"እስኪ ከእኔ ጋር ሆናችሁ ቅዱስ ዳዊት ምን ያህል እግዚአብሔርን ከልቡ ይወደው እንደነበር እናስተውል። ቀን ቀን ያስባቸው ዘንድ ግድ የሚሉት የመሪዎች፣ የአዛዦች፣ የመንግሥታቱ፣ የሕዝቡ፣ የሠራዊቱና ስለ ጦርነት ውሎዎቹ፣ ስለ ሰላም፣ ስለ ፖለቲካውና በቤቱ ውስጥ ወይም ከቤቱ ውጪ ወይም በጎረቤቶቹ ዘንድ ስላለው ችግር ማውጣት ማውረዱ ልቡን ከፍለው ይወስዱበታል።
በዕረፍት ጊዜው እያንዳንዱ ሰው ለመኝታው የሚጠቀምበትን ሰዓት እርሱ ደግሞ ለንስሐ ለጸሎትና ዕንባውን ለማፍሰስ ይጠቀምበታል፡፡ እንዲህ ያለ ተግባሩን የሚፈጽመው ዛሬን አድርጎ ነገን ሳያደርግ አይደለም። ወይም ደግሞ ሁለት ወይም ሦስት ሌሊት በማለፍ አይደለም፤ በእያንዳንዷ ሌሊት እንጂ፡፡ «ሌሊቱን ሁሉ አልጋዬን አጥባለሁ፣ መኝታዬንም በዕንባዬ አርሳለሁ።» የሚለው ቃል የዕንባውን ብዛትና ዕንባው አለማቋረጡን ይገልጽልናል፡፡
እያንዳንዱ ፀጥ ባለ ዕረፍት ውስጥ በሚሆንበት ጊዜ እርሱ ግን እግዚአብሔርን ብቻውን አግኝቶ ለዕንቅልፍ ባልተከደኑ ዓይኖቹ ያለቀስና ያዘነ የግል ኃጢአቶቹን ይነግረዋል፡፡ አንተም ብትሆን እንዲህ ዓይነቱን አልጋ ለራስህ ታበጅ ዘንድ ይገባሃል። በወርቅና ብር ተከበህ መተኛት ከሰዎች ቅናትን ከአርያም ደግሞ ቁጣን ይቀሰቅስብሃል፡፡ እንደ ዳዊት ያለ ዕንባ ግን የሲዖልን እሳት ያጠፋል፡፡
ሌላ አልጋ ደግሞ ላሳይህን? ይህ አልጋ የያዕቆብ ነው። ለስውነቱ ባዶ መሬትን ለትራሱ ደግሞ ድንጋይን የተጠቀመበት አልጋ! ይህ በመሆኑም ያን መንፈሳዊ ድንጋይና ያቺን መላእክት ሲወጡባትና ሲወርዱባት የነበረችውን መሰላል ሊመለከት ችሏል፡፡ (ዘፍ 28፣ ከ1ኛ ቆሮ 10፥4 ጋር አዛምድ፡፡) በመጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ድንጋዮች ለክርስቶስ ምሳሌ ሆነው ተጠቅሰዋል፡፡ እኛም እንዲህ ያሉ ሕልሞች እናይ ዘንድ ሕሊናችንን እንደዚህ ባሉት አልጋዎች ላይ እናሳርፍ፡፡ ነገር ግን ከብር በተሠሩ አልጋዎች ላይ ብንተኛ ደስታን ብቻ ሳይሆን የምናጣው ችግርንም እንጋፈጣለን፡፡
እጅግ በጣም ቀዝቃዛ በሆነ እኩለ ሌሊት አንተ በአልጋህ ውስጥ ተኝተህ ሳለህ ድሀው ሰው ግን በጭድ ክምር ላይ በደጅህ ወድቆ በብርድ እየተንቀጠቀጠና በረሀብ እየተገረፈ ተዘርግቷል:: አንተ ከስዎች ሁሉ ልበ ደንዳና ብትሆን እንኳ ለዚህ ለድሀ የሚገባውን ሳታደርግለት ለራስህ አላስፈላጊ ምቾቶችን መፍቀድህ እርግጠኛ ነኝ ራስህን እንድትረግም ያደርግሃል። «የሚዘምተው ሁሉ ለጦር ያስከተተውን ደስ ያሰኝ ዘንድ ትዳር በሚገኝበት ንግድ ራሱን አያቆላልፍም።» (2ኛ ጢሞ. 2፥4) ተብሎ ተጽፏልና፡፡
አንተም መንፈሳዊ ወታደር ነህ፡፡ እንዲህ ያለ ወታደር ደግሞ በመሬት ላይ ይተኛል እንጂ ከዝሆን ጥርስ በተሠራ አልጋ ላይ አይተኛም፤ እጅግ ያማረ ሽቶም ኣይቀባም፡፡ እንዲህ ያለው ተግባር በመድረክ ላይ እየተወኑ በግድ የለሽነት ከሚኖሩና ከጋለሞታ ሴቶች ጋር ጊዜያቸውን በማባከን የሚኖሩ የምግባረ ብልሹ ሰዎች ተግባር ነው፡፡ የእኛ ጥሩ መዓዛ ግን ሽቱ ሳይሆን መልካም ሥራ ሊሆን ይገባል፡፡ በሽቱ መዓዛ ከሚመጣው ጠንቅ የበለጠ ነፍስን የሚያቆሽሽ ነገር አይኖርም፡፡ በአብዛኛው አፍአዊ (ውጪያዊ) መልካም መዓዛ የሰው ውስጣዊ ማንነት ማደፍና መቆሸሽ ምልክት ነው፡፡
ዲያብሎስ ነፍስን በራስ ወዳድነት ተዋግቶ ሲያሸንፋትና በታላቅ ከንቱነት ሲሞላት አስቀድሞ አቆሽሾት ወይም አጉድፎት ወይም አበልዞት የነበረውን ሰውነት በሽቶ ያጸዳዋል:: ልክ በጉንፋን እንደተያዙና ያለማቋረጥ በአፍንጫቸው የሚወጣውን ፈሳሽ ለማጽዳት ልብሳቸውን፣ እጆቻቸውንና ፊታቸውን እንደሚያጎድፉ ሁሉ እንዲህ ያለው የክፉ ስው ነፍስም ሰይጣን በሰውነቱ ላይ ያፈሰሰበትን ኃጢአት ለማጽዳት ይሞክራል፡፡ ሽቶ ሽቶ ከሚያውድ፣ ከጋለሞታ ጋር ወዳጅነት ከመሠረተ፣ የዳንኪረኛነት ሕይወትን ከሚመራ ሰው ማን ጨዋና መልካም ነገርን መጠበቅ ይችላል? እስቲ ነፍስህ መንፈሳዊ መዓዛን ትተንፍስና ለአንተም ሆነ ለወዳጆችህ ታላቅ በረከትን ታድላቸው፡፡"
(ሀብታምና ድሀ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደሰበከው -ገጽ 21-23 አያሌው ዘኢየሱስ እንደተረጎመው)
@mekra_abaw
በዕረፍት ጊዜው እያንዳንዱ ሰው ለመኝታው የሚጠቀምበትን ሰዓት እርሱ ደግሞ ለንስሐ ለጸሎትና ዕንባውን ለማፍሰስ ይጠቀምበታል፡፡ እንዲህ ያለ ተግባሩን የሚፈጽመው ዛሬን አድርጎ ነገን ሳያደርግ አይደለም። ወይም ደግሞ ሁለት ወይም ሦስት ሌሊት በማለፍ አይደለም፤ በእያንዳንዷ ሌሊት እንጂ፡፡ «ሌሊቱን ሁሉ አልጋዬን አጥባለሁ፣ መኝታዬንም በዕንባዬ አርሳለሁ።» የሚለው ቃል የዕንባውን ብዛትና ዕንባው አለማቋረጡን ይገልጽልናል፡፡
እያንዳንዱ ፀጥ ባለ ዕረፍት ውስጥ በሚሆንበት ጊዜ እርሱ ግን እግዚአብሔርን ብቻውን አግኝቶ ለዕንቅልፍ ባልተከደኑ ዓይኖቹ ያለቀስና ያዘነ የግል ኃጢአቶቹን ይነግረዋል፡፡ አንተም ብትሆን እንዲህ ዓይነቱን አልጋ ለራስህ ታበጅ ዘንድ ይገባሃል። በወርቅና ብር ተከበህ መተኛት ከሰዎች ቅናትን ከአርያም ደግሞ ቁጣን ይቀሰቅስብሃል፡፡ እንደ ዳዊት ያለ ዕንባ ግን የሲዖልን እሳት ያጠፋል፡፡
ሌላ አልጋ ደግሞ ላሳይህን? ይህ አልጋ የያዕቆብ ነው። ለስውነቱ ባዶ መሬትን ለትራሱ ደግሞ ድንጋይን የተጠቀመበት አልጋ! ይህ በመሆኑም ያን መንፈሳዊ ድንጋይና ያቺን መላእክት ሲወጡባትና ሲወርዱባት የነበረችውን መሰላል ሊመለከት ችሏል፡፡ (ዘፍ 28፣ ከ1ኛ ቆሮ 10፥4 ጋር አዛምድ፡፡) በመጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ድንጋዮች ለክርስቶስ ምሳሌ ሆነው ተጠቅሰዋል፡፡ እኛም እንዲህ ያሉ ሕልሞች እናይ ዘንድ ሕሊናችንን እንደዚህ ባሉት አልጋዎች ላይ እናሳርፍ፡፡ ነገር ግን ከብር በተሠሩ አልጋዎች ላይ ብንተኛ ደስታን ብቻ ሳይሆን የምናጣው ችግርንም እንጋፈጣለን፡፡
እጅግ በጣም ቀዝቃዛ በሆነ እኩለ ሌሊት አንተ በአልጋህ ውስጥ ተኝተህ ሳለህ ድሀው ሰው ግን በጭድ ክምር ላይ በደጅህ ወድቆ በብርድ እየተንቀጠቀጠና በረሀብ እየተገረፈ ተዘርግቷል:: አንተ ከስዎች ሁሉ ልበ ደንዳና ብትሆን እንኳ ለዚህ ለድሀ የሚገባውን ሳታደርግለት ለራስህ አላስፈላጊ ምቾቶችን መፍቀድህ እርግጠኛ ነኝ ራስህን እንድትረግም ያደርግሃል። «የሚዘምተው ሁሉ ለጦር ያስከተተውን ደስ ያሰኝ ዘንድ ትዳር በሚገኝበት ንግድ ራሱን አያቆላልፍም።» (2ኛ ጢሞ. 2፥4) ተብሎ ተጽፏልና፡፡
አንተም መንፈሳዊ ወታደር ነህ፡፡ እንዲህ ያለ ወታደር ደግሞ በመሬት ላይ ይተኛል እንጂ ከዝሆን ጥርስ በተሠራ አልጋ ላይ አይተኛም፤ እጅግ ያማረ ሽቶም ኣይቀባም፡፡ እንዲህ ያለው ተግባር በመድረክ ላይ እየተወኑ በግድ የለሽነት ከሚኖሩና ከጋለሞታ ሴቶች ጋር ጊዜያቸውን በማባከን የሚኖሩ የምግባረ ብልሹ ሰዎች ተግባር ነው፡፡ የእኛ ጥሩ መዓዛ ግን ሽቱ ሳይሆን መልካም ሥራ ሊሆን ይገባል፡፡ በሽቱ መዓዛ ከሚመጣው ጠንቅ የበለጠ ነፍስን የሚያቆሽሽ ነገር አይኖርም፡፡ በአብዛኛው አፍአዊ (ውጪያዊ) መልካም መዓዛ የሰው ውስጣዊ ማንነት ማደፍና መቆሸሽ ምልክት ነው፡፡
ዲያብሎስ ነፍስን በራስ ወዳድነት ተዋግቶ ሲያሸንፋትና በታላቅ ከንቱነት ሲሞላት አስቀድሞ አቆሽሾት ወይም አጉድፎት ወይም አበልዞት የነበረውን ሰውነት በሽቶ ያጸዳዋል:: ልክ በጉንፋን እንደተያዙና ያለማቋረጥ በአፍንጫቸው የሚወጣውን ፈሳሽ ለማጽዳት ልብሳቸውን፣ እጆቻቸውንና ፊታቸውን እንደሚያጎድፉ ሁሉ እንዲህ ያለው የክፉ ስው ነፍስም ሰይጣን በሰውነቱ ላይ ያፈሰሰበትን ኃጢአት ለማጽዳት ይሞክራል፡፡ ሽቶ ሽቶ ከሚያውድ፣ ከጋለሞታ ጋር ወዳጅነት ከመሠረተ፣ የዳንኪረኛነት ሕይወትን ከሚመራ ሰው ማን ጨዋና መልካም ነገርን መጠበቅ ይችላል? እስቲ ነፍስህ መንፈሳዊ መዓዛን ትተንፍስና ለአንተም ሆነ ለወዳጆችህ ታላቅ በረከትን ታድላቸው፡፡"
(ሀብታምና ድሀ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደሰበከው -ገጽ 21-23 አያሌው ዘኢየሱስ እንደተረጎመው)
@mekra_abaw