ወደፊት ሂዱ!
አሁን የት ናችሁ? እናንተ ጋር ያለው እውነት ምንድነው? ቆም ብላችሁ በጥልቀት ስታስቡ ምን ጎልቶ ይታያችኋል? በአስተሳሰብ እስራት አትታሰሩ፣ በሰዎች አመለካከት አትገደቡ፣ ፍረሃት መረማመጃ እንዲያሳጣችሁ አትፍቀዱ። ለማንም የማይታየው፣ ማንም ሊረዳው የማይችለው እውነት እናንተ ጋር አለ። እውነታውም ወደፊት መሔድ ነው፤ እውነታው ዝም ብሎ መጓዝ ነው፤ እውነታው ትርጉም ባለው መንገድ ህይወትን መኖር ነው። ለማንም ብላችሁ አትሳቀቁ፣ ለማንም ብላችሁ አትሸማቀቁ፣ በምንም ነገር ላይ ተስፋ አትቁረጡ። ልባችሁ ውስጥ ጥልቅ ፍላጎት ካለ፣ ከማንነታችሁ ጋር የተዋሃደ ብርቱ ሀሳብ ካለ ለማን ብላችሁ ሳትኖሩት ትቀራላችሁ? ለማን ብላችሁ ሳታደርጉት ትቀራላችሁ? ማን ደስ እንዲለውስ ነው ሄዳችሁ የማታገኙት? አሁን ከምትኖሩት የተለየ ህይወት እንዳለ የምታምኑ ከሆነ ያለምንም ግፊትና ጫና ራሳችሁን ወደፊት ግፉት፣ ማንም ሳያስገድዳችሁ ጉዟችሁን ጀምሩ። በእርግጥ ፈልጋችሁ ባላችሁበት ቦታ ለረጅም ጊዜ አትኖሩም። ነገር ግን እንዳልፈለጋችሁት ለማሳየት የግድ መሞከር ይኖርባችኋል።
አዎ! ወደፊት ሂዱ፣ ተንቀሳቀሱ፣ ሁሌም ራሳችሁን ለተሻለ ነገር ለማብቃት ትጉ። ያሰሯችሁ ብዙ ነገሮች ይኑሩ፣ በብዙ ነገር ተያዙ፣ ማንም ምንም ይበላችሁ እናንተ ግን ጉዟችሁ ላይ ብቻ አተኩሩ፣ እናንተ ግን ስለአሁኑና ስለቀጣይ እርምጃችሁ ብቻ አስቡ። ሁሌም ቢሆን አንድ የተለየ መንገድ እንዳለ አትርሱ። ብዙ ሰው የሚመለከተውንም የማይመለከተውንም ለመረዳት ይታገላል፣ ሁሉም ነገር እንዲገባው ይፈልጋል። እውነታው ግን አዕምሮው የሚቀበለውና የሚረዳው በአቅሙ ልክ መሆኑ ነው። ለአዕምሯችሁ ሰላም፣ ለውስጥ መረጋጋታችሁ፣ ለለውጥ ተነሳሽነታችሁ፣ ህልማችሁን ለመኖር፣ የአላማ ሰው ለመሆን ብላችሁ ሁሉንም ነገር ለመረዳት አትሞክሩ። አዕምሯችሁ በዚህም በዛም ጉዳይ ተወጥሮ እንዴትም በትክክል ሊያስብና ሊያስተውል አይችልም። ሄዳችሁ ሄዳችሁ ለብቻ የምትቀሩት እናንተ እንደሆናችሁ አስተውሉ። በፍፁም እዚም እዛም የሚገባ፣ ይሔም ያም የሚያሳስበው ብኩን ሰው እንዳትሆኑ። የራሳችሁ ጉዳይ ላይ ብቻ አተኩሩ፣ ወደፊት ፍሬ የሚያፈራላችሁን ተግባር ብቻ ፈፅሙ፣ የሚመለከታችሁና የሚጠቅማችሁ ቦታ ብቻ ተገኙ።
አዎ! ጀግናዬ..! ድካም በማንኛውም ሰዓት ይመጣል፣ ስንፍና ሁሌም ከበርህ አፋፍ ሆኖ ይጠብቅሃል፣ መቼም ከችግር የፀዳ ህይወት ልትኖር አትችልም። ዋናው ቁብነገር ግን በዚህ ሁሉ መሃል ወደፊት መራመድ መቻልህ ነው። ለማንም ብለህ ለዘመናት አንድ ቦታ ቆመህ አትቅር፣ ማንም እንዲደሰት ወይም ያዝንብኛል ብለህ ፍረሃትህን አትኑረው። ከታጠረልህ አጥር ውጣ፣ ከገባህበት አዘቅት ራስህን መንጭቀህ አውጣ፣ እስራትህን ፍታ፣ በገዛ ሰማይህ ላይ በከፍታ መብረሩን እወቅበት። ጉዞ የሌለው ህይወት ይሰላቻል፣ ለውጥ የሌለው ኑሮ አያጓጓም። ለውጥን አማራጭ አታድርገው፣ ወደፊት መጓዝን መብት አታድርገው። እየተለወጥክ ካልሆነ፣ እያደክ ካልሆነ፣ ሌላው ቢቀር እንኳን እንደ አቅምህ እየጣርክ ካልሆነ ስለህይወት ክፉና ደግ ለማውራት ብቁ እንደሆንክ አታስብ። ነገሮችን አታወሳስብ፣ ችግርና መሰናክሉ ላይ ብቻ አታተኩር። አንቂ ሳትፈልግ በራስህ ንቃ፣ አበረታች ሳትፈልግ ራስህ በርታ፣ ሁሌም ወደፊት ወደ ግብህ አቅጣጫ መጓዝህን ቀጥል።
አሁን የት ናችሁ? እናንተ ጋር ያለው እውነት ምንድነው? ቆም ብላችሁ በጥልቀት ስታስቡ ምን ጎልቶ ይታያችኋል? በአስተሳሰብ እስራት አትታሰሩ፣ በሰዎች አመለካከት አትገደቡ፣ ፍረሃት መረማመጃ እንዲያሳጣችሁ አትፍቀዱ። ለማንም የማይታየው፣ ማንም ሊረዳው የማይችለው እውነት እናንተ ጋር አለ። እውነታውም ወደፊት መሔድ ነው፤ እውነታው ዝም ብሎ መጓዝ ነው፤ እውነታው ትርጉም ባለው መንገድ ህይወትን መኖር ነው። ለማንም ብላችሁ አትሳቀቁ፣ ለማንም ብላችሁ አትሸማቀቁ፣ በምንም ነገር ላይ ተስፋ አትቁረጡ። ልባችሁ ውስጥ ጥልቅ ፍላጎት ካለ፣ ከማንነታችሁ ጋር የተዋሃደ ብርቱ ሀሳብ ካለ ለማን ብላችሁ ሳትኖሩት ትቀራላችሁ? ለማን ብላችሁ ሳታደርጉት ትቀራላችሁ? ማን ደስ እንዲለውስ ነው ሄዳችሁ የማታገኙት? አሁን ከምትኖሩት የተለየ ህይወት እንዳለ የምታምኑ ከሆነ ያለምንም ግፊትና ጫና ራሳችሁን ወደፊት ግፉት፣ ማንም ሳያስገድዳችሁ ጉዟችሁን ጀምሩ። በእርግጥ ፈልጋችሁ ባላችሁበት ቦታ ለረጅም ጊዜ አትኖሩም። ነገር ግን እንዳልፈለጋችሁት ለማሳየት የግድ መሞከር ይኖርባችኋል።
አዎ! ወደፊት ሂዱ፣ ተንቀሳቀሱ፣ ሁሌም ራሳችሁን ለተሻለ ነገር ለማብቃት ትጉ። ያሰሯችሁ ብዙ ነገሮች ይኑሩ፣ በብዙ ነገር ተያዙ፣ ማንም ምንም ይበላችሁ እናንተ ግን ጉዟችሁ ላይ ብቻ አተኩሩ፣ እናንተ ግን ስለአሁኑና ስለቀጣይ እርምጃችሁ ብቻ አስቡ። ሁሌም ቢሆን አንድ የተለየ መንገድ እንዳለ አትርሱ። ብዙ ሰው የሚመለከተውንም የማይመለከተውንም ለመረዳት ይታገላል፣ ሁሉም ነገር እንዲገባው ይፈልጋል። እውነታው ግን አዕምሮው የሚቀበለውና የሚረዳው በአቅሙ ልክ መሆኑ ነው። ለአዕምሯችሁ ሰላም፣ ለውስጥ መረጋጋታችሁ፣ ለለውጥ ተነሳሽነታችሁ፣ ህልማችሁን ለመኖር፣ የአላማ ሰው ለመሆን ብላችሁ ሁሉንም ነገር ለመረዳት አትሞክሩ። አዕምሯችሁ በዚህም በዛም ጉዳይ ተወጥሮ እንዴትም በትክክል ሊያስብና ሊያስተውል አይችልም። ሄዳችሁ ሄዳችሁ ለብቻ የምትቀሩት እናንተ እንደሆናችሁ አስተውሉ። በፍፁም እዚም እዛም የሚገባ፣ ይሔም ያም የሚያሳስበው ብኩን ሰው እንዳትሆኑ። የራሳችሁ ጉዳይ ላይ ብቻ አተኩሩ፣ ወደፊት ፍሬ የሚያፈራላችሁን ተግባር ብቻ ፈፅሙ፣ የሚመለከታችሁና የሚጠቅማችሁ ቦታ ብቻ ተገኙ።
አዎ! ጀግናዬ..! ድካም በማንኛውም ሰዓት ይመጣል፣ ስንፍና ሁሌም ከበርህ አፋፍ ሆኖ ይጠብቅሃል፣ መቼም ከችግር የፀዳ ህይወት ልትኖር አትችልም። ዋናው ቁብነገር ግን በዚህ ሁሉ መሃል ወደፊት መራመድ መቻልህ ነው። ለማንም ብለህ ለዘመናት አንድ ቦታ ቆመህ አትቅር፣ ማንም እንዲደሰት ወይም ያዝንብኛል ብለህ ፍረሃትህን አትኑረው። ከታጠረልህ አጥር ውጣ፣ ከገባህበት አዘቅት ራስህን መንጭቀህ አውጣ፣ እስራትህን ፍታ፣ በገዛ ሰማይህ ላይ በከፍታ መብረሩን እወቅበት። ጉዞ የሌለው ህይወት ይሰላቻል፣ ለውጥ የሌለው ኑሮ አያጓጓም። ለውጥን አማራጭ አታድርገው፣ ወደፊት መጓዝን መብት አታድርገው። እየተለወጥክ ካልሆነ፣ እያደክ ካልሆነ፣ ሌላው ቢቀር እንኳን እንደ አቅምህ እየጣርክ ካልሆነ ስለህይወት ክፉና ደግ ለማውራት ብቁ እንደሆንክ አታስብ። ነገሮችን አታወሳስብ፣ ችግርና መሰናክሉ ላይ ብቻ አታተኩር። አንቂ ሳትፈልግ በራስህ ንቃ፣ አበረታች ሳትፈልግ ራስህ በርታ፣ ሁሌም ወደፊት ወደ ግብህ አቅጣጫ መጓዝህን ቀጥል።