መጠጊያ አለህ!
በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ፣ በየትኛውም ከባድና ቀላል አጋጣሚ ውስጥ የአምላክ መንፈስ አለ። ሽብር፣ ስብራት፣ ስጋት፣ ፍረሃት፤ ጭንቀት ቢገጥምህ የምታመልጥበት፣ የምታልፍበት መጠጊያ አምላክ አለህ። ነገሮች በምክንያት ይሆናሉ፣ ሁነቶች ሌላ ውጤት አስከትለው ይመጣሉ፣ ውጤትም ወደ ሌላ ውጤት ይመራል። አምላክም በህይወታችን የሚከሰቱትን አጋጣሚዎች በምክንያት ዝም ይላቸዋል፤ እነርሱን ከማሳለፍ ወይም ከማስቀረት ይልቅ እኛን ያበረታናል፣ በጥንካሬያችን እንድናልፈው ያደርገናል። ቢያስቀራቸው ለእርሱ እጅጉን ቀላል ነው፤ እኛ ግን በምትክቱ ማግኘት የሚገባንን ጥንካሬ እናጣለን፣ ብርታታችን ይሸሸናል፣ እድገታችን ይገታል፣ ከለውጥ እንርቃለን።
አዎ! ጀግናዬ..! መጠጊያ አለህ! ከጭንቀትህ የምታመልጥበት፣ ፍራቻህን የምትሻገርበት፣ ስጋትህን የምትቀርፍበት በማንነቱ አሳራፊ የሆነ፣ ከለላ የሆነ፣ መጋቢ የሆነ ደንቅ መጠለያ፣ ግሩም መጠጊያ አለህ። በአለማዊ ጫናዎች አትሸበር፤ በሰዎች ጫጫታ አትጨነቅ፣ በምድራዊ ውጣውረድ አትበገር። አላማህን ያዝ፣ አምላክህን አስቀድም፣ ህይወትህን ትርጉም ስጠው፣ ብትደገፍ የማይጥልህን፣ ብታምነው የማይከዳህን፣ ብትከለልበት የማያስጠቃህን ቸር አምላክ፣ ሩህሩህ ፈጣሪ ያዝ። አምላክ ምንም ቢያደርግ ምክንያት አለው፤ ምንም ቢፈጥር ከእኛ የሚልቅ ሰበብ አለው። የሆነው መሆን ስላለበት ሆነ፤ እየሆነ ያለውም መሆን ስላለበት እየሆነ ነው፣ መሆን ያለበትም መሆን ስለሚገባው ይሆናል።
አዎ! ሁሉም ለበጎ ሆኗል፤ በበጎ ያልፋል። የሚቀየር ነገር ይቀየራል፤ የሚስተካከል ይስተካከላል፤ የሚታረም ይታረማል፤ ለውጥም ይመጣል፣ እድገትም ይከሰታል፤ አንዳች ሁነት ግን ላይታለፍ፣ ላያልፍ አይመጣም። የዛሬ ጭንቀቶች ነገ ተረት ናቸው፤ የዛሬ ስጋቶች ነገ ብርታት ናቸው፤ የዛሬ ከባዶች ነገ ሃይል ናቸው። ህያው መጠጊያ ባለበት፣ ዘላለማዊ መሸሸጊያ፣ ማምለጫ ባለበት በጊዜያዊ ጭንቀት፣ በአላፊ ስብራት እራስህን አትጉዳ፤ ከየትኛውም ምድራዊ ፈተና የሚከልልህ፣ የሚጠብቅህ ድንቅ አባት እንዳለህ አስታውስ። በድካምህ ተደገፈው፣ በህመምህ ተጠጋው፣ ጭንቀትህን አዋየው፣ ስጋትህን አስረዳው፣ የማያልፍ የሚመስለውን በእርሱ እለፍ፣ የማይሻገሩት የሚመስለውን በእርሱ ተሻገር፤ በእርሱ ከለላነት፣ በእርሱ መጠጊያነት ከጊዜያዊ ፈተናዎችህ አምልጥ።
በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ፣ በየትኛውም ከባድና ቀላል አጋጣሚ ውስጥ የአምላክ መንፈስ አለ። ሽብር፣ ስብራት፣ ስጋት፣ ፍረሃት፤ ጭንቀት ቢገጥምህ የምታመልጥበት፣ የምታልፍበት መጠጊያ አምላክ አለህ። ነገሮች በምክንያት ይሆናሉ፣ ሁነቶች ሌላ ውጤት አስከትለው ይመጣሉ፣ ውጤትም ወደ ሌላ ውጤት ይመራል። አምላክም በህይወታችን የሚከሰቱትን አጋጣሚዎች በምክንያት ዝም ይላቸዋል፤ እነርሱን ከማሳለፍ ወይም ከማስቀረት ይልቅ እኛን ያበረታናል፣ በጥንካሬያችን እንድናልፈው ያደርገናል። ቢያስቀራቸው ለእርሱ እጅጉን ቀላል ነው፤ እኛ ግን በምትክቱ ማግኘት የሚገባንን ጥንካሬ እናጣለን፣ ብርታታችን ይሸሸናል፣ እድገታችን ይገታል፣ ከለውጥ እንርቃለን።
አዎ! ጀግናዬ..! መጠጊያ አለህ! ከጭንቀትህ የምታመልጥበት፣ ፍራቻህን የምትሻገርበት፣ ስጋትህን የምትቀርፍበት በማንነቱ አሳራፊ የሆነ፣ ከለላ የሆነ፣ መጋቢ የሆነ ደንቅ መጠለያ፣ ግሩም መጠጊያ አለህ። በአለማዊ ጫናዎች አትሸበር፤ በሰዎች ጫጫታ አትጨነቅ፣ በምድራዊ ውጣውረድ አትበገር። አላማህን ያዝ፣ አምላክህን አስቀድም፣ ህይወትህን ትርጉም ስጠው፣ ብትደገፍ የማይጥልህን፣ ብታምነው የማይከዳህን፣ ብትከለልበት የማያስጠቃህን ቸር አምላክ፣ ሩህሩህ ፈጣሪ ያዝ። አምላክ ምንም ቢያደርግ ምክንያት አለው፤ ምንም ቢፈጥር ከእኛ የሚልቅ ሰበብ አለው። የሆነው መሆን ስላለበት ሆነ፤ እየሆነ ያለውም መሆን ስላለበት እየሆነ ነው፣ መሆን ያለበትም መሆን ስለሚገባው ይሆናል።
አዎ! ሁሉም ለበጎ ሆኗል፤ በበጎ ያልፋል። የሚቀየር ነገር ይቀየራል፤ የሚስተካከል ይስተካከላል፤ የሚታረም ይታረማል፤ ለውጥም ይመጣል፣ እድገትም ይከሰታል፤ አንዳች ሁነት ግን ላይታለፍ፣ ላያልፍ አይመጣም። የዛሬ ጭንቀቶች ነገ ተረት ናቸው፤ የዛሬ ስጋቶች ነገ ብርታት ናቸው፤ የዛሬ ከባዶች ነገ ሃይል ናቸው። ህያው መጠጊያ ባለበት፣ ዘላለማዊ መሸሸጊያ፣ ማምለጫ ባለበት በጊዜያዊ ጭንቀት፣ በአላፊ ስብራት እራስህን አትጉዳ፤ ከየትኛውም ምድራዊ ፈተና የሚከልልህ፣ የሚጠብቅህ ድንቅ አባት እንዳለህ አስታውስ። በድካምህ ተደገፈው፣ በህመምህ ተጠጋው፣ ጭንቀትህን አዋየው፣ ስጋትህን አስረዳው፣ የማያልፍ የሚመስለውን በእርሱ እለፍ፣ የማይሻገሩት የሚመስለውን በእርሱ ተሻገር፤ በእርሱ ከለላነት፣ በእርሱ መጠጊያነት ከጊዜያዊ ፈተናዎችህ አምልጥ።