የድርገት ዕጣን
በቅዳሴ ጊዜ ፲፫ ዕርገተ ዕጣን አለ፡፡ ከእነዚያ መካከል በድርገት ጊዜ ሁለት ቀሳውስት አንዱ ሥጋውን አንዱ ደሙን እያጠኑ ይወርዳሉ፡፡ አንድ ቄስ ቢሆንም ሁለቱን (ሥጋውንም ደሙንም) ዕያጠነ ይወርዳል፡፡
ምሥጢሩ፦ መዓዛ መለኮቱ እንዳልተለየው ለማጠየቅ ነው፡፡ "አንድም" ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ሽቱ እያረበረቡ ለመገነዛቸው ምሳሌ ነው፡፡ ዐሥራ ሦስቱ ዕርገተ ዕጣን ምዑዝ መለኮት በሥጋ ዐሥራ ሦስቱን ሕማማተ መስቀልን ለመቀበሉ አምሳል ነው፡፡ (ቅዳሴ ሐዋርያት ትርጓሜ ፪፥፫)
ይህችን ቤተ ክርስቲያን ክርቶስን አታውቅም ሲሏት እንደምን አእምሮ ያደማል! ምን ያህል የአእምሮ ጉድለት እንዳለባቸው እያሰብን እናዝንላቸዋለን፡፡
በቅዳሴ ጊዜ ፲፫ ዕርገተ ዕጣን አለ፡፡ ከእነዚያ መካከል በድርገት ጊዜ ሁለት ቀሳውስት አንዱ ሥጋውን አንዱ ደሙን እያጠኑ ይወርዳሉ፡፡ አንድ ቄስ ቢሆንም ሁለቱን (ሥጋውንም ደሙንም) ዕያጠነ ይወርዳል፡፡
ምሥጢሩ፦ መዓዛ መለኮቱ እንዳልተለየው ለማጠየቅ ነው፡፡ "አንድም" ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ሽቱ እያረበረቡ ለመገነዛቸው ምሳሌ ነው፡፡ ዐሥራ ሦስቱ ዕርገተ ዕጣን ምዑዝ መለኮት በሥጋ ዐሥራ ሦስቱን ሕማማተ መስቀልን ለመቀበሉ አምሳል ነው፡፡ (ቅዳሴ ሐዋርያት ትርጓሜ ፪፥፫)
ይህችን ቤተ ክርስቲያን ክርቶስን አታውቅም ሲሏት እንደምን አእምሮ ያደማል! ምን ያህል የአእምሮ ጉድለት እንዳለባቸው እያሰብን እናዝንላቸዋለን፡፡