ተሸናፊ አትሁን!
ያለህን ሁሉ ሰጥተህ ልትሸነፍ አትችልም፤ የእውቀትህን ጥግ ተጠቅመህ ላይሳካልህ አይችልም፣ የምትችለውን ሁሉ አድርገህ ልትወድቅ አትችልም። እያንዳንዱን እርምጃህን ፈጣሪ ያያል፣ ፍላጎትህን በሚገባ ያውቀዋል፣ ጥልቅ ተነሳሽነትህን ጨምሮ ሁሉንም ጥረትህን ፈጣሪ በእርግጥም ይመለከታል። የሚሰጥም የሚነሳም እርሱ እንደሆነ ታውቃለህ፣ ነገሮችን የሚያሳካልህም እርሱ እንደሆነ ታምናለህ። እንግዲያውስ እምነትህን በእርሱ ላይ ጥለህ ካንተ የሚጠበቀውን ማድረግ ስለምን አቃተህ? እንግዲያውስ የሰጠህን ሁሉ አቅም ሳትጠቀም ስለምን የተሻለ ነገር እንዲሰጥህ ትጠብቃለህ? እንግዲያውስ እንዴት ለስንፍናህ እንዲሸልምህ ትመኛለህ? ዘመንህን በሙሉ ያለህን ሁሉ የማውጣት አቅም አይኖርህም፣ እድሜ ልክህን በፈለከው ሰዓት የምትጠቀመው ጥንካሬና ብርታት የለህም። ሰውነትህ ተጠቀምክበትም አልተጠቀምክበትም የሆነ ጊዜ መድከሙና ከቁጥጥርህ ውጪ መሆኑ አይቀርም። ሁሉም ነገር የሚጠቅምህ በትክክለኛው ጊዜ ስትጠቀመው ነው። አሁን ላይ ያለህን ነገር ሁሉ አውጥተህ እንዳትጠቀም የሚያደርግህ ብዙ ነገር ይኖር ይሆናል። ነገር ግን ሁሉም እንዳለ ሆኖ ምርጫህ ሁለት ነው። አንድም ምክንያትህን አልያም ትልቅ አቅምህን።
አዎ! ማንም የማታምንበትን ነገር እንድታደርግ አያስገድድህም፤ ማንም በግድ አሁን ካለህበት ቦታ አያወጣህም። "ሁሉም ነገር ሲወራ ቀላል ነው።" ከማለትህ በፊት ከወሬው በላይ አንተ በተግባር ያደረከውን ነገር በጥልቀት ተመልከት። ለምትፈልገው ነገር ያለህን ሁሉ ሰጥተሃልን? ቢሆንልኝ ብለህ ለምትመኘው ነገር የምትችለውን ሁሉ አድርገሃልን? የምትመኘውን ህይወት እንዳትኖር የከለከሉህን ነገሮች ለማሸነፍ የሚጠበቅብህን ሁሉ አድርገሃልን? አንድ ሰው ያለውን ሁሉ ከሰጠ፣ እስከ ጥግ ከተፋለመ፣ አንድን ነገር መርጦ እሱ ላይ ለዘመናት ከቆየ፣ የእኔ ነው የሚለውን ነገር ሳያቋርጥ ከሰራው በእርሱ ስኬታማ እንደሚሆን አምኖበታልና ማሳካቱ የማይቀር ነው። ይሔ ነገር ላንተም የማይሰራበት ምንም አይነት ምክንያት አይኖርም። አማኝ አይቸኩልምና ፈጣሪ የልፋትህን ውጤት እንደሚሰጥህ ካመንክ፣ ያንተም ምርጫ ነፃ እንደሚያወጣህ ከተማመንክ አትቸኩል፣ አቋራጭ መንገድን አትመልከት፣ ትንሽ ሞክረህ ተስፋ አትቁረጥ፣ ነገሮች እንዳሰብከው ሳይሆኑ ሲቀሩም አታማር። መዋጥ ያለብህን እውነታ ዋጠው። የአቅምህን ሁሉ አውጥተህ ብትሰራ ሁሉም ነገር ይቀየራል።
አዎ! ጀግናዬ..! ራስህን ካልገደብክ፣ በፍቃድህ አቅምህን ካላሳነስክ፣ እምነትህን ካልሸረሸርክ፣ የውስጥ ፍላጎትህን ካልዘጋሀው በእርግጥም ትሸለማለህ፣ የምርም ታሸንፋለህ፣ የእውነትም ውጤታማ ትሆናለህ። "ምክንያት የሚደረድሩ ብፁዓን ናቸው" የተባለ ይመስል ሁሉም ሰው ምክንያት መደርደር ላይ አንደኛ ነው "አምነህ ስራ" ሲባል ግን ፊቱን ያዞራል። አትሸወድ አምነህ ስራ፤ እንዳትበላ የጉብዝናህን ወራት በሚገባ ተጠቀምባቸው። የተለየ ውጤት የሚያመጡት እነዛ የተለየ እምነትና የተለየ አፈፃፀም ያላቸው ሰዎች ብቻ እንደሆኑ እወቅ። ተሸናፊ አትሁን ያለህን ሁሉ ስጥ፣ መካከለኛ አትሁን የምትችለውን ሁሉ አድርግ፣ በሰዎች ጥንካሬና ስኬት አትቅና እንዴት ያንን ጥንካሬና ስኬት ወደ ራስህ ህይወት ማምጣት እንደምትችል መርምር። ሰዎች አዝነውልህ ፍርፋሪ እየሰጡህ የዘመናት አገልጋያቸው እንዲያደርጉህ አትፍቀድ። ራስህን ቻል፣ ራስህን ወደፊት አውጣ፣ በድብቅ አቅምህ እመን፣ ውስጥህ ለሚንቀለቀለው የማያባራ ፍላጎት እድል ስጠው፣ ሳትሰስት አሁኑ በተግባር ግለጠው።
ያለህን ሁሉ ሰጥተህ ልትሸነፍ አትችልም፤ የእውቀትህን ጥግ ተጠቅመህ ላይሳካልህ አይችልም፣ የምትችለውን ሁሉ አድርገህ ልትወድቅ አትችልም። እያንዳንዱን እርምጃህን ፈጣሪ ያያል፣ ፍላጎትህን በሚገባ ያውቀዋል፣ ጥልቅ ተነሳሽነትህን ጨምሮ ሁሉንም ጥረትህን ፈጣሪ በእርግጥም ይመለከታል። የሚሰጥም የሚነሳም እርሱ እንደሆነ ታውቃለህ፣ ነገሮችን የሚያሳካልህም እርሱ እንደሆነ ታምናለህ። እንግዲያውስ እምነትህን በእርሱ ላይ ጥለህ ካንተ የሚጠበቀውን ማድረግ ስለምን አቃተህ? እንግዲያውስ የሰጠህን ሁሉ አቅም ሳትጠቀም ስለምን የተሻለ ነገር እንዲሰጥህ ትጠብቃለህ? እንግዲያውስ እንዴት ለስንፍናህ እንዲሸልምህ ትመኛለህ? ዘመንህን በሙሉ ያለህን ሁሉ የማውጣት አቅም አይኖርህም፣ እድሜ ልክህን በፈለከው ሰዓት የምትጠቀመው ጥንካሬና ብርታት የለህም። ሰውነትህ ተጠቀምክበትም አልተጠቀምክበትም የሆነ ጊዜ መድከሙና ከቁጥጥርህ ውጪ መሆኑ አይቀርም። ሁሉም ነገር የሚጠቅምህ በትክክለኛው ጊዜ ስትጠቀመው ነው። አሁን ላይ ያለህን ነገር ሁሉ አውጥተህ እንዳትጠቀም የሚያደርግህ ብዙ ነገር ይኖር ይሆናል። ነገር ግን ሁሉም እንዳለ ሆኖ ምርጫህ ሁለት ነው። አንድም ምክንያትህን አልያም ትልቅ አቅምህን።
አዎ! ማንም የማታምንበትን ነገር እንድታደርግ አያስገድድህም፤ ማንም በግድ አሁን ካለህበት ቦታ አያወጣህም። "ሁሉም ነገር ሲወራ ቀላል ነው።" ከማለትህ በፊት ከወሬው በላይ አንተ በተግባር ያደረከውን ነገር በጥልቀት ተመልከት። ለምትፈልገው ነገር ያለህን ሁሉ ሰጥተሃልን? ቢሆንልኝ ብለህ ለምትመኘው ነገር የምትችለውን ሁሉ አድርገሃልን? የምትመኘውን ህይወት እንዳትኖር የከለከሉህን ነገሮች ለማሸነፍ የሚጠበቅብህን ሁሉ አድርገሃልን? አንድ ሰው ያለውን ሁሉ ከሰጠ፣ እስከ ጥግ ከተፋለመ፣ አንድን ነገር መርጦ እሱ ላይ ለዘመናት ከቆየ፣ የእኔ ነው የሚለውን ነገር ሳያቋርጥ ከሰራው በእርሱ ስኬታማ እንደሚሆን አምኖበታልና ማሳካቱ የማይቀር ነው። ይሔ ነገር ላንተም የማይሰራበት ምንም አይነት ምክንያት አይኖርም። አማኝ አይቸኩልምና ፈጣሪ የልፋትህን ውጤት እንደሚሰጥህ ካመንክ፣ ያንተም ምርጫ ነፃ እንደሚያወጣህ ከተማመንክ አትቸኩል፣ አቋራጭ መንገድን አትመልከት፣ ትንሽ ሞክረህ ተስፋ አትቁረጥ፣ ነገሮች እንዳሰብከው ሳይሆኑ ሲቀሩም አታማር። መዋጥ ያለብህን እውነታ ዋጠው። የአቅምህን ሁሉ አውጥተህ ብትሰራ ሁሉም ነገር ይቀየራል።
አዎ! ጀግናዬ..! ራስህን ካልገደብክ፣ በፍቃድህ አቅምህን ካላሳነስክ፣ እምነትህን ካልሸረሸርክ፣ የውስጥ ፍላጎትህን ካልዘጋሀው በእርግጥም ትሸለማለህ፣ የምርም ታሸንፋለህ፣ የእውነትም ውጤታማ ትሆናለህ። "ምክንያት የሚደረድሩ ብፁዓን ናቸው" የተባለ ይመስል ሁሉም ሰው ምክንያት መደርደር ላይ አንደኛ ነው "አምነህ ስራ" ሲባል ግን ፊቱን ያዞራል። አትሸወድ አምነህ ስራ፤ እንዳትበላ የጉብዝናህን ወራት በሚገባ ተጠቀምባቸው። የተለየ ውጤት የሚያመጡት እነዛ የተለየ እምነትና የተለየ አፈፃፀም ያላቸው ሰዎች ብቻ እንደሆኑ እወቅ። ተሸናፊ አትሁን ያለህን ሁሉ ስጥ፣ መካከለኛ አትሁን የምትችለውን ሁሉ አድርግ፣ በሰዎች ጥንካሬና ስኬት አትቅና እንዴት ያንን ጥንካሬና ስኬት ወደ ራስህ ህይወት ማምጣት እንደምትችል መርምር። ሰዎች አዝነውልህ ፍርፋሪ እየሰጡህ የዘመናት አገልጋያቸው እንዲያደርጉህ አትፍቀድ። ራስህን ቻል፣ ራስህን ወደፊት አውጣ፣ በድብቅ አቅምህ እመን፣ ውስጥህ ለሚንቀለቀለው የማያባራ ፍላጎት እድል ስጠው፣ ሳትሰስት አሁኑ በተግባር ግለጠው።