. #ፀጋ_ነፃ_እንጂ_ርካሽ_አይደለም!!!
⚡️ ፀጋ ለማይገባው ሰው የሚሰጥ ነፃ ስጦታ ነው።
⚡️ ፀጋ ተቀባዩን የማይመጥን እና የሰጪውን ለጋሽነት የሚያሳይ ድንቅ ነገር ነው።
⚡️ ፀጋ ዋና ዓላማው የአምላክን ህይወት ምድር ላይ እንድንገልጠው የሚያስችል የእግዚአብሔር አቅም ነው።
⚡️ ፀጋ ሰው እድሜ ልኩን ቢለፋ በደሞዝ ወይም በሽልማት ሊያገኘው የማይችል ነፃ እና የእግዚአብሔር የፍቅር ስጦታ ነው።
⚡️ እግዚአብሔር ልጁን እና ከልጁ ጋር መልካሙን ነገር ሁሉ በፀጋ ሰቶናል። ከእግዚአብሔር ያገኘነው ስጦታ በፀጋ እንጂ እግዚአብሔር እኛ ጋር እዳ ስላለበት አይደለም።
“ለገዛ ልጁ ያልራራለት ነገር ግን ስለ ሁላችን አሳልፎ የሰጠው ያው ከእርሱ ጋር ደግሞ ሁሉን ነገር እንዲያው እንዴት አይሰጠንም?”
ሮሜ 8፥32
* የተመረጥነው በፀጋ ነው።
ኤፌሶን 1
⁴ ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን።⁵ በበጎ ፈቃዱ እንደ ወደደ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን።⁶ በውድ ልጁም እንዲያው የሰጠን የጸጋው ክብር ይመሰገን ዘንድ ይህን አደረገ።⁷ በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት።⁸ ጸጋውንም በጥበብና በአእምሮ ሁሉ አበዛልን።⁹ በክርስቶስ ለማድረግ እንደ ወደደ እንደ አሳቡ፥ የፈቃዱን ምሥጢር አስታውቆናልና፤
* የተጠራነው በፀጋ ነው።
“ያዳነን በቅዱስም አጠራር የጠራን እግዚአብሔር ነውና፥ ይህም እንደ ራሱ አሳብና ጸጋ መጠን ነው እንጂ እንደ ሥራችን መጠን አይደለም፤ ይህም ጸጋ ከዘላለም ዘመናት በፊት በክርስቶስ ኢየሱስ ተሰጠን፥”
— 2ኛ ጢሞቴዎስ 1፥9
* የዳነው በፀጋ ነው።
ቲቶ 2
¹¹ ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤
* የምንኖረው በፀጋ ነው።
“ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤”
— ቲቶ 2፥12-13
* የምናገለግለው በፀጋ ነው።
1ኛ ቆሮንቶስ 15
¹⁰ ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ የሆንሁ እኔ ነኝ፤ ለእኔም የተሰጠኝ ጸጋው ከንቱ አልነበረም ከሁላቸው ይልቅ ግን ደከምሁ፥ ዳሩ ግን ከእኔ ጋር ያለው የእግዚአብሔር ጸጋ ነው እንጂ እኔ አይደለሁም።¹¹ እንግዲህስ እኔ ብሆን እነርሱም ቢሆኑ እንዲሁ እንሰብካለን እንዲሁም አመናችሁ።
#የሆነውን_ሁሉ_የምንሆነው_ሁሉ_የምንሆነው_በፀጋ_ነው!!!
🔥
@Urim7🔥
🔥
@Urim7🔥