጉልህ ይታወቃል፡፡ ድንግልና ጥቅሙን፣ ምሥጢሩን፤ ምሳሌውን የሚያመለክቱ ልዩ ልዩ ስያሜዎች አሉት:: በተለያዩ ቅዱሳት መጻሕፍት የተጠቀሱት እነዚህ የድንግልና መጠሪያዎች በርካታ ቢሆኑም ሦስት ያህሉ ብቻ ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል::
ሀ. ማኅተመ ድንግልና «ክንፈ ድንግልና» ተብሎ ይጠራል፡፡ በዚህ ዓለም ያለ ስጋት ለመንቀሳቀስ የሚያስችል የንጽሕና ክንፍ ነውና፡፡ አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ «ኦ ወለተ እስራኤል መኑ ቀረጸ አክናፈ ድንግልናኪ› በማለት የተናገረው ቃለ መጠይቅ ከላይ መኅተመ ድንግልና ‹ክንፈ ድንግልና (የድንግልና ክንፍ)» ይባላል በሚል ለተገለጸው ሐሳብ ብቁ ማስረጃ ይሆናል፡፡ ከዚህ ዐረፍተ ነገር እንጻር ለተመለከተው ድንግልናቸውን ያልጠበቁ ሰዎች በሙሉ ክንፍ የሌላትን ወፍ ይመስላሉ::
ለ. «ሕጓን ወሰደው› እንዲሉ ድንግልና ‹‹ሕግ›› ይባላል:: ሕግ የተባለበት ምክንያት «አታመንዝር» የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ሕግ መፈጸምና - አለመፈጸምን የሚያስታውቅ የሕግ ምልክት በመሆኑ ነው፡፡
ድንግልና ምንድር ነው?
ድንግል የሚለው ቃል «ተደንገለ፤ ተጠበቀ» ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙ «መጠበቅ» ማለት ነው፡፡ እንደ አገባቡም ፍቺው ሊለያይ ይችላል፡፡ ለምሳሌ:- ድንግል የሚለውን ቃል ለዕቃ የሰጠን እንደ ሆነ ገና ከማምረቻ የወጣ፣ ምንም ያልተሠራበት፣ ያላደፈ ያልጎደፈ፣ ያላረጀ ያላፈጀ፣ ያልተቀላቀለ ማለት ይሆናል፡፡ ድንግል መሬት ሲባል ደግሞ ለምነቱ እንደ ተጠበቀ ያለ፣ ለእርሻ ያልዋለ ወይም ያልታረሰ፣ ያልተቆፈረ፣ ዘር ያላረፈበት እንደ ተፈጠረ ያለ መሬት ማለት ነው፡፡
ድንግል የሚለው ቃል ለሰው ሲነገር ደግሞ ወንድ የማታውቅ (ከወንድ ጋር ሩከቤ ፈጽማ የማታወቅ)፣ ጥብቅ፣ ልጃገረድ ሴት ወይም ሴትን በምንጣፍ ተገናኝቶ የማያውቅ ወንድ ማለት ይሆናል፡፡ በተጨማሪም የተፈጥሮ ንጽሕናቸውን የጠበቁ ንጽሐ ጠባይ ያላደፈባቸው ወንድና ሴት ማለት ነው:: ዘፍ24፥16፣ ራእይ14፥4
ብዙ ጊዜ ይህ ቃል ሲፈታና በዐረፍተ ነገርም ሲገባ የምንመለከተው የመጨረሻውን አስተያየት በመያዝ ወንዶችና ሴቶች የሰው ልጆችን ወክሎ ነው፡፡ ስለዚህ ከላይ በተሰጠው ትንታኔ መሠረት ድንግልና ንዑስ ሕዋስን ወይም አካልን ብቻ ሳይሆን አንድ ድርጊት መፈጸም አለመፈጸሙን የሚያመለክት ቃል ይሆናል ማለት ነው፡፡
በተጨማሪም ይህ ቃል ለመንግሥታት፣ ለሕዝብ፣ ለሀገር፣ ለምእመናን ምሳሌ በመሆን በመጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ጊዜ ተጠቅሷል፡፡ ኢሳ 23÷12 ፣37÷22፣47÷1፣አሞ 5÷2፣ኤር 18÷13፣2ኛ ቆሮ 11÷2
ድንግልናና ማኅተመ ድንግልና
በሰው ልጆች ዘንድ ሩካቤ ካለ ዘር መቀበል፣ ማቀበልና ሰስሎተ ድንግልና (የድንግልና መወገድ) መኖሩ የታወቀ ነው:: ሆኖም ይኽ ስለ ታወቀ ብቻ ሩካቤ ከተፈጸመ ማኅተመ ድንግልና አይኖርም ድንጋሌ ሥጋ ካለ ደግሞ ሩካቤ አልተፈጸመም በማለት ድምዳሜ ላይ መድረስ አይቻልም፡፡ ምክንያቱም ብዙ ጊዜ ሩካቤ አድርገው ድንጋሌ ሥጋቸው ያልተወገደ እንደውም ማኅተመ ድንግልናቸው ሳይገሠሥ እስከ መፅነስ የደረሱ ብዙ ሴቶች ስላሉ ለዚህ ምስክር ናቸው። ከዚህም በተጨማሪ ተፈጥሮአዊ ጽንዐ ድንግልናቸው በሩካቤ ብቻ ሊገሠሥ የማይቻል እየሆነ በቀዶ ጥገና ሕክምና ማኅተመ ድንግልናቸው እንዲወገድ የሚደረግላቸው ብዙ ሴቶች አሉ፡፡
ይህ ከሆነ ድንግል የሚለው ቃል ብቻውን የአንዲት ሴትን ትክክለኛ ድንግልነት ላይገልጽ ይችላል ማለት ነው፡፡ የሚገልጽ ቢሆን ኖሮ ያለ ምንም ተጨማሪ ቃላት ለእመቤታችን በተነገረ ነበር፡፡ ነገር ግን ስለ እመቤታችን አምላክን መፅነስና መውለድ ሲነገር በድንግልና ፀንሳ ወለደችው ከማለት በተጨማሪ «ያለ ሩካቤ፣ ያለ ዘር፣ ያለ ሰስሎተ ድንግልና›› ፀንሳ ወለደችው ማለት በብዙ መጻሕፍት የተለመደ አገላለጽ ነው፡፡ ለምሳሌ፡- «ወይእቲ ንጽሕት እምነ ሠለስቱ ግብራት ዘውእቶሙ ዘርዕ፣ ወሩካቤ፣ ወስስሎተ ድንግልና እለ ሥሩዓን በዕጓለ እመ ሕያው ወእሙራን ቦሙ» - «እርሷም በሰው ልጆች ዘንድ ከታወቁት ከሦስቱ ግብራት የተጠበቀች ናት እነርሱም ሩካቤ ዘር መቀበልና፣ የድንግልና መወገድ ናቸው፡፡» ይላል፡፡ (ትርጓሜ ውዳሴ ማርያም) ስለዚህ ሩካቤና ሰስሎተ ድንግልና የተለያዩና ራሳቸውን የቻሉ ተግባራት ተደርገው መታየት አለባቸው። አንዲትን ሴት ማኅተመ ድንግልና ስላላት ብቻ «ሩካቤ አድርጋ አታውቅም» ወይም ሩካቤ ስላደረገች «ማኅተመ ድንግልና ሊኖራት አይችልም» ብሎ ድምዳሜ ላይ መድረስ አለመቻሉን እንረዳለን፡፡ እመቤታችን ግን «ድንግል» የሚለው ቃል ከሚገልጸው በላይ «ፍጽምት» መሆኗን ተያይዘው በተጠቀሱት ተጨማሪ ቃላት እንረዳለን፡፡ ድንግል ማርያም በሕሊናዋም በሥጋዋም ፍጹም ድንግል የሆነች «ምክሐ ደናግል>> ናት፡፡
ማኅተመ ድንግልና በሩካቤ ሥጋ ጊዜ የሚጠፋ እንደ መሆኑ መጠን በቀጥታ በሥጋ ድንግል ከመሆንና ካለመሆን ጋር መዛመዱ ግልጽ ቢሆንም አንዳንድ ጊዜ ግን ከላይ ከተጠቀሰው በተጨማሪ ማኅተመ ድንግልናን «ከድንግልነት» ጋር ለይተን ለመመልከት የምንገደድበት ሁናቴ ይኖራል፡፡
ለምሳሌ ወንዶች እንደ ሴቶች ተጨባጭና ጉልህ የድንግልና ምልክት ስለሌላቸው ከሴት ጋር ሩካቤ ፈጽመው የማያውቁ ሆነው ሳለ ደናግል አይደሉም ለማለት አይቻልም:: እንደዚሁም ሁሉ ሩካቤን ፈጽመው የማያውቁ ሴቶች ሲወለዱ ጀምሮ ማኅተመ ድንግልና የሌላቸው ሊሆኑ ይችላሉ:: ወይም ከጊዜ በኋላ በክባድ የአካል እንቅስቃሴ፣ በአደጋ፣ በሕክምና ወይም በዕድሜ ብዛት ምክንያት ማኀተመ ድንግልና ሊፈርስባቸው ይችላል:: እንዲህ ያሉ ሴቶች ማኅተመ ድንግልናቸውን ቢያጡም ሩካቤ ፈጽመው እስካላወቁ ድረስ ደናግል መባላቸው የተጠበቀ ነው:: ምክንያቱም ድንግልናና ማኅተመ ድንግልና በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ ተለያይተው ስለሚታዩ ነው::
በሌላ አቅጣጫ ስንመለከት ወንዶች ሩካቤ ፈጽመው ሳለ እንደ ሴቶች የሚገሠሥ ማኅተመ ድንግልና ስለሌላቸው ድንግልናቸው አልፈረሰም እንደማይባል ሁሉ ሴቶች ሩካቤ ሥጋ እየፈጸሙ በልዩ ልዩ ምክንያት ማኅተመ ድንግልናቸው ባይገሠሥም መደበኛ ሩካቤ እስከ ፈጸሙ ድረስ ደናግል ሊባሉ አይችሉም:: ለምሳሌ:- የሚያይ የሚመስል ዓይን እያላቸው በመፍዘዙ ምክንያት የማያዩ ሰዎች የዓይን ምልክታቸው (ዓይን የሚባው ሕዋስ ወይም መልክ) ጨርሶ ስላልጠፋ ብቻ ዓይን አላቸው ይባላልን? እንደዚሁም ሁሉ ሩካቤ ፈጽመው ሳለ ማኀተመ ድንግልናቸው ባለመጥፋቱ ብቻ ደናግል ሊባሉ አይቻልም፡፡
አንዲትን ሴት ድንግል የሚያሰኛት ሥራዋና ዝንባሌዋ ብቻ ነው:: ማኅተመ ድንግልናዋ ስላልተወገደ ብቻ ወይም እርሷ ድንግል መሆን ስለምትፈልግ ወይም «ጳጳስ››ም ሆነ «ባሕታዊ» ጸሎት ስለ ደገመላት ድንግል መሆን አትችልም:: ከዚህ በታች የተጠቀሰው ኃይለ ቃል ይህንን ሐሳብ የሚያጎላ ነው፡፡ ‹‹ወኢያንብር ዕደ ላዕለ ድንግል አላ ምሥጢራ ባሕቲታ ትሬስያ ድንግለ›› የዚህ ዐረፍተ ነገር ትርጓሜ ‹‹ድንግል ናት ብሎ በአንብሮተ ዕድ አይሹማት (ድንግልና) ሾሜሻለው አይበላት:: ፈቃዷ ብቻ ድንግል ያደርጋታል እንጂ የሰው ፈቃድ ድንግል አያደርጋትምና፡፡» የሚል ነው፡፡ (ፍትሐ ነገሥት መንፈሳዊ)
የማኅተመ ድንግልና ስያሜዎች
ማኅተመ ድንግልና ሴት ከወንድ ጋር ሩካቤ አድርጋ አለማወቋን የሚያስረዳ የሥራዋ መገለጫ የእኗኗሯ መታወቂያ ልዩ የተፈጥሮ ምልክትና የድንግልናዊ ኑሮዋ ዘውድ ነው:: ይህ መለኮታዊ ማኅተም በሴቶች አፈ ማኅፀን ቀለበት በሚመስል ስስ ሥጋነት በጉልህ ይታወቃል፡፡ ድንግልና ጥቅሙን፣ ምሥጢሩን፤ ምሳሌውን የሚያመለክቱ ልዩ ልዩ ስያሜዎች አሉት:: በተለያዩ ቅዱሳት መጻሕፍት የተጠቀሱት እነዚህ የድንግልና መጠሪያዎች በርካታ ቢሆኑም ሦስት ያህሉ ብቻ ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል::
ሀ. ማኅተመ ድንግልና «ክንፈ ድንግልና» ተብሎ ይጠራል፡፡ በዚህ ዓለም ያለ ስጋት ለመንቀሳቀስ የሚያስችል የንጽሕና ክንፍ ነውና፡፡ አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ «ኦ ወለተ እስራኤል መኑ ቀረጸ አክናፈ ድንግልናኪ› በማለት የተናገረው ቃለ መጠይቅ ከላይ መኅተመ ድንግልና ‹ክንፈ ድንግልና (የድንግልና ክንፍ)» ይባላል በሚል ለተገለጸው ሐሳብ ብቁ ማስረጃ ይሆናል፡፡ ከዚህ ዐረፍተ ነገር እንጻር ለተመለከተው ድንግልናቸውን ያልጠበቁ ሰዎች በሙሉ ክንፍ የሌላትን ወፍ ይመስላሉ::
ለ. «ሕጓን ወሰደው› እንዲሉ ድንግልና ‹‹ሕግ›› ይባላል:: ሕግ የተባለበት ምክንያት «አታመንዝር» የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ሕግ መፈጸምና - አለመፈጸምን የሚያስታውቅ የሕግ ምልክት በመሆኑ ነው፡፡