ፈቃድህ ፈቃዴ ይሁን!
ከራስ ጋር ንግግር፦ "ለራሴ የማውቅ ይመስለኝ ነበር ነገር ግን በፍፁም አላውቅም፤ የሚሆነኝን መምረጥ የምችል፣ የሚገባኝን የማደርግ ይመስለኝ ነበር። ነገር ግን ምርጫዬ ስህተት ነበር፣ ድርጊቴ መጥፎ ነበር። እንግዲ ትናንት ተሳሳትኩ፣ ትናንት ወደቅኩ፣ በማይሆንኝ መንገድ ተጓዝኩ፣ የማይሆነኝን ተግባር ፈፀምኩ ዛሬ ግን ያንተን ፍቃድ ላስቀድም ወደድኩ፣ አሁን ግን ባንተ ቀዳሚነት ልከተልህ ወሰንኩ። ለራሴ የማስበው ትልቅ እንደሆነ አስብ ነበር አንተ ያሰብክልኝን ስመለከት ግን ምንያህል ለራሴ በትንሹ እንዳሰብኩ ተረዳው። በእውቀቷ የምትመካ ነፍስ ከእውቀቷ በላይ ጠላት የላትም፣ ለራሴ ከእኔ በላይ የሚውቅ የለም ያለ ሰው የፈጣሪውን በረከት የሚርቅ ሰው ነው። ብዙ ጊዜ "እኔ ያልኩት ብቻ ካልሆነ፣ የእኔ ምርጫ ብቻ ነው ትክክል፣ በእኔ ህይወት ማንም አይመለከተውም" ብዬ ፎክሬ ነበር። የሆንኩትን ስሆን የደረሰብኝ ሲደርስብኝ ግን መታረምን መርጬያለሁ፣ ዳግም ላለመውደቅ ራሴን ጠብቄያለሁ። ብቻዬን እንደሆንኩ ሳስብ የመንፈስ ድካሜ ሊጥለኝ ይሞክራል፣ ያንተ ፍቃድ አለማስተዋሌ ሲታወቀኝ ተነሳሽነቴ ሁሉ ይጠፋል።
አዎ! ፈቃድህ ፈቃዴ ይሁን፤ ምርጫህ ምርጫዬ ይሁን፣ ፍላጎትህ ፍላጎቴ ይሁን። አንተ እጄን ይዘህ ምራኝ፣ በጨለማው በዱር በቀደሉ፣ አቀበት ቁልቁለቱ በአውላላው ሜዳ ላይ፣ በችግር በመከራ በምቾቱ በእጦቱ ሁሉ አንተ ከፊቴ ቅደምልኝ። ያ ፍፁም ሃሳብህ በእኔ ላይ ይደረግ፣ ያ ምስራችን የሚያመጣልኝ፣ ብርታትን የሚድለኝ፣ ውስጤን በሃሴት የሚሞላው፣ ልቤን የሚያሞቀው ምርጫህ በእኔ ላይ ይሁን። ከእቅፍህ ወጥቼ ዳግም መሰቃየትን አልፈልግም፣ ህግህን ጥሼ እንደገና ዋጋ መክፈል አልፈልግም። ምራኝ ብዬ እጄን ሰጥቼሃለሁ፣ መንገድህ መንገዴ ይሁን ብዬ ወዳንተ ቀርቤያለሁ። ውሳኔዬ ትልቅ ነውና እንዲሁ መፈፀም ቢከብደኝ እንኳን አንተ በእኔ ላይ አድረህ ፈፅምልኝ። ለዓመታት የታሰርኩበት መጥፎም ጥሩም ልማድ አለኝ። ከእሱም በአንዴ ነቅዬ መውጣት ይሳነኝ ይሆናል፣ አንተ ግን እርሱን ማድረግ ትችላለህና ነቅለህ አስወጣኝ፣ እኔንም ገፍትረህ ወደ መረጥክልኝ ጎራ ቀላቅለኝ። አቅሜ አንተ ነህ፣ ብርታቴ አንተ ነህ።"
አዎ! ጀግናዬ..! ረጅም ርቀት ሩቅ መንገድ በራስህ ምርጫ በራስህ ውሳኔ ተጉዘሃል፣ ያለማንም ጣልቃገብነት፣ ያለማንም አስገጅነት በራስህ ፍቃድ ብዙ ስህተቶችን ፈፅመሃል፣ ዛሬ ላይ ልታነሳቸው ይቅርና ልታስባቸው እንኳን የማትደፍራቸውን ተግባራት ፍፅመሃል። ምርጫና ውሳኔዎችህ ላይ የአምላክ ፍቃድ፣ የእርሱም ጣልቃገብነት ቢኖርበት ዛሬ በትናንት ምርጫዎችህ ባላፈርክ፣ ስራዎችህንም ለመናገር ባላፈርክ ነበር። ማንም ሰው መንፈሱ ሲደሀይ ስጋው መራመድ ያቅተዋል፣ ውስጡ በባዶነት ሲሞላ ሰላምና መረጋጋት ይርቀዋል። መንፈሳዊ ህይወትህን ችላ ብለህ፣ ከፈጣሪህ ጋር ያለህን ግንኙነት ረስተህ፣ ዓለምና ዓለምን ብቻ መርጠህ በፍፁም ረፍትና ሰላምን ልታገኝ አትችልም። መንፈሳዊ እድገት የሌለበት ህይወት ባዶ ነው፣ እግዚአብሔር አምላክ ያልባረከው ቤት ተስፋቢስ ነው። ያለምንም ክፍያ ያገኘሀውን ጊዜ ለሰጪው ለመስጠት አትሰስት፣ ከአምላክህ ጋር በፍቅር ውደቅ፣ የእጆችህ ስራዎችም ይባረኩልህ ዘንድ ፍላጎትህን በርሱ ፍቃድ ላይ አፅና።
ከራስ ጋር ንግግር፦ "ለራሴ የማውቅ ይመስለኝ ነበር ነገር ግን በፍፁም አላውቅም፤ የሚሆነኝን መምረጥ የምችል፣ የሚገባኝን የማደርግ ይመስለኝ ነበር። ነገር ግን ምርጫዬ ስህተት ነበር፣ ድርጊቴ መጥፎ ነበር። እንግዲ ትናንት ተሳሳትኩ፣ ትናንት ወደቅኩ፣ በማይሆንኝ መንገድ ተጓዝኩ፣ የማይሆነኝን ተግባር ፈፀምኩ ዛሬ ግን ያንተን ፍቃድ ላስቀድም ወደድኩ፣ አሁን ግን ባንተ ቀዳሚነት ልከተልህ ወሰንኩ። ለራሴ የማስበው ትልቅ እንደሆነ አስብ ነበር አንተ ያሰብክልኝን ስመለከት ግን ምንያህል ለራሴ በትንሹ እንዳሰብኩ ተረዳው። በእውቀቷ የምትመካ ነፍስ ከእውቀቷ በላይ ጠላት የላትም፣ ለራሴ ከእኔ በላይ የሚውቅ የለም ያለ ሰው የፈጣሪውን በረከት የሚርቅ ሰው ነው። ብዙ ጊዜ "እኔ ያልኩት ብቻ ካልሆነ፣ የእኔ ምርጫ ብቻ ነው ትክክል፣ በእኔ ህይወት ማንም አይመለከተውም" ብዬ ፎክሬ ነበር። የሆንኩትን ስሆን የደረሰብኝ ሲደርስብኝ ግን መታረምን መርጬያለሁ፣ ዳግም ላለመውደቅ ራሴን ጠብቄያለሁ። ብቻዬን እንደሆንኩ ሳስብ የመንፈስ ድካሜ ሊጥለኝ ይሞክራል፣ ያንተ ፍቃድ አለማስተዋሌ ሲታወቀኝ ተነሳሽነቴ ሁሉ ይጠፋል።
አዎ! ፈቃድህ ፈቃዴ ይሁን፤ ምርጫህ ምርጫዬ ይሁን፣ ፍላጎትህ ፍላጎቴ ይሁን። አንተ እጄን ይዘህ ምራኝ፣ በጨለማው በዱር በቀደሉ፣ አቀበት ቁልቁለቱ በአውላላው ሜዳ ላይ፣ በችግር በመከራ በምቾቱ በእጦቱ ሁሉ አንተ ከፊቴ ቅደምልኝ። ያ ፍፁም ሃሳብህ በእኔ ላይ ይደረግ፣ ያ ምስራችን የሚያመጣልኝ፣ ብርታትን የሚድለኝ፣ ውስጤን በሃሴት የሚሞላው፣ ልቤን የሚያሞቀው ምርጫህ በእኔ ላይ ይሁን። ከእቅፍህ ወጥቼ ዳግም መሰቃየትን አልፈልግም፣ ህግህን ጥሼ እንደገና ዋጋ መክፈል አልፈልግም። ምራኝ ብዬ እጄን ሰጥቼሃለሁ፣ መንገድህ መንገዴ ይሁን ብዬ ወዳንተ ቀርቤያለሁ። ውሳኔዬ ትልቅ ነውና እንዲሁ መፈፀም ቢከብደኝ እንኳን አንተ በእኔ ላይ አድረህ ፈፅምልኝ። ለዓመታት የታሰርኩበት መጥፎም ጥሩም ልማድ አለኝ። ከእሱም በአንዴ ነቅዬ መውጣት ይሳነኝ ይሆናል፣ አንተ ግን እርሱን ማድረግ ትችላለህና ነቅለህ አስወጣኝ፣ እኔንም ገፍትረህ ወደ መረጥክልኝ ጎራ ቀላቅለኝ። አቅሜ አንተ ነህ፣ ብርታቴ አንተ ነህ።"
አዎ! ጀግናዬ..! ረጅም ርቀት ሩቅ መንገድ በራስህ ምርጫ በራስህ ውሳኔ ተጉዘሃል፣ ያለማንም ጣልቃገብነት፣ ያለማንም አስገጅነት በራስህ ፍቃድ ብዙ ስህተቶችን ፈፅመሃል፣ ዛሬ ላይ ልታነሳቸው ይቅርና ልታስባቸው እንኳን የማትደፍራቸውን ተግባራት ፍፅመሃል። ምርጫና ውሳኔዎችህ ላይ የአምላክ ፍቃድ፣ የእርሱም ጣልቃገብነት ቢኖርበት ዛሬ በትናንት ምርጫዎችህ ባላፈርክ፣ ስራዎችህንም ለመናገር ባላፈርክ ነበር። ማንም ሰው መንፈሱ ሲደሀይ ስጋው መራመድ ያቅተዋል፣ ውስጡ በባዶነት ሲሞላ ሰላምና መረጋጋት ይርቀዋል። መንፈሳዊ ህይወትህን ችላ ብለህ፣ ከፈጣሪህ ጋር ያለህን ግንኙነት ረስተህ፣ ዓለምና ዓለምን ብቻ መርጠህ በፍፁም ረፍትና ሰላምን ልታገኝ አትችልም። መንፈሳዊ እድገት የሌለበት ህይወት ባዶ ነው፣ እግዚአብሔር አምላክ ያልባረከው ቤት ተስፋቢስ ነው። ያለምንም ክፍያ ያገኘሀውን ጊዜ ለሰጪው ለመስጠት አትሰስት፣ ከአምላክህ ጋር በፍቅር ውደቅ፣ የእጆችህ ስራዎችም ይባረኩልህ ዘንድ ፍላጎትህን በርሱ ፍቃድ ላይ አፅና።