እኔ ግን አደረኩት!
ከእራስ ጋር ንግግር፦ "ስለ ገዛ ሰላሜ፣ ስለ ውስጣዊ መረጋጋቴ፣ ስለ እኔነቴ፣ ስለ ማንነቴ ብዙ አሰብኩ፣ ብዙ አወጣው ብዙ አወረድኩ፣ ብዙ ሰማው ብዙ አወራው። በስተመጨረሻም አንድ ነገር አስተዋልኩ የሰላሜ ባለቤት፣ የመረጋጋቴ መሰረት፣ የጤንነቴ ምንጭ፣ የመንፈሴ ገዢ አምላኬ ቅዱስ እግዚአብሔር እንደሆነ ደረስኩበት። ውስጥን በድፍረት ማዳመጥ ይህን ያክል ቀላል ባይሆንም ይጠቅመኛልና አደረኩት፤ አይኖች ሁሉ ውጪውጪውን በሚያማትሩበት፣ ሰው ሁሉ ሃሳቡ በተሰረቀበት ወቀት እራስን መመልከት ቢከብድም፣ ስለ እራስ ማሰብ፣ ስለ እራስ ማሰላሰል ቢከብድም እኔ ግን አደረኩት፤ ዓለም አጀንዳዋ ባያልቅም፣ ዘወትር ኮሽታ ባይጠፋትም፣ ትኩረቴንም አብዝታ ብትፈታተንም እኔ ግን የእርሷን አጀንዳ ትቼ፣ ጫጫታዋን ወደኋላ ገፍቼ እራሴ ላይ ማተኮር ቻልኩኝ።
አዎ! ዋናው አላማዬ ብዙ ተጉዤ፣ ብዙ ለፍቼ፣ ብዙ ደክሜ፣ ትልቅ ዋጋ ከፍዬ የምደርስበት ስፍራ አይደለም፤ ይልቅ በጉዞዬ መሐል የምገነባው ማንነትና የምፈጥረው ስብዕና ነው። እንደማንኛውም ሰው ጉድለት ቢኖርብኝም እንደማንኛውም ሰውም የተባረኩበት ነገር አለኝ። አምላኬን የማመሰግነው የሚያስፈልገኝን ስለሰጠኝ፣ የሚገባኝ ስፍራ ስላደረሰኝ፣ በጉዞዬ ሁሉ ስለረዳኝ፣ በመውጣት መውረዴ፣ በመውደቅ መነሳቴ፣ በመተቸት መወደሴ ሁሉ አብሮኝ ስለነበረ ብቻ አይደለም። የምስጋናዬ ምክንያት ሰውነቴ ነው፤ የምስጋናዬ ምክንያት እኔን እኔ ስላደረገኝ ነው፤ የአድናቆቴ መንስኤ የአባትነት ፍቅሩ፣ የአምላክነት ስጦታው ነው። እራሴን በማውቀው ልክ ለእራሴ መሆን ባልችልም አምላኬን በማውቀው ልክ ግን እለት እለት በቃሉ ለመመራት፣ ትዕዛዙን ለማክበር፣ ይቅርታውን ለማግኘት የምጥር ምስኪን ልጁ ነኝ። አመስጋኝህ ስላደረከኝ አመሰግንሃለሁ፤ ስጦታህን እንድረዳ በረከትህንም እንድመለከት ስላስቻልከኝ ከልቤ አከብርሃለሁ፤ በደካማው ማንነቴም እወድሃለሁ።
አዎ! ጀግናዬ...! ከእራስህ ገር የምታደርገው ንግግር በአስተውሎት አድርገው፤ ከአምላክህ ጋር ስትወያይ ጉዳይ ከልብህ ተወያይ። ሰው አይኘን አላየኝ፣ ሰማኝ አልሰማኝ፣ ስም አወጣልኝ ፈረደብኝ ብለህ አትፍራ። እራስህ ከእራስህና ከአምላክህ በላይ የሚያቅስህ አካል የለም። እራስህ ላይ ብትፈርድ፣ ለእራስህ የግል አቋም ብታበጅ፣ እምነትህን ብትፈትን፣ መንገድ ብትስት፣ ብትሳሳት ቀዳሚው ሃላፊነት የእንደሆነ አስተውል። ከእራስህና ከደጉ አባትህ በቀር ማንም ስለማይሰማህ የልብ ንግግር አትጨነቅ፤ ከእራስህና ከህያው አምላክህ በቀር ማንም በማያይህ መንፈሳዊ ተግባርህ አትሸማቀቅ። ከእራስህ ጋር ለመነጋገር ነፃ ሁን፤ ከአምላክህ ለመማከር ዘወትር መንፈሰ ጠንካራ ሁን።
ከእራስ ጋር ንግግር፦ "ስለ ገዛ ሰላሜ፣ ስለ ውስጣዊ መረጋጋቴ፣ ስለ እኔነቴ፣ ስለ ማንነቴ ብዙ አሰብኩ፣ ብዙ አወጣው ብዙ አወረድኩ፣ ብዙ ሰማው ብዙ አወራው። በስተመጨረሻም አንድ ነገር አስተዋልኩ የሰላሜ ባለቤት፣ የመረጋጋቴ መሰረት፣ የጤንነቴ ምንጭ፣ የመንፈሴ ገዢ አምላኬ ቅዱስ እግዚአብሔር እንደሆነ ደረስኩበት። ውስጥን በድፍረት ማዳመጥ ይህን ያክል ቀላል ባይሆንም ይጠቅመኛልና አደረኩት፤ አይኖች ሁሉ ውጪውጪውን በሚያማትሩበት፣ ሰው ሁሉ ሃሳቡ በተሰረቀበት ወቀት እራስን መመልከት ቢከብድም፣ ስለ እራስ ማሰብ፣ ስለ እራስ ማሰላሰል ቢከብድም እኔ ግን አደረኩት፤ ዓለም አጀንዳዋ ባያልቅም፣ ዘወትር ኮሽታ ባይጠፋትም፣ ትኩረቴንም አብዝታ ብትፈታተንም እኔ ግን የእርሷን አጀንዳ ትቼ፣ ጫጫታዋን ወደኋላ ገፍቼ እራሴ ላይ ማተኮር ቻልኩኝ።
አዎ! ዋናው አላማዬ ብዙ ተጉዤ፣ ብዙ ለፍቼ፣ ብዙ ደክሜ፣ ትልቅ ዋጋ ከፍዬ የምደርስበት ስፍራ አይደለም፤ ይልቅ በጉዞዬ መሐል የምገነባው ማንነትና የምፈጥረው ስብዕና ነው። እንደማንኛውም ሰው ጉድለት ቢኖርብኝም እንደማንኛውም ሰውም የተባረኩበት ነገር አለኝ። አምላኬን የማመሰግነው የሚያስፈልገኝን ስለሰጠኝ፣ የሚገባኝ ስፍራ ስላደረሰኝ፣ በጉዞዬ ሁሉ ስለረዳኝ፣ በመውጣት መውረዴ፣ በመውደቅ መነሳቴ፣ በመተቸት መወደሴ ሁሉ አብሮኝ ስለነበረ ብቻ አይደለም። የምስጋናዬ ምክንያት ሰውነቴ ነው፤ የምስጋናዬ ምክንያት እኔን እኔ ስላደረገኝ ነው፤ የአድናቆቴ መንስኤ የአባትነት ፍቅሩ፣ የአምላክነት ስጦታው ነው። እራሴን በማውቀው ልክ ለእራሴ መሆን ባልችልም አምላኬን በማውቀው ልክ ግን እለት እለት በቃሉ ለመመራት፣ ትዕዛዙን ለማክበር፣ ይቅርታውን ለማግኘት የምጥር ምስኪን ልጁ ነኝ። አመስጋኝህ ስላደረከኝ አመሰግንሃለሁ፤ ስጦታህን እንድረዳ በረከትህንም እንድመለከት ስላስቻልከኝ ከልቤ አከብርሃለሁ፤ በደካማው ማንነቴም እወድሃለሁ።
አዎ! ጀግናዬ...! ከእራስህ ገር የምታደርገው ንግግር በአስተውሎት አድርገው፤ ከአምላክህ ጋር ስትወያይ ጉዳይ ከልብህ ተወያይ። ሰው አይኘን አላየኝ፣ ሰማኝ አልሰማኝ፣ ስም አወጣልኝ ፈረደብኝ ብለህ አትፍራ። እራስህ ከእራስህና ከአምላክህ በላይ የሚያቅስህ አካል የለም። እራስህ ላይ ብትፈርድ፣ ለእራስህ የግል አቋም ብታበጅ፣ እምነትህን ብትፈትን፣ መንገድ ብትስት፣ ብትሳሳት ቀዳሚው ሃላፊነት የእንደሆነ አስተውል። ከእራስህና ከደጉ አባትህ በቀር ማንም ስለማይሰማህ የልብ ንግግር አትጨነቅ፤ ከእራስህና ከህያው አምላክህ በቀር ማንም በማያይህ መንፈሳዊ ተግባርህ አትሸማቀቅ። ከእራስህ ጋር ለመነጋገር ነፃ ሁን፤ ከአምላክህ ለመማከር ዘወትር መንፈሰ ጠንካራ ሁን።