አል-ፉርቃን የንፅፅር ቻናል


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


ግሩፓችን ~> @Alfurqan12

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


Репост из: Suna Islamic Library
ዓሹራ.pdf
677.6Кб
كن على بصيرة
📚📚የመፅሀፍ ግብዣ📚📚
"ዓሹራ "

✍ ወሂድ ኡመር


📚📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📚
ቻናላችን፦ t.me/sunatube
Join> t.me/sunatube
Share> t.me/Sunatube


የመፀሃፍ ቁዱስ ምስጥር የንብቡት.pdf
4.9Мб
📚📚የመፅሀፍ ግብዣ📚📚
የመፅሐፍ ቅዱስ ሚሥጥር
በሙሥሊም መነፅር

✍ ቀመር ሁሤን


🌈🌈🌈🌈🌈🌈🌈🌈🌈
ቻናላችን፦ t.me/alfurqan11

ግሩፓችን፦ t.me/Alfurqan12


እንቆቅልህ

ክርስትያን አባት ትንሽ ልጁን እያጫወተ መንፈሳዊ ትምህርት እያስተማረው ነው...

👴፦ እንቆቅልህ

👶፦ ምን አውቅልህ

👴፦ •አምላክ ነኝ #ሰው #አይደለሁም
•ፍትሃዊ ነኝ ግን የሰውን ዘር ሁሉ በአዳምና ሔዋን ምክንያት ረገምኩና #ሲኦል #አስገባሁአቸው
•እርግማኑን ላነሳላቸው ብዬ ግን #ሰው #ሆንኩ
• አልሞትም ግን ደግሞ ራሴው እንዳይድኑ ያደረኳቸውን ለማዳን ስል ተቀጥቅጬ ሞትኩላቸው
•በባህሪዬ ሲኦል አልገባም ግን ደግሞ ራሴው ያስገባሁአቸውን ሰዎች ከሲኦል ለማውጣት ብዬ #ሲኦል #ገባሁ
~> እኔ ማነኝ?

👶፦ እ.. አባቢ አወኩት፡፡ ባለፈው በፊልም አይቼዋለው፤ ብዙ ጊዜ "ውኃ ቅዳ ውኃ መልስ" አይነት ስራ ነው የሚሰራው ስወደው😍❤️

👴፦ ጎበዝ የኔ ልጅ እና ማነው?

👶፦ Mr. Bean❤️ ነው

👴፦ ሎቱ ስብሃት😡😡😡

@Alfurqan12
@Alfurqan11


መልስ ለቄስ ቆሞስ 😔ኑ ይህችን ስሙልኝማ
የ YouTubeቻናሌ ቤተሰብ ካልሆናችሁ subscribe አድርጉ ይህ video ከተመቻችሁ like እንዲሁም ይህ video ይጠቅማል ብላችሁ ካሰባችሁ share ሰብስክራይብ ያድርጉ። እንዲሁም የደውል ምልክቱን ይጫኑ።

https://t.me/shemsedinComparativereligion




የስቅለት ታሪክ ግጭቶች
ክፍል 3

የቤተ መቅደስ መጋረጃ ለሁለት የተቀደደው መቼ ነበር ኢየሱስ ጮኾ ከመሞቱ በፊት ወይስ በኋላ❓❔

👉 እንደ ሉቃስ ዘገባ ከሆነ መጀመርያ የቤተ መቅደሱ መጋረጃ ተቀደደና ከዛ በኋላ ኢየሱስ በታላቅ ድምፅ ጮኾ ሞተ፡፡👇
የሉቃስ ወንጌል 23
44 ስድስት ሰዓትም ያህል ነበረ፥ ጨለማም እስከ ዘጠኝ ሰዓት በምድር ሁሉ ላይ ሆነ፥ ፀሐይም ጨለመ፥
45 #የቤተ #መቅደስም #መጋረጃ #ከመካከሉ #ተቀደደ።
46 #ኢየሱስም #በታላቅ #ድምፅ #ጮኾ፡— አባት ሆይ፥ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ፡ አለ። ይህንም ብሎ #ነፍሱን #ሰጠ።

👉 እንደ ማቴዎስ ዘገባ ከሆነ ግን ኢየሱስ በታላቅ ድምፅ ጮኾ ከሞተ በኋላ የቤተ መቅደሱ መጋረጃ ለሁለት እንደተቀደደና ምድር ተናውጣ አለቶችም እንደተሰነጠቁ ይናገራል፡፡👇
የማቴዎስ ወንጌል 27
50 ኢየሱስም ሁለተኛ በታላቅ ድምፅ ጮኾ ነፍሱን ተወ።
51 እነሆም፥ የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ከሁለት ተቀደደ፥ ምድርም ተናወጠች፥ ዓለቶችም ተሰነጠቁ፤
52 መቃብሮችም ተከፈቱ፥ ተኝተው ከነበሩትም ከቅዱሳን ብዙ ሥጋዎች ተነሡ፤

ከሉቃስና ከማቴዎስ ማንኛቸው ናቸው የዋሹት?

t.me/Alfurqan11
@Alfurqan12


"አምላካችን አንድ ነው" የእየሱስ አስተምህሮ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው ፡፡
ሱረቱ መረየም 36
وَإِنَّ ٱللَّهَ رَبِّى وَرَبُّكُمْ فَٱعْبُدُوهُ هَٰذَا صِرَٰطٌ مُّسْتَقِيمٌ
(ዒሳ አለ) «አላህም ጌታዬ ጌታችሁም ነውና ተገዙት፡፡ ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው፡፡»

በማርቆስ ወንጌል ላይ ትኩረትን ሊሻ ግን ትኩረት የተነፈገ አንኳር የሆነን ክስተት ገጠመኝ እናገኛለን፡፡ እየሱስ የብሉይ ኪዳኑን የአንድ አምላክ እምነት (monotheism) ያፀደቀበት፡፡ ከአይሁድ ህግን የተማረ ያወቀ ለእየሱስ ጥያቄ ያቀርባል "ከህግ ሁላ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባው ትዕዛዝ የቱ ነው ይላል"

(የማርቆስ ወንጌል ምዕ. 12)
----------
28፤ ከጻፎችም አንዱ ቀርቦ ሲከራከሩ ሰማና መልካም አድርጎ እንደ መለሰላቸው አስተውሎ። ከሁሉ ፊተኛይቱ ትእዛዝ ማናቸይቱ ናት? ብሎ ጠየቀው።
29፤ ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው። ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ። እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ *ጌታ #አምላካችን አንድ ጌታ ነው*፥
32፤ ጻፊውም። መልካም ነው፥ መምህር ሆይ፤ *#አንድ ነው ከእርሱም በቀር ሌላ የለም* ብለህ በእውነት ተናገርህ፤
34፤ ኢየሱስም በአእምሮ እንደ መለሰ አይቶ። *አንተ ከእግዚአብሔር መንግሥት የራቅህ አይደለህም* አለው። ከዚህም በኋላ ማንም ሊጠይቀው አልደፈረም።


🎯 ይህ ገጠመኝ ታድያ እየሱስ አይሁዶች በአምላክ ዙሪያ ስላላቸው የተዛባ እምነት ግልፅ የሚያድርግበትና ስለ ስላሴ በመለኮት አንድ በአካል ሶስት ፣ሶስቱም እኩል ስልጣን እንዳላቸው የሚያብራራበት እድል ነበር

ከላይ እንዳየነው እየሱስ ከዚህ በተቃረነ መልኩ ከኦሪት ዘዳግም 6:4 ላይ ያለውን ህግ በመዝከር እንዲሁም ከአይሁድ አዋቂ ከነበረው ፃህፍት እሳቤ ጋር ሙሉ በሙሉ ተስማመተዋል

እየሱስ የስላሴን አስተምህሮ ሳይዘክር የአይሁዳውያኑን ስለ አንድ አምላክ እሳቤ በመደገፍ ብሎም ጠያቂውን አንተ ከእግዚአብሔር መንግስት የራክ አይደለህም ብሎ መሰክሮለት እናገኛለን

የአይሁድ ህዝብ በስላሴ በጭራሽ አያምኑም በነብያትም አልተስተማርንም በብሉይም አልተዘከረም ብለው የነሱ ሊቃውንት ይህን ያፀድቃሉ

አለቃ የነበሩን ነቢያቶች በአምላክ ትዕዛዝ መሰረት ያስተማሩን እርሱ አንድ እና ያለ አጋር መሆኑን ነው ፣ እነዚያ የጠመሙት የሚያቀርቧቸውን የተሳሳቱን አስተምህሮ ከልባችን ለማስወገድ ፈጣሪያችን [ዘዳ 6-4 (" እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ አምላካችን እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ነው፤")] ይህንን መሰረታዊ ድንጋጌ አደረገው ፡፡ ነገር ግን ክርስቲያኖቹ አምላክ ከሦስቱ አንዱ ነው አምላካችን ፣ ጌታ ሶስት አካል ነው ፣ ሁሉም አንድ ናቸው የሚለውን ያስተምራሉ፡፡ባለማወቃቸው ከሚናገሩት ነገር ፈጣሪያችን የጠራ ነው ፡፡
Moshe ben Maimon, the Rambam or Maimonides, in his The Essay on Resurrection, trans. Abraham Halkin in The Epistles of Maimonides: crisis and leadership.

አምላክ ራሱን ግልፅ በሆነ መልኩ እርሱ አንድነቱን ገልጾል
★ኢሳይያስ 44:24 ሰማያትን ለብቻዬ የዘረጋሁ ምድርንም ያጸናሁ እግዚአብሔር እኔ ነኝ ከእኔ ጋር ማን ነበረ?
★ዘዳ.32:39፤ አሁንም እኔ ብቻዬን እኔ እንደ ሆንሁ፥ ከእኔም በቀር አምላክ እንደሌለ እዩ፤
★ዘዳ 32:12 እግዚአብሔር ብቻውን መራው፤ ከእርሱም ጋር ሌላ አምላክ አልነበረም።

ነብያትም በብሉይ እንደ አብራሀም ኖህ ሙሴ (በእነርሱ ላይ ሰላም ይሁን) አንዳቸውም ስለ ስላሴ አልሰበኩም የነርሱ አንኳር ትምህርት አንድ አምላክ ከርሱ በቀር ሌላ የለም እርሱ ፍጡራኑን አይመስልም እርሱም ብቻ ነው አምልኮ የሚገባው ነው ፡፡

🎯 ታድያ አምላክ በቁጥር የማይዘለቁ ነቢያትን ልኮ እነሩሱም ስለ አምላክ አንድ መሆን ሲዘክሩ ቆየተው ከሺ ዘመናት በሇላ አልፎ ድንገት እርሱ መለኮት ስላሴ መሆናቸውን ቢገልጽ ይህ ትርጉም አለውን⁉️ ከዚህ ቀደም የነበሩትን የነብያቱንስ ትምህርት አይጣረስምን‼

ወሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱህ




Репост из: 𝓗𝓪𝓫𝓲𝓫 𝓐𝓫𝓭𝓾𝓵𝓯𝓮𝓽𝓪𝓱
አላሁ አክበር
አላሁ አክበር
አላሁ አክበር

አንዲት እህታችን የተለያዩ የሀይማኖት ንፅፅር ትምህርቶችን በግሩፓችን አልፉርቃን ውስጥ ስትከታተል ቆይታ ዛሬ በወርሀ ረመዷን 29ኛ ቀን 29/9/1442 ላይ በአላህ ፍቃድ ከነበረችበት ክርስትና ወደ ተፈጠረችበት እስልምና ተመልሳለች። አልሃምዱሊላሂ ኢላሂል ዐለሚን።

ማሻአላህ
ማሻአላህ
አላሁአክበር

አላህ በዲኑ ላይ ኢስባቱን ይስጣት አሚን!!

https://t.me/Alfurqan12


በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው

"ሂጃብ" حِجَاب

በነጠላ ሲጠራ *حِجَاب*(ሂጃብ) የቁጥር ብዙነትን ለማሳየት ደሞ *حُجُب* (ሁጁብ)
ወይም *أَحْجِبَة* (አህጂባ) እንለዋለን የርሱ ተዛማጅ ከሆኑ ቃላት መሀከል ከልካይ *حَاجِز*(ሀጂዝ) ወይንም ግርዶሽ *بَرْزَخ‎* (በርዘኽ) ናቸው
ቋንቋዊ ፍችው መጋረጃ ማለት ሲሆን እንደ አገባቡ የራሱን ፍች ይይዛል ሂጃብ በእውነት በሀሰት መሀል ላለው መለያ ነው፡፡

ሂጃብ የሴት ልጅ የክብሯ የንፅህናዋ መገለጫ ነው እንጂ እርሷ የበታች መሆኖን የሚገልፅ አይደለም ፈጣሪያችን አላህ በማይሻር ቃሉ እንዲህ ይለናል
49|13|እናንተ ሰዎች ሆይ! እኛ *ከወንድ*ና *ከሴት* ፈጠርናችሁ፡፡ እንድትተዋወቁም ጎሳዎችና ነገዶች አደረግናችሁ፡፡ አላህ ዘንድ በላጫችሁ በጣም አላህን *ፈሪያችሁ* ነው፡፡

አላህ ዘንድ በላጫችን በፆታ ወይም በዘር በቁጅና በቁመና አይደለም ፈጣሪያችን ዘንድ የምንበላለጠው እርሱን ማንኛችን የበለጠ ይፈራል በሚለውም በሌላም አንቀፅ እንዲህ ይለናል
4|124|*ከወንድ* ወይም *ከሴት* እርሱ አማኝ ኾኖ ከበጎ ሥራዎች አንዳችን የሚሠራም ሰው እነዚያ ገነትን ይገባሉ፡፡ በተምር ፍሬ ላይ ያለችን ነጥብ ያክል እንኳ አይበደሉም፡፡

በፆታ ምክንያት አንዳችም የበላይነት ወይም የበታችነት የለም የአላህን የርሱን ፍራቻ በመላበስ ለርሱ ታዛዥ በመሆን እንጂ ሴቶቻችን ለኢስላም ትልቅ ባለውለታም ጀግኖችም ነበሩ እንደ ማሳያ
°የመጀመሪያዋ ሰማዐት(ሸሂድ) ሴት ናት
°መጀመሪያ የነብዩን ጥሪ ሀቅ ነው ብላ ያመነች ሴት ናት
°መምህር የሀይማኖትን ፍርድ ብይን ሰጪ እና 1/3 የሚሆነውን ከነብዩ(ﷺ) በመማር ለ፡በማስተማር ለኛ ያወረሰች ሴት ነበረች
ብዙ ብዙ ..

አላህ በመሀከላችን እኩልነትን ነው ያስቀመጠው ነገር ግን በፍጥረታችን እርሱ ፈጥሪያችን ልዩ አድርጎናል በዚህም አላህ በመላው ልንሰራው ያዘዘን አለ እንዲሁም በተናጠል፡፡ ለሴቶች ከተደነገገው ህግጋት መሀካል ሂጃብ መልበስ አንዱ ነው ፡፡

ሂጃብ ለሴት ልጅ በራስ መተማመኖን ከፍ የሚያደርግ ማንነቷን ገላጭ መለዮ ነው፡፡ ለምሳሌ :-
አንዲት ከፍ ባለ ቦታ ላይ ያለችን ሴት እንናሳ.. የዝግጅት ስብሰባ መሪ ናት እንበል ከታደሙት መሀል አብዛኛዎቹ ወንዶች ቢሆኑና ወደ መድረኩ ስትወጣ የሰውነቷን ቅርፅ የሚጠቁም አጭር ልብስ ረዥም ጫማ እንዲሁም ፀጉሯን ለቃ ብትወጣ .. መጀመሪያ የሚስተዋለው ትኩረትም የሚሰጠው የርሷ የሰውነት ቅርፅ ላይ እንጂ ለሀሳቧ ላይ አይደለም ምን አልባትም ምን እንዳለች ሳይሰሙ እሷን sexualize በማድረግ የሚጠመዱም አይጠፉም
ሴትን ልጅን በማራቆት የሰውነት ቅርፆን በማያት እና የሷን የሰውነት ክፍሎች ላይ በማተኮር ከወንዶች እንደ መዝናኛ እንደሚጠቀሟት እንዳሉ ይታወቃል
*ለሀሳቧ ለርሷነቷ ለማንነቷ ሳይሆን ለስጋዋ ያሰፈስፋሉ *

ከዚ በተቃራኒ አንዲት ሙስሊም ሴት ሂጃቧን ተላብሳ መድረኩን ብመራ 100% በሆነ መልኩ ስለሷ ሀሳብ ወይም ማንነቷ ላይ ብቻ እንጂ በሰውነቷ ስጋዊ ቅርፆ ወይም ክፍሏ ላይ ትኩረት አይኖርም

ሂጃብ ለሴት ልጅ ንፅህናዋን ታማኝነቷን ማሳያ ነው፡፡ እርሷ ለወደደችው ይሆነኛል ላለችው ለሂወት አጋሯ ብቻ እንጂ ለማንም ወንድ እራሷን የከለከለች የጠበቀች መሆኖን ገላጭ ነው ፡፡ ወንዱም ከርሷ ሌላን ማየትን እርም ተደርጎበታል ይህ ታድያ በትዳራቸው መተማመንን እንዲኖር ይረዳል አንዳቸው ለአንዳቸው ብቻ መሆናቸውን ያሳያል
24|30|ለምእመናን ንገራቸው፡- ዓይኖቻቸውን (ያልተፈቀደን ከማየት) ይከልክሉ፤ ብልቶቻቸውንም ይጠብቁ፤ ይህ ለነሱ የተሻለ ነው፤ አላህ በሚሠሩት ሁሉ ውስጥ ዐዋቂ ነው፡፡

ሂጃብ ያለአግባብ የሆነን ለከፋ የወንዶችን ጥቃት መጠበቂያ ነው፡፡ ህንድ ውስጥ 2018 ላይ ብቻ በተደረገ ጥናት በየ15 ደቂቃው አንድ ሴት ልጅ ትደፈራለች። ያ ማለት በየቀኑ 96 ሴት ልጆች በወንድ ይደፈራሉ ማለት ነው። ለዚህ አፀያፊ ድርጊት ግን ወንዶች ብቻ ተጠያቂ አይደሉም ሴቶችም ተጠያቂ ናቸው ምናልባት ሴቶቹ ሂጃብ ቢለብሱና ሌሎች መሰል ሸሪዓዊ ድንጋጌን ቢፈፅሙ ይህንን አስነዋሪ ተግባር በከፍተኛ ደረጃ መቀነስ ይችላሉ።

ሂጃብ ከፈጠሪዋ ጋር ያላትን ግኑኝነት ጥንካሬ ማሳያ ነው፡፡ በሀይማኖቷ መጠንከሯ ለርሷ ውበቷ ነው መልካምን ስነምግባር ስብዕና እንዲኖረት ምክንያት ነው ፡፡ አንዲት ሴትን ለማጨት ቅድሚያ የሚታየው በኢስላም በሀይማኖት ያለት ጥንካሬዋ ነው ምክንያቱም ያ የውስጥ ማንነቷ ማሳያ ነውና፡፡ ለወንዱ ቅድሚያ ለሴት ልጅ ቁመና መልክ ቁንጅና ወይም ለስልጣን ለሀብቷ ቅድሚያ መስፈርት እንዲያውል አልተገባም ነገር የርሷን የሀይማኖት ጥንካሬ እንጂ፡፡ ያ የሚጠቁመው ደሞ የርሷን ውስጣዊ ማንነት አስተሳሰብ ፀባዮ ስለንቦናዋ ነው ፡፡

ﻭﻗﺪ ﺃﺧﺒﺮ ﺍﻟﻨﺒﻲ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ، ﻋﻦ ﺫﻟﻚ ﺑﻘﻮﻟﻪ : « ﺗﻨﻜﺢ ﺍﻟﻤﺮﺃﺓ ﻷﺭﺑﻊ ﺧﺼﺎﻝ : ﻟﻤﺎﻟﻬﺎ، ﻭﺟﻤﺎﻟﻬﺎ، ﻭﻟﺤﺴﺒﻬﺎ، ﻭﻟﺪﻳﻨﻬﺎ، ﻓﺎﻇﻔﺮ ﺑﺬﺍﺕ ﺍﻟﺪﻳﻦ ﺗﺮﺑﺖ ﻳﺪﺍﻙ»

ረሱል (ሰላለሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋሉ፦ “ሴት ልጅ ለአራት ነገሮች ትገባለች። ለገንዘቧ፣ ለዘር ክብሯ፣ ለውበቷና ለዲኗ(በኢስላም ሀይማኖት ባላት ጥንካሬ)። የዲን ባለቤት የሆነችውን ምረጥ። ይህን ካላደረግክ እጅህ አመድ አፋሽ ትሁን።” Sahih al-Bukhari 5090In-book reference : Book 67, Hadith 

ﺃﻓﻀﻞ ﻣﺎ ﻳﻨﺒﻐﻲ ﺗﻮﻓﺮﻩ ﻓﻲ ﺍﻟﺰﻭﺟﻴﻦ، ﻣﻠﺘﺰﻣﺎ ﺑﺸﺮﺍﺋﻊ ﺍﻹﺳﻼﻡ ﻓﻲ ﺣﻴﺎﺗﻪ ﻓﻼ ﻳﻈﻠﻢ ﺯﻭﺟﺘﻪ، ﻓﺈﻥ ﺃﺣﺒّﻬﺎ ﺃﻛﺮﻣﻬﺎ ﻭﺇﻥ ﻟﻢ ﻳﺤﺒﻬﺎ ﻟﻢ ﻳﻈﻠﻤﻬﺎ ﻭﻟﻢ ﻳُﻬﻨﻬﺎ

እጅግ በላጩ ምርጥ ባል ማለት የአላህ ዲን በሚገባ የሚያውቅና ስነ ምግባሩ ያማረ ነው። ዲኑን(የኢስላም ሀይማኖቱን) የሚያውቅ ካገባሽ ከወደደሽ በእጅጉ ያከብርሻል፤ የማይወድሽ ከሆነ አያዋርድሽም ክብርሽን በሚገባ ይጠብቅልሻል። ስለዚህ ዲን(የኢስላም ሀይማኖት) ያለው የስነ ምግባር ባለቤት ምርጫሽ ሊሆን ይገባል።

°ሂጃብ ከመጥፎ ዝንባሌ ከመጥፎ ተግባር መጠበቂያ ነው
°ሂጃብ ለጠንካራ ሴት እና ለዐማኝ ሴት መለዮ ነው
°ሂጃብ የንፅህና የክብር መገለጫ ነው
°ሂጃብ ለአምላክ ትዕዛዝ አቤት ማለትን ታዛዥነትን ማሳያ ነው
°ሂጃብ ለኢስላም አምባሳደር መሆን ነው
°ሂጃብ የጨዋነት ማሳያ ነው
°ሂጃብ ከዋሊጌወች ጥቃት መጠበቂያ ነው
°ሂጃብ ለራስ የሰጠነውን ክብር እንዲሁም በራስ መተማመን ማሳያ ነው
°ሂጃብ በሴት መሀካል ያለውን የጎጥዩሽ መታያየት selfish አጉል ጥላቻን ቅናትን ቀራፊ ነው
°ሂጃብ አንዱ lifestyle( የሂወት መርህ) ነው
*ሂጃብ ለሴት ልጅ ውበቷ ለወንድ ደሞ መጠበቂያ ነው*

ወሰላሙ አለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካቱህ

✍ወንድም ሀቢብ




• سورة الحشر •🍃

▫️ القارئ ؛ #اسلام_صبحي

•🍃• سورة الحشر

▫️የልብ እርጋታ ለማግኘት
ስትጨናነቁ ስራ ሲበዛባቹ ስትታመሙ ወዘተ ወዲያውኑ ቁርአን ስትሰሙ ሁሉነገር ትረሱታላቹ ሱበሀን አላህ ይገርማል

ነቢዩ ﺻﻠﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ
ቁርኣንን ማንበብ ትሩፋቱ ምን ያህል እንደሆነ እንዲህ በማለት ነግረውናል
ﻋﻦ ﻋَﺒْﺪ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺑْﻦ ﻣَﺴْﻌُﻮﺩٍ، ﻗﺎﻝ : ﻗَﺎﻝَ ﺭَﺳُﻮﻝُ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺻَﻠَّﻰ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﻋَﻠَﻴْﻪِ ﻭَﺳَﻠَّﻢَ : ‏( ﻣَﻦْ
ﻗَﺮَﺃَ ﺣَﺮْﻓًﺎ ﻣِﻦْ ﻛِﺘَﺎﺏِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻓَﻠَﻪُ ﺑِﻪِ ﺣَﺴَﻨَﺔٌ ، ﻭَﺍﻟﺤَﺴَﻨَﺔُ ﺑِﻌَﺸْﺮِ ﺃَﻣْﺜَﺎﻟِﻬَﺎ، ﻟَﺎ ﺃَﻗُﻮﻝُ ﺍﻟﻢ
ﺣَﺮْﻑٌ، ﻭَﻟَﻜِﻦْ ﺃَﻟِﻒٌ ﺣَﺮْﻑٌ ﻭَﻟَﺎﻡٌ ﺣَﺮْﻑٌ ﻭَﻣِﻴﻢٌ ﺣَﺮْﻑٌ ‏) ، ﻭﺻﺤﺤﻪ ﺍﻷﻟﺒﺎﻧﻲ ﻓﻲ
"ﺻﺤﻴﺢ ﺍﻟﺘﺮﻣﺬﻱ " 2910 ተ
‹ ከአላህ ቁርኣን አንድ ፊደል ያነበበ ሰው በዚያ አሥር ምንዳ ያገኛል፡
‹አሊፍ ላም ሚም› ሲል አንድ ፊደል ነው አልላችሁም፡ ነገር ግን አሊፍ
አንድ ፊደል ነው ላምም አንድ ፊደል ሚምም አንድ ፊደል ነው
____
አላህ ቁርኣንን እንዳላቀው ሁሉ የረመዳንን ጊዜያት አላቀው በረመዳን ወር
ቁርኣንን ማንበብ መቅራት ምንዳውን እጥፍ ድርብ ነው


@KatetagiwuMangad

القارئ ؛ #اسلام_صبحي


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ያማል በጣም‼
=============
«ይህንን ጭካኔ ሁሉም ይመልከተው። ሼር አድርጉት!»
||
«ኧረ በአላህ! ኧረ በአላህ‼ ተውኝ!
*
ኧረ ልጆቼ! ኧረ ልጆቼ‼»
እያለ ቢለምናቸውም እምቢ አሉት። በጾም አንጀቱ እያነሱ ይጥሉታል።
የጭካኔና የአረመኔነት ጥግ!
መንገድ ላይ እያዞሩ ሳልባጅ ከሚሸጡት ሰዎች መካከል አንዱ ነው። ቤተሰቡን የሚያስተዳድረው በዚህ ነው።

«ኧረ በአላህ!» ይላቸዋል! የኔ ከርታታ ለፍቶ አዳሪ ሚስኪን! አላህን የማይፈሩ ልበ ደንዳኖች አጋጥመውት!
«የላብ አደሮች ቀን» እያሉ ቀን መርጦ ከማክበር ለዚህ አይነቱ ሚስኪን ማዘን ይበልጣል።

ልጆቹ ለጊዜው ከአጠገቡ ባይሆኑም ይህን ያባታቸውን የተማፅኖ ድምፅ በሰሙ ጊዜ ምን ይሰማቸው ይሆን በአላህ?!
*
በህጋዊነት ሽፋን የሚፈጸም ህገ ወጥነት‼
እነዚህም ብሎ ደምብ አስከባሪ!
ስንት ግዙፍ የኮንትሮባንድ አንቀሳቃሽ ባለበት ወቅት ህግ የሚከበረው በዚህ ተራ ሚስኪን ግለሰብ ላይ ነው?!
ምን አይነት ጨካኝ አንጀት ቢኖራቸው ነው እንዲህ እየተማጸናቸው የሚያብጠለጥሉት?!
Really heart touching‼ Painful‼
በየትኛውም መልኩ ትክክል ሊሆን የማይችል ከሰብዓዊነት ያፈነገጠ ጸያፍ ድርጊት ነው።
እነዚህን አካላት ተጣርተው መያዝ አለባቸው።

በዚሁ አጋጣሚ ይህን ግለሰብ አፈላልጉትና በተቻለ መጠን ትንሽ የገንዘብ ድጋፍ ይደረግለት።
በበኩሌ ለማስተባበር ፈቃደኛ ነኝ።
አድራሻውን እንደምንም አፈላልጉልኝ!
*
«ሼር በማድረግ አድራሻውን እናፈላልገው! የወንድማችንን እምባ እንበስ!»
||



https://t.me/KatetagiwuMangad


በአላህ ስም እጅግበጣም አዛኝ በሆነ እጅግ በጣም መሀሪ በሆነ


ከሰማይ የወረዱ ሰማያውያን መፅሃፍ
 በጥራዝ መልክ የሚገኙ መፅሃፍት
የተከበረው ቁርኣን.. የመጨረሻው መፅሃፍ

የተውራት /ኦሪት/ መበረዝ

የኢንጂል /ወንጌል/ መበረዝ

የተከበረው ቁርኣን የቀደሙትን መፅሃፎች እውነትነት ስለማረጋገጡ

ወደ እውነት የሚያደርሰው መንገድ

ከሰማይ በወረዱት መፅሃፍት ማመን (አል-ኢማን ቢኩቱብ አስ-ሰማዊያ) ከስድስቱ የእምነት ምሶሶዎችን (አርካን አል-ኢማን) ውስጥ በሶስተኛ ደረጃ የተጠቀሰ ነው። በዚህ ጽሁፍ ይህንን አበይት የእምነት ክፍል በዝርዝር እንመለከታለን።

አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ወደ መልእክተኞቹና ነቢያቶቹ ወህይ ያደረጋቸው /በራእይ የገለፀላቸው/ የሆኑ ምክሮችና ትምህርቶች አሉ። ከነኚህም መካከል በመፅሀፍ መልክ የተጠረዙ ያሉ ሲሆን ከነኚህም ውጭ እኛ የማናውቃቸው የሆኑ አሉ። ሁሉም ነቢይ የተላከበትን መልእክት ወደ ህዝቦቹ አድርሷል። አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ አለ

كَانَ النَّاسُ أُمَّةً وَاحِدَةً فَبَعَثَ اللَّهُ النَّبِيِّينَ مُبَشِّرِينَ وَمُنْذِرِينَ وَأَنْزَلَ مَعَهُمُ الْكِتَابَ بِالْحَقِّ لِيَحْكُمَ بَيْنَ النَّاسِ فِيمَا اخْتَلَفُوا فِيهِ [٢:٢١٣]

“ሰዎቹ ሁሉ አንድ ሕዝብ ነበሩ፤ (ተለያዩ)። አላህም ነቢያትን አብሳሪዎችና አስፈራሪዎች አድርጎ ላከ። ከእነርሱም ጋር መጻሕፍትን በሰዎቹ መካከል በዚያ በርሱ በተለያዩበት ነገር ይፈርድ ዘንድ በእውነት አወረደ።” (አል-በቀራህ 2፤ 213)

فَإِنْ كَذَّبُوكَ فَقَدْ كُذِّبَ رُسُلٌ مِنْ قَبْلِكَ جَاءُوا بِالْبَيِّنَاتِ وَالزُّبُرِ وَالْكِتَابِ الْمُنِيرِ [٣:١٨٤]

“ቢያስተባብሉህም ከአንተ በፊት በግልጽ ተዓምራትና በጽሑፎች፣ በብሩህ መጽሐፍም የመጡት መልክተኞች በእርግጥ ተስተባብለዋል።” (ኣሊ ዒምራን 3፤ 184)

በጥራዝ መልክ የሚገኙ መፅሃፍት

1. በነቢዩ ሙሣ (ዐ.ሠ) ላይ የወረደው ተውራት /ኦሪት/

አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ አለ

إِنَّا أَنْزَلْنَا التَّوْرَاةَ فِيهَا هُدىً وَنُورٌ يَحْكُمُ بِهَا النَّبِيُّونَ الَّذِينَ أَسْلَمُوا لِلَّذِينَ هَادُوا وَالرَّبَّانِيُّونَ وَالأَحْبَارُ بِمَا اسْتُحْفِظُوا مِنْ كِتَابِ اللَّهِ وَكَانُوا عَلَيْهِ شُهَدَاءَ [٥:٤٤]

“እኛ ተውራትን በውስጥዋ መምሪያና ብርሃን ያለባት ስትኾን አወረድን። እነዚያ ትዕዛዝን የተቀበሉት ነቢያት በእነዚያ አይሁዳውያን በኾኑት ላይ በርሷ ይፈርዳሉ። ሊቃውንቱና ዐዋቂዎቹም ከአላህ መጽሐፍ እንዲጠብቁ በተደረጉትና በርሱም ላይ መስካሪዎች በኾኑት (ይፈርዳሉ)።” (አል-ማኢዳህ 5፤ 44)

وَمَا قَدَرُوا اللَّهَ حَقَّ قَدْرِهِ إِذْ قَالُوا مَا أَنْزَلَ اللَّهُ عَلَى بَشَرٍ مِنْ شَيْءٍ قُلْ مَنْ أَنْزَلَ الْكِتَابَ الَّذِي جَاءَ بِهِ مُوسَى نُوراً وَهُدىً لِلنَّاسِ تَجْعَلُونَهُ قَرَاطِيسَ تُبْدُونَهَا وَتُخْفُونَ كَثِيراً [٦:٩١]

“ ‘አላህ በሰው ላይ ምንም አላወረደም’ ባሉም ጊዜ አላህን ተገቢ ክብሩን አላከበሩትም። (እንዲህ) በላቸው፡- ‘ያንን ብርሃንና ለሰዎች መሪ ኾኖ ሙሳ ያመጣውን መጽሐፍ ክፍልፍሎች የምታደርጉት ስትኾኑ ማን አወረደው?’ ” (አል-አንዓም 6፤91)

2. በነቢዩ ዒሣ (ዐ.ሠ) ላይ የወረደው ኢንጂል /ወንጌል/

አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ አለ

وَقَفَّيْنَا عَلَىٰ آثَارِهِم بِعِيسَى ابْنِ مَرْيَمَ مُصَدِّقًا لِّمَا بَيْنَ يَدَيْهِ مِنَ التَّوْرَاةِ وَآتَيْنَاهُ الْإِنجِيلَ فِيهِ هُدًى وَنُورٌ وَمُصَدِّقًا لِّمَا بَيْنَ يَدَيْهِ مِنَ التَّوْرَاةِ وَهُدًى وَمَوْعِظَةً لِّلْمُتَّقِينَ [٥:٤٦]
“በፈለጎቻቸውም (በነቢያቶቹ ፈለግ) ላይ የመርየምን ልጅ ዒሳን ከተውራት በስተፊቱ ያለውን አረጋጋጭ ሲኾን አስከተልን። ኢንጂልንም በውስጡ ቀጥታና ብርሃን ያለበት በስተፊቱ ያለችውን ተውራትንም የሚያረጋግጥ ለጥንቁቆችም መሪና ገሳጭ ሲኾን ሰጠነው።” (አል-ማኢዳህ 5፤ 46)

3. በነቢዩ ዳውድ (ዐ.ሠ) ላይ የወረደው ዘቡር
አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ አለ

وَآتَيْنَا دَاوُدَ زَبُوراً [١٧:٥٥]

“ዳውድንም ዘቡርን ሰጥተነዋል።” (አል-ኢስራእ 17፤ 55)
4. በነቢዩ ኢብራሂም እና በነቢዩ ሙሣ (ዓ.ሠ) ላይ የወረዱት ፅሁፎች /ሱሁፍ/
አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ አለ
أَمْ لَمْ يُنَبَّأْ بِمَا فِي صُحُفِ مُوسَىٰ ﴿٣٦﴾ وَإِبْرَاهِيمَ الَّذِي وَفَّىٰ ﴿٣٧﴾ أَلَّا تَزِرُ وَازِرَةٌ وِزْرَ أُخْرَىٰ ﴿٣٨﴾ وَأَن لَّيْسَ لِلْإِنسَانِ إِلَّا مَا سَعَىٰ ﴿٣٩﴾ وَأَنَّ سَعْيَهُ سَوْفَ يُرَىٰ ﴿٤٠﴾ ثُمَّ يُجْزَاهُ الْجَزَاءَ الْأَوْفَىٰ ﴿٤١﴾ وَأَنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ الْمُنتَهَىٰ ﴿٤٢﴾

“ይልቁንም በዚያ በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ ባለው ነገር አልተነገረምን? በዚያም (የታዘዘውን) በፈጸመው በኢብራሂም (ጽሑፎች ውስጥ ባለው አልተነገረምን?) (እርሱም ኃጢያት) ተሸካሚ ነፍስ የሌላይቱን ነፍስ ኃጢኣት አትሸከምም። ለሰውም ሁሉ የሠራው እንጅ ሌላ የለውም። ሥራውም ሁሉ ወደ ፊት ይታያል። ከዚያም ሙሉውን ምንዳ ይመነዳዋል። መጨረሻውም ወደ ጌታህ ብቻ ነው።” (አን-ነጅም 53፤36-42)

قَدْ أَفْلَحَ مَن تَزَكَّىٰ ﴿١٤﴾ وَذَكَرَ اسْمَ رَبِّهِ فَصَلَّىٰ ﴿١٥﴾ بَلْ تُؤْثِرُونَ الْحَيَاةَ الدُّنْيَا ﴿١٦﴾ وَالْآخِرَةُ خَيْرٌ وَأَبْقَىٰ ﴿١٧﴾ إِنَّ هَٰذَا لَفِي الصُّحُفِ الْأُولَىٰ ﴿١٨﴾ صُحُفِ إِبْرَاهِيمَ وَمُوسَىٰ ﴿١٩﴾

“የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ። የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ። ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ትመርጣላችሁ። መጨረሻይቱ (ሕይወት) በላጭ ሁል ጊዜ ዘውታሪም ስትኾን። ይህ በፊተኞቹ መጻሕፍት ውስጥ ያልለ ነው። በኢብራሂምና በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ።” (አል-አዕላ 87፤ 14-19)

ከአቢ ዘር (ረ.ዐ) እንደተዘገበው ለአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ)፡-

“በኢብራሂም ላይ የወረዱ ፅሁፎች ምን ይመስሉ ነበር? በማለት ጠየቅኳቸው። እርሣቸውም ‘ሁሉም ምሣሌዎች ናቸው።’ በማለት መለሱ።

 በቀጣዩ ክፍል የምናየው ይሆናል ኢንሻአላህ

✍ሀዩነኝ የኡስታዜ አቡሀይደር ተማሪ

https://t.me/KatetagiwuMangad


Репост из: Eliyah Mahmoud
ኢዜማ እስልምናን የኢትዮጵያ ደህንነት ስጋት አድርጎ የገለጸበት ሚስጥራዊ ሰነድ ይፋ ወጣ‼
====================================================
«የኢዜማን እውነተኛ ማንነት የማያውቀው ህዝብ እንዳይሸወድ መረጃውን ሼር በማድረግ ህዝቡን እናንቃ! የፓርቲው ማንነት ከቀን ወደ ቀን ይበልጥ ፍንትው እያለ መጥቷል።»
||
✍ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) የተሰኘው የፖለቲካ ፓርቲ በዘንድሮው 6ኛው የሃገራችን ምርጫ ከሚሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል አንዱ ነው። በርካታ እጩዎችን በማስመዝገብ ከአሁኑ ገዢ ፓርቲ (ብልፅግና) በመቀጠል ሁለተኛ ደረጃ ይዟል።

✔ የዚህ ፓርቲ ሊቀመንበር የሆኑት ብርሃኑ ነጋ (ዶ/ር) የርሳቸው ፓርቲ ከተመረጠ ኢስላማዊ ባንክ እንደማይፈቅድ ከአሁን በፊት የተናገሩ ሲሆን፤ ይህን እውነታ ከቀናት በፊት በድጋሜ ማረጋገጣቸው ይታወቃል።
*
✔ ይህ በእንዲህ እንዳለ ሰሞኑን ከዚህ ፓርቲ ያፈተለከ አንድ ሚስጥራዊ መረጃ ይፋ ወጥቷል።
ኢዜማ የሃገሪቷን ወቅታዊ የደህንነት ስጋት የተነተነበት አንድ ባለ 14 ገፅ ሚስጥራዊ ሰነድ አዘጋጅቷል። ዶ/ር ብርሃኑ በዚህ ሰነዳቸው ላይ ከፓርቲያቸው ከኢዜማ እና ከመሰሎቹ በስተቀር ለሀገር ደህንነት ስጋት ብሎ ያልፈረጁት የለም።
ሰነዱ «የሃገሪቷ ወቅታዊ የደህንነት ስጋት ትንተና» ይሰኛል‼

[ሙሉውን 14ቱንም ገፅ በዚህ ሊንክ ብትገቡ ታገኙታላችሁ።
https://t.me/MuradTadesse/10898]
*
✔ በዚህ ሰነድ ላይ በርካታ አካላት የሃገራችን የደህንነት ስጋት ተብለው የተጠቀሱ ሲሆን፤ እስልምናን በተመለከተ ግን «ወቅታዊ የብሄራዊ ደህንነት ስጋቶች» በተሰኘው የሰነዱ የመጀመሪያ ክፍል ላይ «ጽንፈኝነት» በተሰኘ ዐውድ ስር ገፅ 7 እና 8 ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት በአጽንኦት ተጠቅሷል።
ሰነዱ ካነሳቸው ነጥቦች መካከል፦
①) የእስልምና አክራሪነት በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች እየተስፋፋ መሆኑ፣
②) የእስልምና ኃይማኖት ተከታዮች በብዛት በሚገኙባቸው አካባቢዎች ላይ የእስልምናን አክራሪነት በወጣቱ ላይ የማስረጽ ሥራ እየተሠራ መሆኑ፣
③) በሃገሪቱ የሚነሱ የተለያዩ ቀውሶችን ከማስነሳት አልፎ እስከ ማባባስ ድረስ እየሠሩ መሆኑ፣
④) መስጅዶች የዚህ እንቅስቃሴ ዋነኛ መፍለቂ መሆናቸው፣
⑤) በተለያዩ ባለሃብቶች እንደሚደግፉና የተጠናከረ ህቡዕ አንድነት ያላቸው መሆኑን፣
⑥) ከግብፅ፣ ከሳዑዲ ዓረቢያና ከኳታር ጋር ለዚሁ አላማ ጥብቅ ግንኙነት ያላቸው መሆኑ፣
⑦) የገቢ ምንጫቸው ከውጭ የሚላክ ገንዘብ፣ ከኮንትሮባንድ ሥራ፣ ከመዓድናት ሽያጭና መንግስት በማያውቀው በሌላ መልክ ገቢ የሚያገኙ መሆኑን፣
⑧) አይኤስ፣ አል-ቃዒዳና አል-ሸባብ በኢትዮጵያ እንቅስቃሴ የጀመሩ መሆኑን፣
⑨) ሙስሊም ምሁራንና የማህበረሰብ አንቂዎች ለእምነታቸው የተቆረቆሩ በመምሰል ህዝብ ወደ ጽንፈኝነት እንዲገባ ለመሥራት አቅደው ቆርጠው የተነሱ መሆኑን፣
⑩) ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) በጽንፈኛ ሙስሊሞች የሚሾፈር ስለሆነ እንዲታገድ… ወዘተ የሚሉ እጅግ በጣም አደገኛና መርዘኛ ሃሳቦች ተነስተዋል።

✔ በግሌ ከዚህ ሰነድና ከዚህ በፊትም ኢዜማ ካለው አመለካከት በመነሳት፤
ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ደህንነት ከኢዜማ የበለጠ ስጋት እንደሌለ ተረድቻለሁ።
*
የሚመለከተው አካል የዚህን ፓርቲ መርዘኝነት ተረድቶ ከወዲሁ ከምርጫ ቦርድ ቢያሰናብተው መልካም ነው።
ገና ስልጣን ሳይዙ ይህን ያክል መርዘኛ ከሆኑ፤ አቅሙን ካገኙ ደግሞ ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ ለመገመት የግድ ሩቅ አዋቂ መሆን አይጠበቅም።

*
«የፓርቲውን መርዘኝነት ሼር በማድረግ እናሳውቅ! ህዝቡ ሊነቃ ይገባል!»
||
t.me/MuradTadesse


Super Hitman ኢያቡስቴ🦸‍♂🦹‍♂

《የዳዊት ኃያላን ስም ይህ ነው። የአለቆች አለቃ የሆነ ከነዓናዊው #ኢያቡስቴ ነበረ፤ እርሱም #ጦሩን #አንሥቶ #ስምንት #መቶ #ያህል #በአንድ #ጊዜ #ገደለ።》

መጽሀፈ ሳሙኤል ካልዕ 23፡8

t.me/Alfurqan11
@Alfurqan12
@Abu_mussaab


🎧 *ሁሉነገር* *የእርሱ* *ብቻነው* # *3*
📖 سورة النمل ምዕራፍ (27)
🌸🍃 part / 3 🕊{{ሱረቱል ነምል}}

🌸🍃🎙 *በኡስታዝ* *ኻሊድ* *ክብሮም*



@KatetagiwuMangad


Репост из: Sαlαh Responds ⛉
♻️ከ9 ዓመት በፊት ወንድም "አሊ አታይ" እና ታዋቂው የክርስትና አቃቤ "ዴቪድ ውድ" በአንድ ርዕስ ላይ ይወያያሉ፣ ውይይቱ ጥያቄ እና መልስ ላይ ሲደርስ ወንድም "አሊ አታይ" ጥያቄውውን እንዲህ ብሎ ያቀርባል።

🎙Ali Ataie:- ማርቆስ 16፥18 ላይ ያመኑት ሰዎች የሚጎዳቸው ነገር ቢጠጡ እንኳ ምንም እንደማይሆኑ ተፅፏል እስኪ አንተ ይህ ቃል የእግዚአብሔር ቃል ነው የምትል ከሆነ ይህንን መርዝ ጠጣው ካልጠጣሀው መፅሐፍ ቅዱስ የአምላክ ቃል እንዳልሆነ መስክረሃል ማለት ነው።


🎙David Wood:- በአለማችን ላይ ያሉ ሁሉም የመፅሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ያ ክፍል ተዓማኒ ነው ብለው አያምኑም፣ ቡኋለ ላይ የተጨመረበት ጭማሪ ነው፣ ጥንታውያን ቅጂዎች ያንን ክፍል የላቸውም፣ ስለዚህ ያ ሀሳብ በጥንታዊያን ምንጮች ውስጥ የለም፣ የኛ ጥንታዊያን ምንጮች በጭራሽ ስለመርዝ የሚያወራውን ክፍል አልያዙትም ስለዚህ መጠጣት አልችልም (Every bible scholar in the world says that was not authentic, this was a later addition and so that's not in the early source material, as far as our earliest records don't have that part about the poison) ውይይቱን ለማግኘት «ይህችን» ይጫኑ

እኛም ስንል የነበረው ይህንኑ ነው፣ በክርስትናው ዓለም ስመጥር የሆኑትና በግምባር ቀደም የሚጠቀሱ ሁለቱ ጥንታዊያን እደ-ክታባት ማርቆስ ወንጌል ምዕራፍ 16 ከ ቁጥር 9-20 ድረስ የላቸውም። ዶከተር ዴቪድ እንደመሰከረው ስለመርዝ የሚያወራው ክፍል ጨምሮ 12ቱ አንቀፆች ከግዜ ቡኋለ የተጨመሩበት የብርዘት ውጤቶች ብቻ ናቸው (መፅሐፍ ቅደስ ተበርዟል ስንላችሁ በማስረጃ ነው)

Sαlαh responds ተቀላቀሉን


Christmas in the Quran The Truth

Christians associate christmas with the birh of jesus (pbuh) on dec 25th.for orthodox christians.it's january7th.the point is.here is the truthful story about the birth of jesus/lsa(pbuh).and who cares what day it was . it changes nothing .only Allah Knows exactly which day it was and regardless.it's irrelevant
@KatetagiwuMangad


ሙ፦ ከመልአክት ፍጥረት እና ከሰው ፍጥረት የትኛው ይበልጣል?

ክ፦ ምን ሆነሃል መጽሀፉ #ሰውን #በእግዚአብሔር #አምሳል #ፈጠረው! እንጂ መች መልአክት በእግዚአብሔር አምሳል ተፈጠሩ ይላል?

ሙ፦ እሺ እንደዛ ከሆነ መጨረሻችሁ ለምን ቁልቁል መውረድ ሆነ?

ክ፦ አልገባኝም ምን ለማለት ፈልገህ ነው?

ሙ፦ እኔማ ያልኩት በመጀመርያ ስትፈጠሩ ከመልአክትም አምሳል በላይ በሆነ በእግዚአብሔር አምሳል ተፈጥረናል ካላችሁ በኋላ እስክትሞቱ ድረስ በተስፋ የጠበቃችኋትና ሙሉ እድሜአችሁን በኖራችሁላት ዘላለማዊ ገነት ስትገቡ ቁልቁል ወርዳችሁ ሰውነታችሁን ጥላችሁ ለምን በመልአክት አምሳል እንሆናለን ትላላችሁ?

ክ፦ እ? ምን አይነት ጥያቄ ነው መጽሀፍ ቅዱስ ላይ ያለ ጥያቄ ብቻ ነው መጠየቅ ያለብህ አትፈላሰፍ፡፡

ሙ፦ ባይብል ላይ የጥያቄ ማኑዋል አለ እንዴ?🤔
መልሱ በባይብል የለም እያልክ ከሆነ ያግባባናል አይደንቀኝም ብዙ ጥያቄዎቼን ባይብል አይመልሳቸውም፡፡ ይህ ደግሞ የሚሆነው ከኔ ጥያቄዎች ችግር ሳይሆን ከመጽሀፍህ የመልስ እጦት ድርቅ ነው፡፡

ክ፦ አይ አይ የኔ እውቀት ማነስ እንጂ መጽሀፍ ቅዱሳችንማ ለሁሉም መልስ አለው! ቆይማ እዚህ ግሩፕ ያሉትን ልጠይቃቸው ከኔ በውቀት የሚበልጡ ብዙ ወንድሞቼ አሉ፡፡

ሙ፦ እና ቅድም ባይብል ላይ የለም ከምትል እንደሱ ችግርህን አትናገርም ነበር?😁 ለማንኛውም ጠይቃቸው እኔ መልስ ነው ምፈልገው፡፡

ክ፦ እሺ ተወዳጆቼ ለዚህ እስላም ጥያቄ ማነው ሚመልስልኝ?

t.me/Alfurqan11
@Alfurqan12
@Abu_mussaab

Показано 20 последних публикаций.

327

подписчиков
Статистика канала