በነገራችን ላይ በሥረዓት ዙሪያ እንዴ ኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የሚያምር እና የጥንት ሥርዓት ያለው የለም በተለይ ከንቂያ በፊት ያለው የአባቶች ትምህርት ስታነቡ የዚያኔዋን ቤተክርስቲያን ሥርዓት የምታገኙት ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ካለባበስ ጀምሮ ምናምን..። የግብጽ ቤተ ክርስቲያን በሥርዓት ዙሪያ እንኳን ከኢትዮጵያ መወዳደር አትችልም ። በነሱ የምቀናው ካህናቶቹ ከአማኙ ጋ ያላቸው ግንኙነት ፓትሪያሪኮቹ የሚጽፋቸው መጸሐፎች ስታዩ የእኛ ግን ምን ሁነው ነው ትላላችሁ የነሱን ትጋት አይታችሁ በዚህ በዚህ እቀናለሁ እና ደግሞ ሁሉም ለሥራ ያላቸው ትጋት ሲባል እሰማለሁ