አስፈሪ ሰው ሁኑ!
አንድ ሰው ጥሩ ሰውም አስፈሪ ሰውም መሆን አይችልም ብላችሁ የምታስቡ ከሆነ ተሳስታችኋል። በሚገባ ይችላል። በጥሩነት ማስፈራትን የተካኑ ብዙ ሰዎች አሉ። በብዙዎች የሚከበር የሚፈራና የሚደመጥ ሰው መሆን ከፈለጋችሁ በጣም ብዙ ጥረት አይጠበቅባችሁም። አንድ ወሳኝ ነገር ብቻ አድርጉ። ዝምታችሁ እንዲናገር አድርጉ። የዓለማችን በጣም አስፈሪውና አደገኛው ሰው ጮክ ብሎ የሚያወራና በሰው ፊት ለራሱ የተለየ ቦታ የሚሰጥ ሰው አይደለም። ይልቅ አስፈሪው ሰው ሙኑም የማይታወቀውና ከስንት አንዴ የሚናገረው ሰው ነው። አስፈሪ ሰው ብዙ የማይታይ ሃይል አለው። ብዙ አይናገርም ሲናገር ግን በአንዴ ትልቅ ተፅዕኖ መፍጠር ይችላል፣ ብዙ ቦታ አይገኝም በሚገኝበት ስፍራ ግን በብዙዎች ይከበራል፣ ስለራሱ ደጋግሞ አያወራም በተግባር ያሳያል። ሰው እንዲፈራችሁ የምታደርጉት ሰውን ለመጉዳት ወይም በሰው ለመጠቀም ሳይሆን የራሳችሁን ጥቅምና ክብር ለማስጠበቅ ነው። የዋህነትም ሲበዛ እንደ ሬት ይጎመዝዛል። ለራሳችሁ መቆም የማትችሉ የሁሉም ሰው መጠቀሚያና መጫወቻ አትሁኑ።
አዎ! ራሱን የሚጠብቅ አስፈሪ ሰው ሁኑ፤ ራሱን አድኖ ለብዙዎች መትረፍ የሚችል መጥፎ ሰው ሁኑ። ጅብ ካለፈ እንደሚጮሀው ውሻ እንዳትሆኑ ተጠንቀቁ። ከብዙ አቅጣጫ ከተጎዳችሁና ከተበደላችሁ ቦሃላ ዳግም ለመነሳት አትፍጨርጨሩ። አስቀድማችሁ የማይናወጥ ፅኑ ማንነትን ገንቡ፣ ለራሳችሁ ተገን ሁኑ። ምንም አይነት ያለፍቃዳችሁ በህይወታችሁ ውስጥ የሚከናወን ነገር እንዲኖር አትፍቀዱ። አንዳንዴ ባዶ ክብር ያዋርዳል፣ ቀን ቆርጦ ዋጋ ያስከፍላል፣ ሳታስቡት አንገት ያስደፋችኋል። ፍረሃት የታከለበት ክብር ግን ድንበራችሁን ሁሉ ያስጠብቃል፣ ዙሪያችሁን ሁሉ ያፀዳዋል። ሃይላችሁን አሰባስቡ፣ አቅማችሁን አጠናክሩ፣ ደረጃችሁን ጨምሩ፣ የሚያኮራችሁን ስብዕናና ማንነት ገንቡ። በፍረሃት የምታከብሩትን አንድ ሰው አስቡ። ምናልባትም ያን ሰው ትወዱት ይሆናል፣ ትልቅ ቦታ ትሰጡት ይሆናል፣ በዛው ልክም ትፈሩታላችሁ። የምትፈሩት ሊጎዳችሁ ስለሚችል ወይም ልታሸንፉት ስለማትችሉ አይደለም። የምትፈሩት ከእናንተ የላቀ ደረጃን ስላለው ነው፣ በፍረሃት የምታከብሩት ኬት ተነስቶ አንዴት የት እንደደረስ በሚገባ ስለምታውቁ ነው፣ እናንተን ለማስፈራራት ምንም አይነት የተለየ ነገር ስለማያደርግ ነው።
አዎ! ጀግናዬ..! ጥሩ ሰው ሁን በዛው ልክም ለሚንቁህና ለሚሳለቁብህ ሰው አስፈሪ መሆንህን እንዳትረሳ። ለሚወድህ ፍቅርን፣ ለሚያከብርህ ክብርን፣ ጊዜ ለሚሰጥህ ጊዜና ትኩረትን፣ ለሚያስደስትህም ሳቅና ደስታን ትሰጣለህ ለሚንቅህ ግን ክብርን ልትሰጥ አትችልም፣ ለሚያንቋሽሽህ ግን ቦታ ልትሰጥ አትችልም፣ ስምህን ለሚያጠፋው ግን ትኩረትህን ልትሰጠው አትችልም። ምንም ያህል መልካም ብትሆን መልካምነትህ በራሱ የማይሰራበት ስፍራ መኖሩን አስተውል። ለሰዎች ጥሩ ነገር አድርግ፣ ሰዎችን ውደድ፣ ሰዎችን አክብር የራስህን ክብር ግን በየቦታው አትጣል፣ በፍፁም ራስህን ባይተዋር አታድርግ። ለሰዎች ተፋለም ለራስህ ግን ከዛ በላይ ተፋለም፣ ሰዎችን ጠብቅ ራስህን ግን ከዛ በላይ ጠብቅ። ስምህ በጥሩነት ይነሳ፣ ምግባርህ በመልካምነት ይታወቅ ድንበርህ ሲታለፍ ግን ዝም እንደማትል አሳይ። ሰውን አትጥላ፣ ተጎድቼያለሁ ብለህ አቅም የሌለውን ሰው ለመጉት አትነሳ፣ በእውነቱ አዛኝ ልብ ይኑርህ። ነገር ግን አቅምህን ሊገዳደር ለሚመጣው በር ሰባሪ እውነተኛ ማንነትህን አሳየው። አስፈሪ ሰው የሚያስፈራው አንዱ በትዕግስቱ ሲሆን ሌላውም በዝምታው ነው። በዙሪያህ ካሉ ሰዎች ሁሉ ዝምተኛውና ታጋሹ ሰው ሁን፣ የአስፈሪነትን ሃይልም ተጎናፀፍ።
አንድ ሰው ጥሩ ሰውም አስፈሪ ሰውም መሆን አይችልም ብላችሁ የምታስቡ ከሆነ ተሳስታችኋል። በሚገባ ይችላል። በጥሩነት ማስፈራትን የተካኑ ብዙ ሰዎች አሉ። በብዙዎች የሚከበር የሚፈራና የሚደመጥ ሰው መሆን ከፈለጋችሁ በጣም ብዙ ጥረት አይጠበቅባችሁም። አንድ ወሳኝ ነገር ብቻ አድርጉ። ዝምታችሁ እንዲናገር አድርጉ። የዓለማችን በጣም አስፈሪውና አደገኛው ሰው ጮክ ብሎ የሚያወራና በሰው ፊት ለራሱ የተለየ ቦታ የሚሰጥ ሰው አይደለም። ይልቅ አስፈሪው ሰው ሙኑም የማይታወቀውና ከስንት አንዴ የሚናገረው ሰው ነው። አስፈሪ ሰው ብዙ የማይታይ ሃይል አለው። ብዙ አይናገርም ሲናገር ግን በአንዴ ትልቅ ተፅዕኖ መፍጠር ይችላል፣ ብዙ ቦታ አይገኝም በሚገኝበት ስፍራ ግን በብዙዎች ይከበራል፣ ስለራሱ ደጋግሞ አያወራም በተግባር ያሳያል። ሰው እንዲፈራችሁ የምታደርጉት ሰውን ለመጉዳት ወይም በሰው ለመጠቀም ሳይሆን የራሳችሁን ጥቅምና ክብር ለማስጠበቅ ነው። የዋህነትም ሲበዛ እንደ ሬት ይጎመዝዛል። ለራሳችሁ መቆም የማትችሉ የሁሉም ሰው መጠቀሚያና መጫወቻ አትሁኑ።
አዎ! ራሱን የሚጠብቅ አስፈሪ ሰው ሁኑ፤ ራሱን አድኖ ለብዙዎች መትረፍ የሚችል መጥፎ ሰው ሁኑ። ጅብ ካለፈ እንደሚጮሀው ውሻ እንዳትሆኑ ተጠንቀቁ። ከብዙ አቅጣጫ ከተጎዳችሁና ከተበደላችሁ ቦሃላ ዳግም ለመነሳት አትፍጨርጨሩ። አስቀድማችሁ የማይናወጥ ፅኑ ማንነትን ገንቡ፣ ለራሳችሁ ተገን ሁኑ። ምንም አይነት ያለፍቃዳችሁ በህይወታችሁ ውስጥ የሚከናወን ነገር እንዲኖር አትፍቀዱ። አንዳንዴ ባዶ ክብር ያዋርዳል፣ ቀን ቆርጦ ዋጋ ያስከፍላል፣ ሳታስቡት አንገት ያስደፋችኋል። ፍረሃት የታከለበት ክብር ግን ድንበራችሁን ሁሉ ያስጠብቃል፣ ዙሪያችሁን ሁሉ ያፀዳዋል። ሃይላችሁን አሰባስቡ፣ አቅማችሁን አጠናክሩ፣ ደረጃችሁን ጨምሩ፣ የሚያኮራችሁን ስብዕናና ማንነት ገንቡ። በፍረሃት የምታከብሩትን አንድ ሰው አስቡ። ምናልባትም ያን ሰው ትወዱት ይሆናል፣ ትልቅ ቦታ ትሰጡት ይሆናል፣ በዛው ልክም ትፈሩታላችሁ። የምትፈሩት ሊጎዳችሁ ስለሚችል ወይም ልታሸንፉት ስለማትችሉ አይደለም። የምትፈሩት ከእናንተ የላቀ ደረጃን ስላለው ነው፣ በፍረሃት የምታከብሩት ኬት ተነስቶ አንዴት የት እንደደረስ በሚገባ ስለምታውቁ ነው፣ እናንተን ለማስፈራራት ምንም አይነት የተለየ ነገር ስለማያደርግ ነው።
አዎ! ጀግናዬ..! ጥሩ ሰው ሁን በዛው ልክም ለሚንቁህና ለሚሳለቁብህ ሰው አስፈሪ መሆንህን እንዳትረሳ። ለሚወድህ ፍቅርን፣ ለሚያከብርህ ክብርን፣ ጊዜ ለሚሰጥህ ጊዜና ትኩረትን፣ ለሚያስደስትህም ሳቅና ደስታን ትሰጣለህ ለሚንቅህ ግን ክብርን ልትሰጥ አትችልም፣ ለሚያንቋሽሽህ ግን ቦታ ልትሰጥ አትችልም፣ ስምህን ለሚያጠፋው ግን ትኩረትህን ልትሰጠው አትችልም። ምንም ያህል መልካም ብትሆን መልካምነትህ በራሱ የማይሰራበት ስፍራ መኖሩን አስተውል። ለሰዎች ጥሩ ነገር አድርግ፣ ሰዎችን ውደድ፣ ሰዎችን አክብር የራስህን ክብር ግን በየቦታው አትጣል፣ በፍፁም ራስህን ባይተዋር አታድርግ። ለሰዎች ተፋለም ለራስህ ግን ከዛ በላይ ተፋለም፣ ሰዎችን ጠብቅ ራስህን ግን ከዛ በላይ ጠብቅ። ስምህ በጥሩነት ይነሳ፣ ምግባርህ በመልካምነት ይታወቅ ድንበርህ ሲታለፍ ግን ዝም እንደማትል አሳይ። ሰውን አትጥላ፣ ተጎድቼያለሁ ብለህ አቅም የሌለውን ሰው ለመጉት አትነሳ፣ በእውነቱ አዛኝ ልብ ይኑርህ። ነገር ግን አቅምህን ሊገዳደር ለሚመጣው በር ሰባሪ እውነተኛ ማንነትህን አሳየው። አስፈሪ ሰው የሚያስፈራው አንዱ በትዕግስቱ ሲሆን ሌላውም በዝምታው ነው። በዙሪያህ ካሉ ሰዎች ሁሉ ዝምተኛውና ታጋሹ ሰው ሁን፣ የአስፈሪነትን ሃይልም ተጎናፀፍ።