📖“እንደ ልብህ ይስጥህ፤ ፈቃድህንም ሁሉ ይፈጽምልህ።”
መዝሙር 20፥4
ዳዊት ምርቃቱን ማዝነቡን እንደቀጠለ ነው። “እንደ ልብህ ይስጥህ፤ ፈቃድህንም ሁሉ ይፈጽምልህ።” (መዝ 20፥4) የሚለውን ምርቃት "አሜን! ይሁንልኝ!" እንላለን።
የልባችን ፈቃድ በፈቃዱ ይተካልን። የእርሱ ሀሳብ ሀሳባችንን ይተካው። ውስጣችን "በጎ፣ ደስ በሚያሰኝና ፍፁም በሆነው" ፈቃዱ ይሞላ። ከሚታየው ይልቅ የማይታየውን ማየት ይሁንልን። ከጊዜያዊ ደስታ ይልቅ ዘላለማዊ ሀሴትን እግዚአብሔር ያጎናፅፈን። ኃጢአት የሞላበትን የድንጋዩን ልብ አውጥቶ በፅድቅ የተሞላ የስጋን ልብ ይስጠን።
አሜን! አሜን! አሜን!...
የልባችንን ምኞት እንደ መልካም ፈቃዱ ይስጠን። እንዲህ ቢሆንልኝ ብለን የምናስበው ነገር ሁሉ ይሳካልን። ፈቃዳችንን ሁሉ እግዚአብሔር አምላክ ይፈፅምልን። የሸለቆው ሕይወታችን ያብቃልን። ወደ ከፍታ መውጣታችን ይፍጠንልን። ካለንበት ስፍራ መስፈንጠር ይሁንልን። የውድቀት ዘመናችን ያብቃልን። የከፍታችን ዘመን ይምጣልን። የእሮሮው ጊዜ አክትሞ እልልታችን ይምጣ።
አሜን! አሜን! አሜን!...
Join Our channel ⭐
🔥@Urim7🔥
🔥@Urim7🔥
መዝሙር 20፥4
ዳዊት ምርቃቱን ማዝነቡን እንደቀጠለ ነው። “እንደ ልብህ ይስጥህ፤ ፈቃድህንም ሁሉ ይፈጽምልህ።” (መዝ 20፥4) የሚለውን ምርቃት "አሜን! ይሁንልኝ!" እንላለን።
የልባችን ፈቃድ በፈቃዱ ይተካልን። የእርሱ ሀሳብ ሀሳባችንን ይተካው። ውስጣችን "በጎ፣ ደስ በሚያሰኝና ፍፁም በሆነው" ፈቃዱ ይሞላ። ከሚታየው ይልቅ የማይታየውን ማየት ይሁንልን። ከጊዜያዊ ደስታ ይልቅ ዘላለማዊ ሀሴትን እግዚአብሔር ያጎናፅፈን። ኃጢአት የሞላበትን የድንጋዩን ልብ አውጥቶ በፅድቅ የተሞላ የስጋን ልብ ይስጠን።
አሜን! አሜን! አሜን!...
የልባችንን ምኞት እንደ መልካም ፈቃዱ ይስጠን። እንዲህ ቢሆንልኝ ብለን የምናስበው ነገር ሁሉ ይሳካልን። ፈቃዳችንን ሁሉ እግዚአብሔር አምላክ ይፈፅምልን። የሸለቆው ሕይወታችን ያብቃልን። ወደ ከፍታ መውጣታችን ይፍጠንልን። ካለንበት ስፍራ መስፈንጠር ይሁንልን። የውድቀት ዘመናችን ያብቃልን። የከፍታችን ዘመን ይምጣልን። የእሮሮው ጊዜ አክትሞ እልልታችን ይምጣ።
አሜን! አሜን! አሜን!...
Join Our channel ⭐
🔥@Urim7🔥
🔥@Urim7🔥