✿✟ የ҈ ዳ҈ ዊ҈ ት҈ ዜ҈ ማ҈ ✟✿


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


╭━─━─━─≪✠≫─━─━─━╮╭━─━─━─
ገና እንዘምራለን
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ የመዝሙር ግጥሞችን ወረባቶችን ከነዜማቸው ለማግኘት @Zemaryan
╰━─━─━─≪✠≫─━─━─━╯╰━─━─━─
ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት ጥያቄ> creator ለማግኝት @kidanemiherat_bot
@yita21
@Binyam
https://youtu.be/Fz4JARE6-DI

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций






💕#ሐምሌ_19_እንኳን_አደረሳችሁ💕

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት ኢየሉጣንና ልጇን ቅዱስ ቂርቆስን ከሞት አደጋ እንደታደገበት... የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤል
፣ ቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ የቅድስት ኢየሉጣ ተራዳኢነት ጸሎት አይለየን።

╔═★══════════📄══╗
⛓         @Zemaryan          ⛓
⛓         @Zemarya
n          ⛓
⛓         @Zemaryan          ⛓
╚══📃══════════★═╝
         ʟɪɴᴋ 👆 ᴛᴀʙ . sʜᴀʀᴇ


" ባልተጠበቀና ባልተለመደ ሁኔታ ብቅ ብቅ ሲሉ የሚታዩት ራስን በራስ የመሾም አባዜ መገታት አለባቸው " - ቅዱስ ፓትርያርኩ

ቅዱስ ፓትርያርኩ ፤ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን " ራስን በራስ የመሾም " አባዜ መገታት አለባቸው ሲሉ አሳሰቡ።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ  ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ዛሬ በተካሄደው ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት ስርዓት ላይ ንግግር አሰምተው ነበር።

በንግግራቸው ላይም ፤ " በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ባልተጠበቀና ባልተለመደ ሁኔታ ብቅ ብቅ ሲሉ የሚታዩት ራስን በራስ የመሾም አባዜ መገታት አለባቸው " ብለዋል።

" ማንኛውም ችግር በውይይትና በምክክር የተበደለውንም በትክክል በመካስ መፈታት ይገባዋል! " ያሉት ቅዱስነታቸው " ከዚህ ውጭ በጥፋት ላይ ጥፋት እየተከሠተ የቤተ ክርስቲያንን ህልውና የሚፈታተን ድርጊት ማቆም አለብን " ሲሉ አሳስበዋል።

ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተ ክርስቲያንን አንድነትና ቀኖና ለመጠበቅና ለማስጠበቅ ባደረገው ጥረት፣ እንደዚሁም ኦርቶዶክሳዊው ሕዝበ ክርስቲያን ባቀረበው አቤቱታ ከዚህ ቀደም የተፈጸመው የቀኖና ጥሰት ታርሞ በዛሬው ዕለት ትክክለኛውን ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንና ቀኖናዊ ሕግን የጠበቀ ሥርዓተ ሢመት መከናወኑን የገለፁት ቅዱስ ፓትርያርኩ ይህ በመሆኑ " ለመላው ሕዝበ ክርስቲያን እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን " ብለዋል።

" ለወደፊትም ለሀገርና ለቤተ ክርስቲያን አንድነት በሚጠቅም ጉዳይ ሁሉ ፤ በዚህ ዓይነት በውይይትና በምክክር ብቻ እየፈታን ሕዝባችን በመንፈስና በልማት የሚያድግበትን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር በጋራ እንድንሰራ ጥሪያችንን እያቀረብን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡ " ሲሉ ገልጸዋል።

(የቅዱስ ፓትርያርኩ ሙሉ ንግግር ከላይ ተያይዟል)




ቅዱስ ፓትርያርኩ ወደ አዲስ አበባ ተመለሱ።
---------------------------------------------------


ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና  ከሀገር ሽማግሌዎች  ጋር  በክልል ትግራይ መቐለ የነበራቸውን ቆይታ አጠናቀው ወደ አዲስ አበባ ተመልሷል ።

ምንጭ: ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት


👑 መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ  👑   ሰኔ 30

➡️ የዓለም ብርሃን ለሆነው ባሕታዊ ፤ በክብረ ፈጣሪው ለተከበበ ንዑድ ክቡር አባታችን ገባሬ ተአምራት ወመንክራት፤ ሴቶች ከወለዷቸው ቅዱሳን ወገን እሱን የሚበልጥ ማንም እንደሌለና እንደማይኖር አምላካችን በሕያው ቃሉ ለመሰከረለት እንቁ አገልጋይና ጽኑ የእውነት ሰማዕት ለሆነው፤ ክብሩ ማንነቱ ከኹሉ ለላቀው የክርስቶስ መንገድ ጠራጊ የአዲሱ የምህረት ዘመን መሸጋገሪያ ድልድይ፡ የአሮጌው ብሉይ ዘመን ፍጻሜ ማኅተም ለሆነው መምህር መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ዓመታዊ የልደት በዓል እንኳን አደረሳችሁ ! እንኳን አደረሳችሁ! እንኳን አደረሳችሁ ።

➡️ አባታችን መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በሰማዕትነት ፍጻሜው ወቅት "አቤቱ ጌታዬ ሆይ በቃል ኪዳኔ አምነው ስሜን የሚጠሩ መታሰቢያየን የሚያደርጉ ኃጥአንን ሁሉ ማርልኝ!" ብሎ በትህትና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በለመነው መሠረት...

➡️ ጌታችንም በማይታበለው የከበረ ቃሉ፦ በስሙ የተማጸነ፤ ዝክሩን ያዘከረ፤ መታሰቢያውን ያደረገ፤ ስሙን የጠራ በቃልኪዳኑ የታመነ፤ ወዘተ... ወዳጆቹንም በወር በወር የበዓሉ መታሰቢያ ዕለት በውሃ ላይ ገድሉን አንብበው ቢጠመቁ ወር እስከ ወር የሰሩትን ኃጥአት ይቅር እንደሚላቸው...

➡️ ያም ባይሆን መስከረም 2፤ ሰኔ 30 በአመታዊ ክብረ በዓሉ ገድሉ በተነበበበት ማየ ጸሎት (ውሃ) አምኖ፣ ታምኖ፣ ተማጽኖ፣ በሠራው ኃጢአት አዝኖ ተጸጽቶ የተጠመቀ ማንም ይሁን ማን እንደ እግዚአብሔር ቸርነት ከዓመት እስከ ዓመት የፈጸመው ኃጢአቱ ቀልጦ ጠፍቶለት ያለወቀሳ ያለ ከሰሳ ሰተት ብሎ መንግሥተ ሰማያት እንዲገባ ይህንንና የመሳሰለውን ቃልኪዳን ከአምላኩ ተቀብሏል።

➡️ነገር ግን ይህ ሁሉ የሚሆነው በእምነትና በእውነት ሲጠቀሙበት ነውና እንደቃልኪዳኑ ኖረን በቃልኪዳኑ ለመጠቀም ያብቃን! አሜን። 🙏
.ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉን 👇
╔═★══════════📄══╗
⛓         @Zemaryan          ⛓
⛓         @Zemaryan          ⛓
⛓         @Zemaryan          ⛓
╚══📃══════════★═╝
         ʟɪɴᴋ 👆 ᴛᴀʙ . sʜᴀʀᴇ


እግዚአብሔር ❤️

ሲገድሉትም የዋህ ነው፣
ሳይገለጥ ይታወቃል፡፡
ሳይታወቅም ግልጥ ነው፡፡
ሲርቁት ይቀርባል፣
ሲጠሉት ይወድዳል፡፡
አጥሩ ነበልባል ነው ቤቱ ውኃ ነው

በነፋስ ክንፍ ይሄዳል፡፡

መላእክቱንም ሥጋ የሌላቸው ረቂቃን አደረጋቸው፤

የሚያገልግሉትንም የእሳት ነበልባል አደረጋቸው፡፡
መሬትን የሚመለከታት፣
እንድትንቀጠቀጥ የሚያደርጋትም እርሱ ነው፡፡

ሲነካቸውም ተራሮች ይጤሳሉ።

ዓለም ሁሉ በፊቱ የተመዘነ ነው፡፡

ስለዚህም እርሱ ራሱን ሲገልጥ የእስራኤልን ቅዱስ እኔን በማን ትመስሉኛላችሁ?

ሰማይም እንደ ብረት ትጸናለች፤
መሬትም እንደ ልብስ ታረጃለች።

በውስጧ የሚኖሩትም ሁሉ እንደ አንበጣ ናቸው እንደ ዝናም ነጠብጣብም ናቸው። እንደምትሰበስብ የዓይን ሚዛንም ናቸው፡፡ የአንዱን ሚዛን ጉድለቱን የሚጨምር ትንሽ ሚዛንም ይህ ነው፡፡ በእርሱ ዘንድ የዚህ ዓለም ምሳሌ ሆነው ከተባለው ጋር እኩል ይሆን ዘንድ፡፡ ነቢዩም ይህን ተገንዝቦ «ሰውነቴ በአንተ ዘንድ እንደ ኢምንት ነው አለ፡፡

ስለገናናነቱ መልካምን ያደረገ የእርሱን ነገር ጠንቅቆ መናገር ፈጽሞ አይቻለንምና ዝም እንበል፣ ክብር፣ ቡራኬ፣ ምስጋና በፍጥረታቱ፣ በዓለማቱ ሁሉ ለአብ ለወልድ፣ ለመንፈስ ቅዱስ ይሁን፡፡ አሜን፡፡




መልካሙን የማይብህ
ክፉውን የማልፍብህ
ፍቅር እኮ ነህ ጌታዬ
አምላኬ ዋስትናዬ
❤❤❤❤❤❤❤❤❤

4k 0 56 2 21

ሰውነቴ ባንተ ፍቅር ተጠምዳለች
ውለታህን እያሰበች ታለቅሳለች
መከራው ተረሳ ትካዜ ቀረልኝ
ገብረመንፈስ ቅዱስ ፈጥነህ ደርሰህልኝ


ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

.ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉን 👇
╔═★══════════📄══╗
⛓         @Zemaryan          ⛓
⛓         @Zemaryan          ⛓
⛓         @Zemaryan          ⛓
╚══📃══════════★═╝
         ʟɪɴᴋ 👆 ᴛᴀʙ . sʜᴀʀᴇ


አግዘኝ አምላኬ ጠላት እንዳይጥለኝ
ደካማ ነኝ እኔ አንተ ካልደገፍከኝ
ባንተ ስለሆነ መቆም መራመዴ
ጉዞዬ እንዲቀና ቅደም በመንገዴ
❤❤❤❤❤❤❤❤❤


በሰማያት ላይ ከፍ ከፍ በል

     🔸
🔸🔹🔸
     🔸
በሰማያት ላይ ከፍ ከፍ በል
ክብርህም በምድር ይነገራል
ዘመን የሚዋጅ አለን ምስጋና
መድኃኔዓለም ስምህ ገናና

.ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉን 👇
╔═★══════════📄══╗
⛓         @Zemaryan          ⛓
⛓         @Zemaryan          ⛓
⛓         @Zemaryan          ⛓
╚══📃══════════★═╝
         ʟɪɴᴋ 👆 ᴛᴀʙ . sʜᴀʀᴇ


🌹የልጅሽ ቸርነት🌹

የልጅሽ ቸርነት ያንቺ ማማለድ
ድንግል ቃልኪዳንሽ የርሱ ሰው መውደድ
አወጣኝ ከክፉ አዳነኝ ከሞት

ባርኪኝ የአምላክ እናት ይራቅ ጉስቁልናዬ
አፌን በሳቅ ሙይው እንዲታበስ እንባዬ
እኔ ወዳንቺ ልጠጋ ልማልድ ከፊትሽ
አንገትን አያስቀልስም እናቴ ልመናሽ

ሰርጉን እንዳልገባ ልብሴን አሳድፌያለው
በምልጃሽ በማመን ላንቺ አሳስባለው
በሥላሴ ፊት ስምሽ በእውነት ሰልጥኗልና
ይታረቃል እግዚአብሔር ድንግል ባንቺ ልመና

ነግረሽው ነውና ልጅሽ የታገሰኝ
እንደ ኃጢያቴ ብዛት ፈጥኖ ያላጠፋኝ
እውነተኛ መዝገቤ ነሽ ድህነት ያገኘሁብሽ
ወደቤ ነሽ እመቤቴ በሰላም ያረፍኩብሽ

ኃጥአን እንዲጸድቁ ምክንያት አድርጎሻል
ከሞት ወደ ሕይወት አዳም ተሻግሮብሻል
በጌታ ፊት በወረደ በመረረ እንባሽ
የአባቴ ብሩካን ብሎ ይቀበለኝ ልጅሽ

....ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉን 👇
╔═★══════════📄══╗
⛓         @Zemaryan          ⛓
⛓         @Zemaryan          ⛓
⛓         @Zemaryan          ⛓
╚══📃══════════★═╝
         ʟɪɴᴋ 👆 ᴛᴀʙ . sʜᴀʀᴇ


በአንተ ጨለማዬ በራ
ዘማሪ ገብረአምላክ ደሳለኝ


በአንተ ጨለማዬ በራ(2)
ተከፈተልኝ መንገዴ
ዋጋ አለው አንተን መውደዴ
አቀርባለሁኝ መዝሙር አቀርባለሁኝ ሽብሸባ
የክብር ንጉስ ሲመለክ የሰላም ንጉስ ሲገባ (2)

በሞት ጥላ በድቅድቅ ዓለም ኮብልዬ
ድምፁን ሰማሁ ልጄ ሆይ ሲለኝ ጌታዬ
እጁን ሳየው ይላወስ ጀመር አንጀቴ
የህማም ሰው ተስሎ ቀርቷል ከፊቴ

እውነተኛ ሀሰት የሌለው አዋጅ
መስቀሉ ላይ እዩት በደልን ሲዋጅ
ደሙ ነክቶህ ተከፍሎልሀል ተብዬ
ሰላም ገባሁ መድኃኒት ሆኖኝ ጌታዬ

ማምለጫዬ የተረፍኩብህ ከሞት
ማዕረጌ አጌጥኩኝ በአንተ ፍቅር
ፈላጊዬ ያኖረኝ በትከሻው
በጎ እድል ነው ለሰው ልጅ መጨረሻው


....ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉን 👇
╔═★══════════📄══╗
⛓         @Zemaryan          ⛓
⛓         @Zemaryan          ⛓
⛓         @Zemaryan          ⛓
╚══📃══════════★═╝
         ʟɪɴᴋ 👆 ᴛᴀʙ . sʜᴀʀᴇ


መድኃኔአለም

መድኃኔዓለም የለም የሚሳነው
አማኑኤል የለም የሚሳነው
እርሱ ቃል ሲናገር ተራራው ሜዳ ነው
መድኃኔዓለም የለም የሚሳነው

አላስብም ነበር አልፈዋለሁ ብዬ
ጉንጭ አልፎ ትራሴን እያጠበ እንባዬን
እየተፈጸመ ኃይሉ በድካሜ
ማእበሉን አለፍኩኝ ቀለለልኝ ሸክሜ
#አዝ
የቤቴ እራስ ነው የእቅዴ መሪ
በክፉም በደጉም ነፍሴን አስተማሪ
ፈጥሮ የማይረሳኝ ቤዛዬ ደረሰ
ቤቴን ደስታ ሞላው እንባዬ ታበሰ
#አዝ
ትናንት ባዶ ነበር የለኝ የሚሰፈር
አንዳች አልነበረኝ የሚታይ የሚቆጠር
ከርሱ የተነሳ ዛሬ ግን ሙሉ ነኝ
ክብር ለእርሱ ይሁን አለ የማይተወኝ
#አዝ
እየከለከለ ለእኔ ማይጠቅመኝን
በጊዜ እየሰጠ ደግሞ የሚረባኝን
ሁሉ በእርሱ ሆኗል አልሆነም ያለ እርሱ
ውዳሴ ምስጋና ይድረስ ለንጉሱ

....ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉን 👇
╔═★══════════📄══╗
⛓         @Zemaryan          ⛓
⛓         @Zemaryan          ⛓
⛓         @Zemaryan          ⛓
╚══📃══════════★═╝
         ʟɪɴᴋ 👆 ᴛᴀʙ . sʜᴀʀᴇ


ጾመ ሐዋርያት

በወርኃ ሰኔ የሚጾም በመሆኑ ይህ ጾም በተለምዶ የሰኔ ጾም በመባል ይታወቃል፡፡ ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ለስብከተ ወንጌል ከመሰማራታቸው በፊት የጾሙት ጾም ነው፡፡ ጾመ ሐዋርያትን ለመጀመሪያ ጊዜ የጾሙት ቅዱሳን ሐዋርያት ሲሆኑ የጾሙበትም ዋና ምክንያት በሃምሳኛው ቀን ሀብተ መንፈስ ቅዱስ ስለተቀበሉና እግዚአብሔር ስላደረገላቸው መልካም ነገር ለማዘከር ነው፡፡

ጾመ ሐዋርያት በዓለ ጰራቅሊጦስ በመጀመሪያው ሰኞ ይውላል፡፡ ጌታችን አምላካችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌው ደቀ መዛሙርቱን ይህን ጾም እንደሚጾሙት እንዲህ ተናግሮ ነበር፡፡ ‹‹በዚያን ጊዜ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ወደ እርሱ ቀርበው። ‹‹እኛና ፈሪሳውያን፥ ብዙ እንጾማለን፥ ደቀ መዛሙርትህስ ለምን አይጾሙም? አሉት፡፡›› (ማቴ.፱፥፲፬)  ደቀ መዛሙርቱ ይህንን በጠየቁት ጊዜ ጌታችን እንዲህ ብሎ መልሶላቸው ነበር፡፡ ‹‹ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፤ የሙሽራው ሚዜዎች ሙሽራው  ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ አይችሉም፤ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፤ ያንጊዜም ይጾማሉ፡፡›› (ማቴ.፱፥፲፭)
 
በቅዱሳን ሐዋርያት ላይ ያደረው ጸጋ መንፈስ ቅዱስና ሀብተ መንፈስ ቅዱስ በእኛም ላይ እንዲያድር፣ ከቅዱሳን ሐዋርያቱ በረከት እንድንሳተፍ፣ አገልግሎታችን በስኬት እንዲቃና እና ወርኃ ክረምቱ በሰላም ያልፍልን ዘንድ ጾመ ሐዋርያትን መጾም አስፈላጊ ነው፡፡ ከጸሎትና ምጽዋትን መንፈሳዊ እድገትን በጾም አስምረን ከራሳችንን እና ከእግዚአብሔር አምላካችን ጋር የምንታረቅበት እንዲሆንልን የቅዱሳን አባቶቻችን ሐዋርያት በረከትና ጸሎትም አይለየን፡፡
 
የአምላካችን እግዚአብሔር ቸርነት፣ የቅድስት ድንግል ማርያም እና የቅዱሳን ሐዋርያት  አማላጅነትና ተራዳኢነት አይለየን፤ አሜን!
 

.....ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉን 👇
╔═★══════════📄══╗
⛓         @Zemaryan          ⛓
⛓         @Zemaryan          ⛓
⛓         @Zemaryan          ⛓
╚══📃══════════★═╝
         ʟɪɴᴋ 👆 ᴛᴀʙ . sʜᴀʀᴇ


🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱

ጰራቅሊጦስ፦ ማለት መንጽሒ (የሚያነጻ)፣ መጽንዒ (የሚያጸና)፣ መስተፈሥሒ (ደስታን የሚሰጥ)፣ መስተሥርይ (ኃጢአትን ይቅር የሚል)፣ ናዛዚ (የሚያረጋጋ)፣ ከሣቲ (ምሥጢርን የሚገልጥ) የሚል ትርጉምን ይሰጣል መጻሕፍተ ሠለስቱ ሐዲሳት።


"ዐቢየ ተስፋ ዘአስፈዎሙ ይቤሎሙ ኢየሱስ ለአርዳኢሁ እስእሎ ለአቡየ ይፈኑ ለክሙ መንፈሰ ጽድቅ ጰራቅሊጦስ።"

ትርጉም፡-
ታላቅ ተስፋ ያደረገላቸው ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀመዛሙርቱን አባቴን እለምነዋለሁ እውነት መንፈስን ይልክላችኋል።
ሊቁ ቅዱስ ያሬድ።

"ወበ፶ ዕለት ፈነወ ሎሙ መንፈሰ ቅዱሰ ከመ ዘእሳት ወተናገሩ በነገረ ኵሉ በሐዉርት።"

ትርጉም፦
በሃምሳውም ቀን በእሳት አምሳል መንፈስ ቅዱስን ሰደደላቸው በአገሩ ሁሉ ቋንቋ ተናገሩ።

የቅዳሴ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ።

.....ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉን 👇
╔═★══════════📄══╗
⛓         @Zemaryan          ⛓
⛓         @Zemaryan          ⛓
⛓         @Zemaryan          ⛓
╚══📃══════════★═╝
         ʟɪɴᴋ 👆 ᴛᴀʙ . sʜᴀʀᴇ

Показано 18 последних публикаций.

15 653

подписчиков
Статистика канала
Популярное в канале