የህንድ እርምጃ በፓኪስታን
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከሀያ በላይ ንፁሀን ቱሪስቶች በካሽሚር መገደላቸውን ተከትሎ ህንድ በፓኪስታን ላይ ከፍተኛ እርምጃ ልትወስድ መሆኑን አሳውቃለች።
የህንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቪክራም ሚሲሪ ከጥቃቱ ኋላ አስቸኳይ የፀጥታ ካቢኔ ስብሰባ ስለመጠራቱ ለጋዜጠኞች ገልፀዋል።
በዚህም በአስቸኳይ ስብሰባ ህንድንና ፓኪስታንን የሚያዋስኑ ዋና ዋና ድንበሮችን ለመዝጋትና የኢንዱ ወንዝ ውሀ የማካፈል የውሀ ስምምነት ለማራዘም መወሰኑ ተናግረዋል።
አክለውም ወደ ህንድ በልዩ ቪዛ የሚጓዙ ፓኪስታናውያን እንዲታገዱም የገቡትም በ48 ሰአት ህንድን ለቀው እንዲወጡ አሳስበዋል።
የፓኪስታኑ ጠቅላይ ሚኒስትር የህንድን እርምጃና አደጋውን ተከትሎ ማብራሪያ እንዲሰጡ በብሄራዊ ፀጥታ ኮሚቴ ጥሪ እንደቀረበላቸው ታውቋል።
ለ26 ንፁሀን ህልፈት ለበርካቶች መቁሰል ምክንያት የሆነው የካሽሚር የሽብር ጥቃት ቲ አር ኤፍ የተሰኘ አማፂ ቡድን ሀላፊነቱን ወስጃለሁ ብሏል።
ይህ ሀይል በፓኪስታን ድጋፍ ይደረግለታል ስትል ህንድ ተደጋጋሚ ክስ ታቀርባለች።
ጥቃቱንና የህንድን ምላሽ ተከትሎ ከሀገራቱ አልፎ ቀጠናው ውጥረት ውስጥ እንዳይገባ ተሰግቷል።
ዘገባው የአልጀዚራ ነው።
@ZenaAdis_Ethiopia
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከሀያ በላይ ንፁሀን ቱሪስቶች በካሽሚር መገደላቸውን ተከትሎ ህንድ በፓኪስታን ላይ ከፍተኛ እርምጃ ልትወስድ መሆኑን አሳውቃለች።
የህንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቪክራም ሚሲሪ ከጥቃቱ ኋላ አስቸኳይ የፀጥታ ካቢኔ ስብሰባ ስለመጠራቱ ለጋዜጠኞች ገልፀዋል።
በዚህም በአስቸኳይ ስብሰባ ህንድንና ፓኪስታንን የሚያዋስኑ ዋና ዋና ድንበሮችን ለመዝጋትና የኢንዱ ወንዝ ውሀ የማካፈል የውሀ ስምምነት ለማራዘም መወሰኑ ተናግረዋል።
አክለውም ወደ ህንድ በልዩ ቪዛ የሚጓዙ ፓኪስታናውያን እንዲታገዱም የገቡትም በ48 ሰአት ህንድን ለቀው እንዲወጡ አሳስበዋል።
የፓኪስታኑ ጠቅላይ ሚኒስትር የህንድን እርምጃና አደጋውን ተከትሎ ማብራሪያ እንዲሰጡ በብሄራዊ ፀጥታ ኮሚቴ ጥሪ እንደቀረበላቸው ታውቋል።
ለ26 ንፁሀን ህልፈት ለበርካቶች መቁሰል ምክንያት የሆነው የካሽሚር የሽብር ጥቃት ቲ አር ኤፍ የተሰኘ አማፂ ቡድን ሀላፊነቱን ወስጃለሁ ብሏል።
ይህ ሀይል በፓኪስታን ድጋፍ ይደረግለታል ስትል ህንድ ተደጋጋሚ ክስ ታቀርባለች።
ጥቃቱንና የህንድን ምላሽ ተከትሎ ከሀገራቱ አልፎ ቀጠናው ውጥረት ውስጥ እንዳይገባ ተሰግቷል።
ዘገባው የአልጀዚራ ነው።
@ZenaAdis_Ethiopia