ጠንካራ ሁኑ!
በምድር ላይ በክብር ትመላለሱ ዘንድ፣ ዓለም ቦታ ትሰጣችሁ ዘንድ፣ ሰዎች ይፈልጓችሁና ይመርጧችሁ ዘንድ፣ የህይወትን ፈተናንም በድል ትወጡ ዘንድ ጠንካራ ሁኑ። ከአለት የጠነከረ ጠንካራ፣ በእሳት ተፈትኖ ከሚወጣው ብረት በላይ ጠንካራ፣ ልቡ የደነደነ፣ ውስጡ የረጋ፣ ለምንም ለማንም የማትበገር ብርቱ ጠንካራ ሰው ሁኑ። በዚህ ዓለም ለደካሞች ቦታ የለም፣ ምድር ሰነፎችን ሸልማ አታውቅም። ህይወትን እስከኖራችሁ ድረስ የጀብደኛ ህይወትን ኑሩ። በእያንዳንዳችን ህይወት ውስጥ ምንአይነት ከባባድ ነገሮች እንደሚፈጠሩ አናውቅም። ነገር ግን የምናውቀው አንድ ነገር አለ እርሱም "ጠንካራ ካልሆንን በእነዛ ከባባድ ክስተቶች ምክንያት አሳዛኝ ህይወት መኖራችንን ነው።" ተስፋችሁ የመከነ ቢመስላችሁም በፍፁም ተስፋ አትቁረጡ፣ ህይወት ከባድ ብትመስላችሁም በፍፁም እጅ እንዳትሰጡ፣ ሰዎች እንደገፏችሁ ቢሰማችሁም ለራሳችሁ ብርቱ ወዳጅ ሁኑ። ደካማ መሆን ለውድቀት ያመቻቻችኋል፣ ስንፍና በቀላሉ እንድትሸነፉ ያደርጋችኋል፣ ልፍስፍስ መሆን ተስፋን ያሳጣችኋል። ከልባችሁ አስባችሁ አቅማችሁን መዝኑት፣ ጥንካሬያችሁን ለኩት፣ ከፊትለፊት የሚጠብቃችሁን ፈተና ለማለፍ ያላችሁን ብርታት መርምሩት።
አዎ! ጠንካራ ሁኑ፣ በጨለማ መሃል ብረሃንን የምትመለከቱ፣ በማጣት ሰዓት ማግኘትን የምታምኑ፣ በረሃብ ወቅት ጥጋብም እንደሚኖር የምታስተውሉ፣ በብቸኝነት ሰዓት የፈጣሪ አብሮነት እንዳለ የምትረዱ፣ በመገፋት ወቅት ማራኪ ፍቅር እንደሚመጣ የምታስቡ ጠንካራ ሰው ሁኑ። በምንም መንገድ ለራሳችሁ የደካማነት አማራጭ አትስጡ፣ ፈተና ቢበዛ፣ ችግር ቢፈራረቅ፣ ዓለምም ፊቷን ብታዞርባችሁ እንዴትም በህይወታችሁ ተስፋ እንዳትቆርጡ። አስቀድማችሁ ያያችሁት ብሩህ ቀን ከጨለማው ማግስት ይጠብቃችኋል፣ ከልባችሁ ከምትፈልጉት መንፈሳዊ ደሴታችሁ በችግራችሁ በኩል ትደርሱበታላችሁ፣ ደጋግማችሁ ያሰባችሁት ለውጥና እድገት በጥረታችሁ ልክ እጃችሁ ይገባል። በማጣት ውስጥም ብትሆኑ፣ ለጊዜው ስኬት ቢርቃችሁ፣ በሰዓቱ የምትፈልጉበት ቦታ ባትደርሱ፣ ውስጣችሁ መረጋጋት ቢሳነው፣ መቋጫ የሌለው ሀሳብ ፋታ ቢነሳችሁ እንኳን መኖር የሚያምርባችሁ ጠንካራ ስትሆኑ ብቻ እንደሆነ እወቁ፣ ዓለም እጇን ዘርግታ በፍቅር የምትቀበላችሁ አሸናፊዎች ስትሆኑ ብቻ እንደሆነ ተረዱ።
አዎ! ጀግናዬ..! የልብህን እምነት መደበቅ አትችልም፣ ምግባርህን ሸሽገህ አትዘልቀውም፣ ስንፍናህን ልትሰውረው አትችልም። እምነትና አስተሳሰብህ ሳይውል ሳያድር በውጤትህ ይገለጣል፣ ለራስህ የምትሰጠው ቦታና በራስመተማመንህ በተግባርህ ይታያል። ጠንካራ፣ ለዓለም ፈተና የማይበገር፣ በምድራዊ ችግር ተስፋ የማይቆርጥ፣ ልቡን በአምላኩ ፍቅር ያደነደነ፣ ረዳት ደጋፊውን እያሰበ የሚፀና ሰው መሆን ከፈለክ ስቃይን አትሽሽ፣ ፈተና በመጣ ቁጥር አታማር፣ ችግር ሲደራረብብህ ቶሎ አትብረክረክ። በቀላሉ የሚገኝ ጥንካሬ የለም፣ እንደ ቀልድ የሚገኝ ብርታት የለም። "በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዟችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።" እንዳለ ቅዱስ መፅሐፍ ዓለምን ያሸነፈላችሁን ፈጣሪ እያሰባችሁ ጠንክሩ፣ ብቻችሁን እንዳልሆናችሁ እያሰባችሁ በመከራ መሃል ፅኑ። ተስፋ የማይቆርጥ ትውልድ እርሱ በስተመጨረሻ አስደሳቹን የድል ፅዋ እንደሚጎነጭ እመኑ።
በምድር ላይ በክብር ትመላለሱ ዘንድ፣ ዓለም ቦታ ትሰጣችሁ ዘንድ፣ ሰዎች ይፈልጓችሁና ይመርጧችሁ ዘንድ፣ የህይወትን ፈተናንም በድል ትወጡ ዘንድ ጠንካራ ሁኑ። ከአለት የጠነከረ ጠንካራ፣ በእሳት ተፈትኖ ከሚወጣው ብረት በላይ ጠንካራ፣ ልቡ የደነደነ፣ ውስጡ የረጋ፣ ለምንም ለማንም የማትበገር ብርቱ ጠንካራ ሰው ሁኑ። በዚህ ዓለም ለደካሞች ቦታ የለም፣ ምድር ሰነፎችን ሸልማ አታውቅም። ህይወትን እስከኖራችሁ ድረስ የጀብደኛ ህይወትን ኑሩ። በእያንዳንዳችን ህይወት ውስጥ ምንአይነት ከባባድ ነገሮች እንደሚፈጠሩ አናውቅም። ነገር ግን የምናውቀው አንድ ነገር አለ እርሱም "ጠንካራ ካልሆንን በእነዛ ከባባድ ክስተቶች ምክንያት አሳዛኝ ህይወት መኖራችንን ነው።" ተስፋችሁ የመከነ ቢመስላችሁም በፍፁም ተስፋ አትቁረጡ፣ ህይወት ከባድ ብትመስላችሁም በፍፁም እጅ እንዳትሰጡ፣ ሰዎች እንደገፏችሁ ቢሰማችሁም ለራሳችሁ ብርቱ ወዳጅ ሁኑ። ደካማ መሆን ለውድቀት ያመቻቻችኋል፣ ስንፍና በቀላሉ እንድትሸነፉ ያደርጋችኋል፣ ልፍስፍስ መሆን ተስፋን ያሳጣችኋል። ከልባችሁ አስባችሁ አቅማችሁን መዝኑት፣ ጥንካሬያችሁን ለኩት፣ ከፊትለፊት የሚጠብቃችሁን ፈተና ለማለፍ ያላችሁን ብርታት መርምሩት።
አዎ! ጠንካራ ሁኑ፣ በጨለማ መሃል ብረሃንን የምትመለከቱ፣ በማጣት ሰዓት ማግኘትን የምታምኑ፣ በረሃብ ወቅት ጥጋብም እንደሚኖር የምታስተውሉ፣ በብቸኝነት ሰዓት የፈጣሪ አብሮነት እንዳለ የምትረዱ፣ በመገፋት ወቅት ማራኪ ፍቅር እንደሚመጣ የምታስቡ ጠንካራ ሰው ሁኑ። በምንም መንገድ ለራሳችሁ የደካማነት አማራጭ አትስጡ፣ ፈተና ቢበዛ፣ ችግር ቢፈራረቅ፣ ዓለምም ፊቷን ብታዞርባችሁ እንዴትም በህይወታችሁ ተስፋ እንዳትቆርጡ። አስቀድማችሁ ያያችሁት ብሩህ ቀን ከጨለማው ማግስት ይጠብቃችኋል፣ ከልባችሁ ከምትፈልጉት መንፈሳዊ ደሴታችሁ በችግራችሁ በኩል ትደርሱበታላችሁ፣ ደጋግማችሁ ያሰባችሁት ለውጥና እድገት በጥረታችሁ ልክ እጃችሁ ይገባል። በማጣት ውስጥም ብትሆኑ፣ ለጊዜው ስኬት ቢርቃችሁ፣ በሰዓቱ የምትፈልጉበት ቦታ ባትደርሱ፣ ውስጣችሁ መረጋጋት ቢሳነው፣ መቋጫ የሌለው ሀሳብ ፋታ ቢነሳችሁ እንኳን መኖር የሚያምርባችሁ ጠንካራ ስትሆኑ ብቻ እንደሆነ እወቁ፣ ዓለም እጇን ዘርግታ በፍቅር የምትቀበላችሁ አሸናፊዎች ስትሆኑ ብቻ እንደሆነ ተረዱ።
አዎ! ጀግናዬ..! የልብህን እምነት መደበቅ አትችልም፣ ምግባርህን ሸሽገህ አትዘልቀውም፣ ስንፍናህን ልትሰውረው አትችልም። እምነትና አስተሳሰብህ ሳይውል ሳያድር በውጤትህ ይገለጣል፣ ለራስህ የምትሰጠው ቦታና በራስመተማመንህ በተግባርህ ይታያል። ጠንካራ፣ ለዓለም ፈተና የማይበገር፣ በምድራዊ ችግር ተስፋ የማይቆርጥ፣ ልቡን በአምላኩ ፍቅር ያደነደነ፣ ረዳት ደጋፊውን እያሰበ የሚፀና ሰው መሆን ከፈለክ ስቃይን አትሽሽ፣ ፈተና በመጣ ቁጥር አታማር፣ ችግር ሲደራረብብህ ቶሎ አትብረክረክ። በቀላሉ የሚገኝ ጥንካሬ የለም፣ እንደ ቀልድ የሚገኝ ብርታት የለም። "በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዟችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።" እንዳለ ቅዱስ መፅሐፍ ዓለምን ያሸነፈላችሁን ፈጣሪ እያሰባችሁ ጠንክሩ፣ ብቻችሁን እንዳልሆናችሁ እያሰባችሁ በመከራ መሃል ፅኑ። ተስፋ የማይቆርጥ ትውልድ እርሱ በስተመጨረሻ አስደሳቹን የድል ፅዋ እንደሚጎነጭ እመኑ።