የተወካዮች ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ አባላት የሳፋሪኮምን የስራ እንቅስቃሴ ገመገሙ
ሐሙስ ህዳር 12 ቀን 2017(አዲስ ማለዳ) በዛሬው እለት የተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያን አጠቃላይ የስራ ሂደት እና አፈጻጸም ገምግመዋል።
በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ዋና መስሪያ ቤት በተካሄደው በዚህ ፕረሮግራም ላይ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዊም ቫንሄልፑት ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በመሆኑም ላለፋት ሶስት አመታት ከ6ሚሊዮን በላይ ደንበኞችን ማፍራት መቻሉን እና በ9 የክልል ከተሞች አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ዋና ስራ አስፈጻሚው አስታውቀዋል።
እንዲሁም በኤም ፔሳ የሞባይል ግብይት ከበርካታ ባንኮች ጋር በጋራ በመስራት ላይ መሆኑን እና በተለያዩ አካባቢዎች ለመንግስት ትምህርት ቤት ተማሪዎች የትምህርት መሳሪያ መስጠታቸውን ለምክርቤት አባላቱ ገልጸዋል።
በተጨማሪ ጉልህ የገበያ ሀይል ወይም አንድ የሳፋሪኮም ደንበኛ ወደ ኢትዮ ቴሌኮም ተጠቃሚ ጋር ለመደወል ተጨማሪ ክፍያ እንዳይከፍል ለማስቻል እንዲሁም ለማስፋፊያ እና የግንባታ ፍቃድ ላይ ከምክር ቤቱ ድጋፍ ተጠይቋል።
የምክር ቤቱ አባላትም በቀረበው ሪፖርት ላይ ሀሳብ አስተያየት ካነሱ በኋላ ለተጠየቀው የድጋፍ እና የፍቃድ ጥያቄ ተወያይተው ምላሽ እንደሚሰጡ ገልጸዋል፡፡
ሐሙስ ህዳር 12 ቀን 2017(አዲስ ማለዳ) በዛሬው እለት የተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያን አጠቃላይ የስራ ሂደት እና አፈጻጸም ገምግመዋል።
በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ዋና መስሪያ ቤት በተካሄደው በዚህ ፕረሮግራም ላይ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዊም ቫንሄልፑት ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በመሆኑም ላለፋት ሶስት አመታት ከ6ሚሊዮን በላይ ደንበኞችን ማፍራት መቻሉን እና በ9 የክልል ከተሞች አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ዋና ስራ አስፈጻሚው አስታውቀዋል።
እንዲሁም በኤም ፔሳ የሞባይል ግብይት ከበርካታ ባንኮች ጋር በጋራ በመስራት ላይ መሆኑን እና በተለያዩ አካባቢዎች ለመንግስት ትምህርት ቤት ተማሪዎች የትምህርት መሳሪያ መስጠታቸውን ለምክርቤት አባላቱ ገልጸዋል።
በተጨማሪ ጉልህ የገበያ ሀይል ወይም አንድ የሳፋሪኮም ደንበኛ ወደ ኢትዮ ቴሌኮም ተጠቃሚ ጋር ለመደወል ተጨማሪ ክፍያ እንዳይከፍል ለማስቻል እንዲሁም ለማስፋፊያ እና የግንባታ ፍቃድ ላይ ከምክር ቤቱ ድጋፍ ተጠይቋል።
የምክር ቤቱ አባላትም በቀረበው ሪፖርት ላይ ሀሳብ አስተያየት ካነሱ በኋላ ለተጠየቀው የድጋፍ እና የፍቃድ ጥያቄ ተወያይተው ምላሽ እንደሚሰጡ ገልጸዋል፡፡