ማስታወቂያ
ትምህርት ሚኒስቴር ከሰኔ 2/2017 ጀምሮ የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ለሚወስዱ መደበኛ እና ኢ-መደበኛ ፕሮግራም ዕጩ ተመራቂዎች እና ዳግም ተፈታኞች ፈተናውን ለመውሰድ የብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) እንደቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡ ይታወቃል።
በመሆኑም በዩኒቨርሲቲያችን ትምህርት ላይ ያላችሁ እና ከዚህ ቀደም ተፈትናችሁ ማለፊያ ውጤት ሳታሟሉ የቀራችሁ ዳግም ተፈታኞች ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ምዝገባ እንድታካሂዱ አጥብቀን እናስታውቃለን።
በዚህ መሰረት:-
የመጀመሪያ ዙር ተፈታኞች የመታወቂያውን FAYDA FIN ቁጥር እስከ ረቡዕ ሜያዚያ 22/2017 ዓ/ም ድረስ በአካዳሚክ ፕሮፋይላችሁ /SMiS) እንድታስገቡ፣
ዳግም ተፈታኝ አመልካቾች የአገልግሎት ክፍያ በቴሌ ብር በኩል ብቻ ከፍላችሁ ከሚያዝያ 14/2017 ዓ.ም እስከ ግንቦት 05/2017 ዓ.ም ድረስ ከላይ የተጠቀሱትን ቅድመ ሁኔታዎች በማሟላት በhttps://exam.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ማሳወቁን እንገልጻለን፡፡
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሬጂስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት
ትምህርት ሚኒስቴር ከሰኔ 2/2017 ጀምሮ የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ለሚወስዱ መደበኛ እና ኢ-መደበኛ ፕሮግራም ዕጩ ተመራቂዎች እና ዳግም ተፈታኞች ፈተናውን ለመውሰድ የብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) እንደቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡ ይታወቃል።
በመሆኑም በዩኒቨርሲቲያችን ትምህርት ላይ ያላችሁ እና ከዚህ ቀደም ተፈትናችሁ ማለፊያ ውጤት ሳታሟሉ የቀራችሁ ዳግም ተፈታኞች ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ምዝገባ እንድታካሂዱ አጥብቀን እናስታውቃለን።
በዚህ መሰረት:-
የመጀመሪያ ዙር ተፈታኞች የመታወቂያውን FAYDA FIN ቁጥር እስከ ረቡዕ ሜያዚያ 22/2017 ዓ/ም ድረስ በአካዳሚክ ፕሮፋይላችሁ /SMiS) እንድታስገቡ፣
ዳግም ተፈታኝ አመልካቾች የአገልግሎት ክፍያ በቴሌ ብር በኩል ብቻ ከፍላችሁ ከሚያዝያ 14/2017 ዓ.ም እስከ ግንቦት 05/2017 ዓ.ም ድረስ ከላይ የተጠቀሱትን ቅድመ ሁኔታዎች በማሟላት በhttps://exam.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ማሳወቁን እንገልጻለን፡፡
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሬጂስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት