ማጣትን ልመዱ!
በህይወታችሁ በአጋጣሚም ሆነ በምክንያት ብዙ ነገር ልታጡ ትችላላችሁ። ያላችሁን ሁሉ ከማጣትም በላይ የሆነ ጊዜ ባዶ እጃችሁን ልትቀሩ ትችላላችሁ። የእኔ የምትላቸውን ሰዎች ታጣላችሁ፣ ለዓመታት የደከማችሁበትን ሀብትና ንብረት ታጣላችሁ፣ ለረጅም ጊዜ የገነባችሁትን ስም በማይረባ ምክንያት ታጣላችሁ፣ ከራሳችሁ ጋር ሰጣገባ ውስጥ ገብታችሁ ራሳችሁን ታጣላችሁ። ነገር ግን ምንም እንኳን ማጣት አብዝቶ ቢጎበኛችሁ፣ ባዶነት ደጋግሞ ቢፈትናችሁ እናንተ ግን በባዶነትም ሆነ በማጣት ውስጥ መኖር እንደምትችሉ ራሳችሁን ማሳመን ይኖርባችኋል። የገነባችሁት ትልቅ ህንፃ ቢፈርስ እንኳን ዳግም ከዜሮ ተነስታችሁ ልትገነቡት እንደምትችሉ ከልባችሁ እመኑ። ምንም ነገር የሚሆነው በምክንያት ነው። ምክንያቱንም ለበጎ ወይም ለመጥፎ ማዋሉ የእናንተ ድርሻ ነው። "ከዛሬ ነገ ልወድቅ ነው፣ ያፈራውትን ንብረት አጣለው፣ የቀረበኝ ሰው ይርቀኛል፣ ሰው አጣለሁ፣ ብቻዬን ቀራለሁ" ብላችሁ ማድረግ ያለባችሁን ነገር ሳታደርጉ እንዳትቀሩ። በዓለም ልታሸንፉ የምትችሉት ከማጣት ቦሃላ ዳግም ቀና ማለት ስትችሉ፣ ከወድቀት ቦሃላም ዳግም ራሳችሁን መገንባት ስትችሉ ብቻ ነው።
አዎ! ማጣትን ልመዱ፣ እርዛቱን፣ ችግሩን፣ ውድቀቱን፣ ባዶነቱን፣ ብቸኝነቱን እያንዳንዱን አሉታዊውን የህይወትን የፈተና ገፅ ልመዱት። የችግር ብዛት ልባችሁን እንዲያስጨንቅ አትፍቀዱ፣ የአንድ ሰሞን ውድቀት ልባችሁን እንዲሰብር አትፍቀዱለት። ወዳጅና ጠላታችሁን ስታገኙ ሳይሆን ስታጡ እንደምትለዩ አስተውሉ። ችግርን መላመድ ጥበብ ነው፣ እስከ ህይወት ፍፃሜ ተቀበሎት መኖር ግን ሞኝነት ነው። ምንም ቢሆንባችሁ ከሁኔታው ጋር አትጋጩ፣ ምንም ቢደርስባችሁ የደረሰባችሁን ለመካድ አትታገሉ። ውስጣችሁ ያርፍ ዘንድ፣ ልባችሁ እንድትረጋጋ፣ አዕምሯችሁ በሚገባ እንዲያስብ ከተፈጠረው ክስተት ጋር ሰላም ፍጠሩ። ወደቀኝም ዞራችሁ ወደ ግራ፣ ወደላይም አላችሁ ወደታች የማይናጥ ፅኑ አቋም ካላችሁ ምንም ሁኔታ ሊያሸብራችሁ አይችልም። ዛሬ ታጣላችሁ ነገ ግን ታገኛላችሁ፣ ዛሬ ትታመማላችሁ ነገ ግን ፈውስን ታገኛላችሁ፣ ዛሬ ትራባላችሁ ነገ እናንተ ጠግባችሁ ብዙዎችን ታጠግባላችሁ፣ ዛሬ ውስጣችሁ ይረበሻል፣ የሚያስደነግጥ ክስተት ይፈጠርባችኋል፣ ከባባድ ክስተቶች ይፈጠሩባችኋል ነገ ግን ሁሉም ይቀየራል ውስጣችሁ ያርፋል፣ ሰላማችሁ ይመለሳል፣ ክስተቶቹም ጥሩ የህይወት ትምህርት ይሆኗችኋል።
አዎ! ጀግናዬ..! አሉልኝ ብለህ የተመካህባቸው ነገሮ ሁሉ ፊታቸውን ቢያዞሩብህ፣ ማንም አይንህን ለአፈር ብልህ እንኳን ለራስህ የሚያዝን ልቦና ካለህ የትኛውንም ነገር ከመሬት አንስተህ መገንባት እንደምትችል እመን። እምነትህም የሚወራ ሳይሆን የሚኖር፣ ማስረጃ የምትፈልግለት ሳይሆን ማስረጃው ፈልጎህ የሚመጣ ነው። በሰው መገፋት፣ መከዳት፣ ከሰው መጣላት፣ ሰው ፊት ክብርና ቦታ ማጣት ሁሉም በአንዴ በህይወትህ ሊከሰቱ ይችላሉ። ለክስተቶቹ የሰጠሀው ቦታና እነርሱን የምትረዳበት መንገድ ግን ሊያስተካክላቸውም ሊያጠፋቸውም ይችላል። "የሆነብኝ ነገር ከአቅሜ በላይ ነው፣ በሆነብኝ ላይ እኔ ስልጣኑ የለኝም።" ከሚለው የውሱንነት ገደብ ራስህን አውጣ። ዓለም ሁሌም ስኬትን አትሰጥህም፣ ምድር ላይ ሁሌም በምቾት አትመላለሱም። ታገኛለህ ታጠላህ፣ ስኬታማ ትሆናለህ በዛው ልክ ደጋግመህ ትወድቃለህ። ስታገኝ በደስታ ጮቤ የምትረግጥ ስታጣም ጥግ ይዘህ የምታለቅስ፣ ሲሳካልህ እዩኝ እዩኝ የምትል ስትወድቅም ደብቁኝ ደብቁኝ የምትል ከሆነ የገዛ ጠላትህ ራስህ እንደሆንክ አስተውል። ከሁኔታዎች ጋር ተስማማ፣ በማጣትም በማግኘት ውስጥ ትክክለኛ ማንነትህን እንዳታጣ ተጠንቀቅ።
በህይወታችሁ በአጋጣሚም ሆነ በምክንያት ብዙ ነገር ልታጡ ትችላላችሁ። ያላችሁን ሁሉ ከማጣትም በላይ የሆነ ጊዜ ባዶ እጃችሁን ልትቀሩ ትችላላችሁ። የእኔ የምትላቸውን ሰዎች ታጣላችሁ፣ ለዓመታት የደከማችሁበትን ሀብትና ንብረት ታጣላችሁ፣ ለረጅም ጊዜ የገነባችሁትን ስም በማይረባ ምክንያት ታጣላችሁ፣ ከራሳችሁ ጋር ሰጣገባ ውስጥ ገብታችሁ ራሳችሁን ታጣላችሁ። ነገር ግን ምንም እንኳን ማጣት አብዝቶ ቢጎበኛችሁ፣ ባዶነት ደጋግሞ ቢፈትናችሁ እናንተ ግን በባዶነትም ሆነ በማጣት ውስጥ መኖር እንደምትችሉ ራሳችሁን ማሳመን ይኖርባችኋል። የገነባችሁት ትልቅ ህንፃ ቢፈርስ እንኳን ዳግም ከዜሮ ተነስታችሁ ልትገነቡት እንደምትችሉ ከልባችሁ እመኑ። ምንም ነገር የሚሆነው በምክንያት ነው። ምክንያቱንም ለበጎ ወይም ለመጥፎ ማዋሉ የእናንተ ድርሻ ነው። "ከዛሬ ነገ ልወድቅ ነው፣ ያፈራውትን ንብረት አጣለው፣ የቀረበኝ ሰው ይርቀኛል፣ ሰው አጣለሁ፣ ብቻዬን ቀራለሁ" ብላችሁ ማድረግ ያለባችሁን ነገር ሳታደርጉ እንዳትቀሩ። በዓለም ልታሸንፉ የምትችሉት ከማጣት ቦሃላ ዳግም ቀና ማለት ስትችሉ፣ ከወድቀት ቦሃላም ዳግም ራሳችሁን መገንባት ስትችሉ ብቻ ነው።
አዎ! ማጣትን ልመዱ፣ እርዛቱን፣ ችግሩን፣ ውድቀቱን፣ ባዶነቱን፣ ብቸኝነቱን እያንዳንዱን አሉታዊውን የህይወትን የፈተና ገፅ ልመዱት። የችግር ብዛት ልባችሁን እንዲያስጨንቅ አትፍቀዱ፣ የአንድ ሰሞን ውድቀት ልባችሁን እንዲሰብር አትፍቀዱለት። ወዳጅና ጠላታችሁን ስታገኙ ሳይሆን ስታጡ እንደምትለዩ አስተውሉ። ችግርን መላመድ ጥበብ ነው፣ እስከ ህይወት ፍፃሜ ተቀበሎት መኖር ግን ሞኝነት ነው። ምንም ቢሆንባችሁ ከሁኔታው ጋር አትጋጩ፣ ምንም ቢደርስባችሁ የደረሰባችሁን ለመካድ አትታገሉ። ውስጣችሁ ያርፍ ዘንድ፣ ልባችሁ እንድትረጋጋ፣ አዕምሯችሁ በሚገባ እንዲያስብ ከተፈጠረው ክስተት ጋር ሰላም ፍጠሩ። ወደቀኝም ዞራችሁ ወደ ግራ፣ ወደላይም አላችሁ ወደታች የማይናጥ ፅኑ አቋም ካላችሁ ምንም ሁኔታ ሊያሸብራችሁ አይችልም። ዛሬ ታጣላችሁ ነገ ግን ታገኛላችሁ፣ ዛሬ ትታመማላችሁ ነገ ግን ፈውስን ታገኛላችሁ፣ ዛሬ ትራባላችሁ ነገ እናንተ ጠግባችሁ ብዙዎችን ታጠግባላችሁ፣ ዛሬ ውስጣችሁ ይረበሻል፣ የሚያስደነግጥ ክስተት ይፈጠርባችኋል፣ ከባባድ ክስተቶች ይፈጠሩባችኋል ነገ ግን ሁሉም ይቀየራል ውስጣችሁ ያርፋል፣ ሰላማችሁ ይመለሳል፣ ክስተቶቹም ጥሩ የህይወት ትምህርት ይሆኗችኋል።
አዎ! ጀግናዬ..! አሉልኝ ብለህ የተመካህባቸው ነገሮ ሁሉ ፊታቸውን ቢያዞሩብህ፣ ማንም አይንህን ለአፈር ብልህ እንኳን ለራስህ የሚያዝን ልቦና ካለህ የትኛውንም ነገር ከመሬት አንስተህ መገንባት እንደምትችል እመን። እምነትህም የሚወራ ሳይሆን የሚኖር፣ ማስረጃ የምትፈልግለት ሳይሆን ማስረጃው ፈልጎህ የሚመጣ ነው። በሰው መገፋት፣ መከዳት፣ ከሰው መጣላት፣ ሰው ፊት ክብርና ቦታ ማጣት ሁሉም በአንዴ በህይወትህ ሊከሰቱ ይችላሉ። ለክስተቶቹ የሰጠሀው ቦታና እነርሱን የምትረዳበት መንገድ ግን ሊያስተካክላቸውም ሊያጠፋቸውም ይችላል። "የሆነብኝ ነገር ከአቅሜ በላይ ነው፣ በሆነብኝ ላይ እኔ ስልጣኑ የለኝም።" ከሚለው የውሱንነት ገደብ ራስህን አውጣ። ዓለም ሁሌም ስኬትን አትሰጥህም፣ ምድር ላይ ሁሌም በምቾት አትመላለሱም። ታገኛለህ ታጠላህ፣ ስኬታማ ትሆናለህ በዛው ልክ ደጋግመህ ትወድቃለህ። ስታገኝ በደስታ ጮቤ የምትረግጥ ስታጣም ጥግ ይዘህ የምታለቅስ፣ ሲሳካልህ እዩኝ እዩኝ የምትል ስትወድቅም ደብቁኝ ደብቁኝ የምትል ከሆነ የገዛ ጠላትህ ራስህ እንደሆንክ አስተውል። ከሁኔታዎች ጋር ተስማማ፣ በማጣትም በማግኘት ውስጥ ትክክለኛ ማንነትህን እንዳታጣ ተጠንቀቅ።