💐ወድዶኛልና አዳነኝ
📖“ወደ ሰፊ ስፍራም አወጣኝ፤ ወድዶኛልና አዳነኝ።”
መዝሙር 18፥19
አንዱ አካል ከሌላው አካል ጋር ግንኙነት የሚፈጥርበት መንገድ ይለያያል። በሰውኛ መነፅር ሲታይ እነዚህን ሰዎች በአንድ ሕብረት ውስጥ የጨመራቸው የጋራ ፍላጎታቸው ነው። ምን አልባት የግንኙነታቸው መሰረት ገንዘብ፣ ስራ፣ ስልጣን፣ ቁንጅና፣ የትምሕርት ደረጃ ወዘተ ... ሊሆን ይችላል። እነዚህ ከላይ ለመዘርዘር የሞከርናቸው ነገሮች ምን አልባት በፊት እንደነበሩበት ባይቀጥሉና ቢበላሹ፣ ሰዎቹ በፊት የነበራቸውን ሕብረት ይዘው የመቀጠላቸው ነገር ጥያቄ ውስጥ ይገባል።
እግዚአብሔር አምላክ ከሰው ልጆች ጋር ግንኙነትን ሲፈጥር መሰረቱ ፍቅር ነበር። ይህንን ሕብረት ያቋቋመው በሁኔታዎች ላይ ተመርኩዞና ለሰው ልጆች ቅድመ ሁኔታን በማስቀመጥ አልነበረም። ይልቁን ራሱን ተማምኖ ይህንን ስርዓት ዘረጋ። ምክንያቱም “እግዚአብሔር ፍቅር ነውና።” (1ኛ ዮሐ 4፥8) የመንግስቱም መሰረት ከእርሱ ዘንድ የመነጨውን ይህ ፍቅር ሆነ። ይህም ብቻ አይደለም። ፍቅርን የማወቃችን አንፃራችን ሆነ። “እርሱ ስለ እኛ ነፍሱን አሳልፎ ሰጥቶአልና በዚህ ፍቅርን አውቀናል፤” (1ኛ ዮሐ 3፥16)
የሰው ልጅ ከነበረበት የከፍታ ስፍራ በኃጢአት ምክንያት ቁልቁል ተፈጠፈጠ። ኃጢአትም ይዘርረው ዘንድ በፈቃዱ ነጎደ። ነገር ግን ኃጢአትን እንጂ ኃጢአተኛውን የማይጠላው አምላክ ከታላቅ ፍቅሩ የተነሳ የሰው ልጆችን ለማዳን ሲል ሰው ሆኖ ወደዚች ምድር መጣ። የዕዳ ፅፈታችንን በሙሉ ከእኛ ላይ አስወገደልን። “በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው፤ እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ አስወግዶታል፤” (ቆላ 2፥14) ኃጢአታችንን ወስዶ በመስቀል ላይ በመንጠልጠል ዳግም ሕይወትን ሰጠን። “ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ።” (1ኛ ጴጥ 2፥24) ይህ ስለ እኔና እናንተ የተከፈለ ድንቅ መስዋዕትነት ነው። ፍቅር ማለት ይህ ነው! ታዲያ ይህን ቤዛነት በመረዳት ፈቃዳችንን በፈቃዱ ውስጥ በመሰወር ልንመላለስ ይገባል። “ወድዶኛልና አዳነኝ” (መዝ 18፥19) የሚለውም ዝማሬ ዘውትር ትዝታችን ይሁንልን።
🔥@Urim7🔥
🔥@Urim7🔥
📖“ወደ ሰፊ ስፍራም አወጣኝ፤ ወድዶኛልና አዳነኝ።”
መዝሙር 18፥19
አንዱ አካል ከሌላው አካል ጋር ግንኙነት የሚፈጥርበት መንገድ ይለያያል። በሰውኛ መነፅር ሲታይ እነዚህን ሰዎች በአንድ ሕብረት ውስጥ የጨመራቸው የጋራ ፍላጎታቸው ነው። ምን አልባት የግንኙነታቸው መሰረት ገንዘብ፣ ስራ፣ ስልጣን፣ ቁንጅና፣ የትምሕርት ደረጃ ወዘተ ... ሊሆን ይችላል። እነዚህ ከላይ ለመዘርዘር የሞከርናቸው ነገሮች ምን አልባት በፊት እንደነበሩበት ባይቀጥሉና ቢበላሹ፣ ሰዎቹ በፊት የነበራቸውን ሕብረት ይዘው የመቀጠላቸው ነገር ጥያቄ ውስጥ ይገባል።
እግዚአብሔር አምላክ ከሰው ልጆች ጋር ግንኙነትን ሲፈጥር መሰረቱ ፍቅር ነበር። ይህንን ሕብረት ያቋቋመው በሁኔታዎች ላይ ተመርኩዞና ለሰው ልጆች ቅድመ ሁኔታን በማስቀመጥ አልነበረም። ይልቁን ራሱን ተማምኖ ይህንን ስርዓት ዘረጋ። ምክንያቱም “እግዚአብሔር ፍቅር ነውና።” (1ኛ ዮሐ 4፥8) የመንግስቱም መሰረት ከእርሱ ዘንድ የመነጨውን ይህ ፍቅር ሆነ። ይህም ብቻ አይደለም። ፍቅርን የማወቃችን አንፃራችን ሆነ። “እርሱ ስለ እኛ ነፍሱን አሳልፎ ሰጥቶአልና በዚህ ፍቅርን አውቀናል፤” (1ኛ ዮሐ 3፥16)
የሰው ልጅ ከነበረበት የከፍታ ስፍራ በኃጢአት ምክንያት ቁልቁል ተፈጠፈጠ። ኃጢአትም ይዘርረው ዘንድ በፈቃዱ ነጎደ። ነገር ግን ኃጢአትን እንጂ ኃጢአተኛውን የማይጠላው አምላክ ከታላቅ ፍቅሩ የተነሳ የሰው ልጆችን ለማዳን ሲል ሰው ሆኖ ወደዚች ምድር መጣ። የዕዳ ፅፈታችንን በሙሉ ከእኛ ላይ አስወገደልን። “በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው፤ እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ አስወግዶታል፤” (ቆላ 2፥14) ኃጢአታችንን ወስዶ በመስቀል ላይ በመንጠልጠል ዳግም ሕይወትን ሰጠን። “ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ።” (1ኛ ጴጥ 2፥24) ይህ ስለ እኔና እናንተ የተከፈለ ድንቅ መስዋዕትነት ነው። ፍቅር ማለት ይህ ነው! ታዲያ ይህን ቤዛነት በመረዳት ፈቃዳችንን በፈቃዱ ውስጥ በመሰወር ልንመላለስ ይገባል። “ወድዶኛልና አዳነኝ” (መዝ 18፥19) የሚለውም ዝማሬ ዘውትር ትዝታችን ይሁንልን።
🔥@Urim7🔥
🔥@Urim7🔥