ወሎ ቤተ አምራ ውስጥ አስደናቂ ድል ተመዘገበ:-
በደቡብ ወሎ ዞን መቅደላ ወረዳ የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር አማራ ሳይት መቅደላ ክፍለ ጦር ሼህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል::
-
ትናንት ታህሳስ 30 ቀን 2017 ዓመተ ምህረት ከወረዳው መቀመጫ ማሻ ከተማ ወደ ኮሬብ በሲኖትራክ ሲንቀሳቀስ የነበረ አድማ ብተና ላይ በተፈፀመ ድንገተኛ ጥቃት ሲኖትራኩ ላይ ያሉት አድማ ብተናዎችን እሳት በልቷቸዋል::
-
ደምወዝ ተቀብለው ሲገሰግሱ ድስም የምትባል ቦታ ላይ ነው ጭዳ የተደረጉት:: የአማራ ሳይት መቅደላ ክፍለ ጦር ምክትል አዛዥ ፋኖ ሙሀመድ አሊ (ጭንቅየለሽ) እና የሼህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ ዋና አዛዥ ፋኖ በለጠ ምትክ (ድሮን) በመሩት በዚህ ኦፕሬሽን አስደናቂ ድል ሊመዘገብ መቻሉን የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር አማራ ሳይት መቅደላ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ፋኖ ቃለአብ ወርቅዬ አስታውቋል::
-
በዚሁ በመቅደላ ወረዳ ውስጥ ታህሳስ 28 ቀን አቶ ኢብራሂም የተባለ ግለሰብ ከኮሬብ ወደ ማሻ ከተማ የቤተሰቡን እና የጎረቤቹን የሴፍቲኔት ገንዘብ ለመቀበል እንደመጣ መነሀሪያ ፊት ለፊት ህይወቱን በግፍ ተነጥቋል::
ይህ ግለሰብ ከፋኖ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌለው ሲሆን ከዚህ ቀደምም አንድ የባጃጅ ሾፌርን ሙዚቃ ለምን ከፈትክ ብለው ህይወቱን ተነጥቋል ተብሏል::
ጥምር ጦሩ በንፁሀን ላይ አሰቃቂ ግፍ መፈፀሙን ቀጥሏል ያለው ፋኖ ቃለአብ ይህን ግፍ የሚፈፅም ጠላት ጋር ንግግር ስለሌለን በምክክር ኮሚሽን ስም ደሴ ተሰባስቦ የሚመክር አካል ወደ እኛ ቢመጣ ቅጣታችን የከበደ እና እስከ ሞት የሚደርስ ነው ብሏል::
በደቡብ ወሎ ዞን መቅደላ ወረዳ የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር አማራ ሳይት መቅደላ ክፍለ ጦር ሼህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል::
-
ትናንት ታህሳስ 30 ቀን 2017 ዓመተ ምህረት ከወረዳው መቀመጫ ማሻ ከተማ ወደ ኮሬብ በሲኖትራክ ሲንቀሳቀስ የነበረ አድማ ብተና ላይ በተፈፀመ ድንገተኛ ጥቃት ሲኖትራኩ ላይ ያሉት አድማ ብተናዎችን እሳት በልቷቸዋል::
-
ደምወዝ ተቀብለው ሲገሰግሱ ድስም የምትባል ቦታ ላይ ነው ጭዳ የተደረጉት:: የአማራ ሳይት መቅደላ ክፍለ ጦር ምክትል አዛዥ ፋኖ ሙሀመድ አሊ (ጭንቅየለሽ) እና የሼህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ ዋና አዛዥ ፋኖ በለጠ ምትክ (ድሮን) በመሩት በዚህ ኦፕሬሽን አስደናቂ ድል ሊመዘገብ መቻሉን የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር አማራ ሳይት መቅደላ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ፋኖ ቃለአብ ወርቅዬ አስታውቋል::
-
በዚሁ በመቅደላ ወረዳ ውስጥ ታህሳስ 28 ቀን አቶ ኢብራሂም የተባለ ግለሰብ ከኮሬብ ወደ ማሻ ከተማ የቤተሰቡን እና የጎረቤቹን የሴፍቲኔት ገንዘብ ለመቀበል እንደመጣ መነሀሪያ ፊት ለፊት ህይወቱን በግፍ ተነጥቋል::
ይህ ግለሰብ ከፋኖ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌለው ሲሆን ከዚህ ቀደምም አንድ የባጃጅ ሾፌርን ሙዚቃ ለምን ከፈትክ ብለው ህይወቱን ተነጥቋል ተብሏል::
ጥምር ጦሩ በንፁሀን ላይ አሰቃቂ ግፍ መፈፀሙን ቀጥሏል ያለው ፋኖ ቃለአብ ይህን ግፍ የሚፈፅም ጠላት ጋር ንግግር ስለሌለን በምክክር ኮሚሽን ስም ደሴ ተሰባስቦ የሚመክር አካል ወደ እኛ ቢመጣ ቅጣታችን የከበደ እና እስከ ሞት የሚደርስ ነው ብሏል::