👉 ልዩ ዕለት
የዛሬቱ ዕለት ከሁሉም ዕለታት ልዩ ዕለት ናት የድንቅ ምሥጢር መገለጫ ልዩ ዕለት
ወይእኅዛሁ ሰብዑ አንስት ለአሐዱ ብእሲ እንዲል ሰባት ሴቶች አንዱን ወንድ ይይዙታል ማለትም በሰባቱ ዕለታት ተፈጥረው የተመለኩ ፍጥረታት የአምላክን አምላክነት ይመሰክራሉ ማለት ነው የመሰከሩባት ልዩ ዕለት
አንድም ሰባቱ ተአምራት ተፈጽመው ጌትነቱን የሚሰብኩባት ልዩ ዕለት
➟ ፀሐይ የጨለመባት ልዩ ዕለት
➟ጨረቃ በደም የታጠበችባት ልዩ ዕለት
➟ከዋክብትም ጽናተቸውን የለቀቁባት ልዩ ዕለት
➟ካምስት መቶ ብቅ ከስድስት መቶ ዝቅ የሚሉ ሙታን ከመስቀሉ እግርጌ እንደ አሸን የፈሉባት ልዩ ዕለት
➟ መቃብራት የተከፈቱባት ሙታን የተነሱባት ልዩ ዕለት
➟ ድንጋዮች የተፈተቱባት ልዩ ዕለት
➟የቤተ መቅደሱ ከሦስት ካራት የተቀደደባት ልዩ ዕለት
➣ መድኀን ክርስቶስ ቅድስት ነፍሱን ከቅድስት ሥጋው በፈቃዱ የለየባት ልዩ ዕለት
➣ ምእመንንም የሞሸረባት ልዩ ዕለት
➣ እጁን በደም ነክሮ ለኖረ ሽፍታ ወንበዴም ምሕረት የወረደባት
➣ገነት ለመጀመሪያ ጊዜ የተከፈተችባት ልዩ ዕለት ወዘተርፈ
በአጠቃላይ ከሰው ልጆች ይልቅ ደግሞ ግዕዛን የሌላቸው ፍጥረታት እግዚአብሔርነቱን የመሰከሩባት ልዩ ዕለት ናት
➣ እኛስ የፀሐይን ያህል መስክረን ይሆን ?
የጨረቃን ያህልስ እንባ አልቅሰን ደም ደም አልቅሰን እዝኅ በማለቅስ በእንባ በደም በመራጨት መስክረን ይሆን ?
የከዋክብትን ያህልስ መስክረን ይሆን ?
የሙታንን ያህልስ
የድንጋዮችን ያህልስ ልባችን ተሰንጥቆ ይሆን ?
የመጋረጃውን ያህል ምን ያህል ተብሰክስከን ይሆን ?
➟ ነገሩስ ከእነዚህ ሁሉ እንደምናንስ ምንም እንደማይሰማን ቅዱስ ኤፍሬም እንዲህ ገልጾታል
እስኪ እንስማው
"ፀሐይ ሰኢኖ ጽዕለተ እግዚእ ጸዊረ ብርሃኖ ለጽልመት ሜጠ ወንሕነሰ እም ጽልመት አከይነ ወኢ እምልብነ ንፈቱ ንትነሳሕ መንጦላዕተ ቤተ መቅደስ እንዘ አልቦ ዘአበሰ ርእሶ ሰጠጠ ወንሕነሰ በእንተ ኀጢአትነ ኢተነሳሕነ ወኢ በልብነ ንፈቱ አጻብአ ፈረስ ወፀር ተንሢኦሙ አማሰኑ ብሔረነ ከመ ለእግዚአብሔር ፈሪሀነ ውስተ ንስሓ ንግባእ ወበዘሂ ኢተነሳሕነ ወኢደንገፅነ ንትነሳሕ እንከ"
➟ትርጉም
ፀሐይ እንኳ የጌታውን ስድብ መሸከም ተስኖት ብርሃኑን ወደጨለማ ለውጧል እኛ ግን ከጨለማ ከፍተናል ከልባችንም ንስሓ ለመግባት አልወድም የቤተ መቅደሱም መጋረጃ በደል ሳይኖርበት ራሱን ቀዷል እኛ ግን ስለኀጢአታችን ከልባችን ንስሓ ለመግባት አንወድም እግዚአብሔርንም በመፍራት ንስሓ ወደንስሓ እንድንመለስ የጠላትና የፈረስ እጣቶች ተነስተው ሀገራችንን አጥፍተዋል በዚህም ንስሓ አልገባንም ንስሓ ለመግባትም እንግዲህ አልደነገጥንም ።
ወንበዴውን የማረ ጌታ ይማረን
ከአብርሃም ፈቃዴ
የዛሬቱ ዕለት ከሁሉም ዕለታት ልዩ ዕለት ናት የድንቅ ምሥጢር መገለጫ ልዩ ዕለት
ወይእኅዛሁ ሰብዑ አንስት ለአሐዱ ብእሲ እንዲል ሰባት ሴቶች አንዱን ወንድ ይይዙታል ማለትም በሰባቱ ዕለታት ተፈጥረው የተመለኩ ፍጥረታት የአምላክን አምላክነት ይመሰክራሉ ማለት ነው የመሰከሩባት ልዩ ዕለት
አንድም ሰባቱ ተአምራት ተፈጽመው ጌትነቱን የሚሰብኩባት ልዩ ዕለት
➟ ፀሐይ የጨለመባት ልዩ ዕለት
➟ጨረቃ በደም የታጠበችባት ልዩ ዕለት
➟ከዋክብትም ጽናተቸውን የለቀቁባት ልዩ ዕለት
➟ካምስት መቶ ብቅ ከስድስት መቶ ዝቅ የሚሉ ሙታን ከመስቀሉ እግርጌ እንደ አሸን የፈሉባት ልዩ ዕለት
➟ መቃብራት የተከፈቱባት ሙታን የተነሱባት ልዩ ዕለት
➟ ድንጋዮች የተፈተቱባት ልዩ ዕለት
➟የቤተ መቅደሱ ከሦስት ካራት የተቀደደባት ልዩ ዕለት
➣ መድኀን ክርስቶስ ቅድስት ነፍሱን ከቅድስት ሥጋው በፈቃዱ የለየባት ልዩ ዕለት
➣ ምእመንንም የሞሸረባት ልዩ ዕለት
➣ እጁን በደም ነክሮ ለኖረ ሽፍታ ወንበዴም ምሕረት የወረደባት
➣ገነት ለመጀመሪያ ጊዜ የተከፈተችባት ልዩ ዕለት ወዘተርፈ
በአጠቃላይ ከሰው ልጆች ይልቅ ደግሞ ግዕዛን የሌላቸው ፍጥረታት እግዚአብሔርነቱን የመሰከሩባት ልዩ ዕለት ናት
➣ እኛስ የፀሐይን ያህል መስክረን ይሆን ?
የጨረቃን ያህልስ እንባ አልቅሰን ደም ደም አልቅሰን እዝኅ በማለቅስ በእንባ በደም በመራጨት መስክረን ይሆን ?
የከዋክብትን ያህልስ መስክረን ይሆን ?
የሙታንን ያህልስ
የድንጋዮችን ያህልስ ልባችን ተሰንጥቆ ይሆን ?
የመጋረጃውን ያህል ምን ያህል ተብሰክስከን ይሆን ?
➟ ነገሩስ ከእነዚህ ሁሉ እንደምናንስ ምንም እንደማይሰማን ቅዱስ ኤፍሬም እንዲህ ገልጾታል
እስኪ እንስማው
"ፀሐይ ሰኢኖ ጽዕለተ እግዚእ ጸዊረ ብርሃኖ ለጽልመት ሜጠ ወንሕነሰ እም ጽልመት አከይነ ወኢ እምልብነ ንፈቱ ንትነሳሕ መንጦላዕተ ቤተ መቅደስ እንዘ አልቦ ዘአበሰ ርእሶ ሰጠጠ ወንሕነሰ በእንተ ኀጢአትነ ኢተነሳሕነ ወኢ በልብነ ንፈቱ አጻብአ ፈረስ ወፀር ተንሢኦሙ አማሰኑ ብሔረነ ከመ ለእግዚአብሔር ፈሪሀነ ውስተ ንስሓ ንግባእ ወበዘሂ ኢተነሳሕነ ወኢደንገፅነ ንትነሳሕ እንከ"
➟ትርጉም
ፀሐይ እንኳ የጌታውን ስድብ መሸከም ተስኖት ብርሃኑን ወደጨለማ ለውጧል እኛ ግን ከጨለማ ከፍተናል ከልባችንም ንስሓ ለመግባት አልወድም የቤተ መቅደሱም መጋረጃ በደል ሳይኖርበት ራሱን ቀዷል እኛ ግን ስለኀጢአታችን ከልባችን ንስሓ ለመግባት አንወድም እግዚአብሔርንም በመፍራት ንስሓ ወደንስሓ እንድንመለስ የጠላትና የፈረስ እጣቶች ተነስተው ሀገራችንን አጥፍተዋል በዚህም ንስሓ አልገባንም ንስሓ ለመግባትም እንግዲህ አልደነገጥንም ።
ወንበዴውን የማረ ጌታ ይማረን
ከአብርሃም ፈቃዴ