ብሒለ አበው


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Другое


የአባቶቻችን ተግሳፅና ምክር
ለ ሃሳብ አስተያየት @fikreabe

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Другое
Статистика
Фильтр публикаций




📷 እርግጠኛ ነኝ ፕሮፍይሎን ለመቀየር ፈልገው ፕሮፍይል የሚያደርጉት ጠፍቶ  ተቸግረው ያውቃሉ።

የናንተን ችግር ለመፍታት በአይነቱ ለየት ያለ አዲስ መንፈሳዊ ቻናል ይዘንላችሁ መተናል ከናንተ የሚጠበቀው ከታች ባለው ሊንክ join ማድረግ ብቻ ነው👇👇👇👇👇👇📷

https://t.me/addlist/isQbYInIIR0zNTc0


Репост из: *****ny
ጎልልልልልልልልልል ሮናልዶዶዶዶ

ሮናልዶ አሁን ለአል ናስር ተገልብጦ ያስቆጠራትን አስደናቂ ኳስ ይመልከቱ 👇👇

https://t.me/addlist/-qAEJW_rhus0NGVk






Репост из: ࿇EL҉O҉H҉E҈ P҉I҉C҉T҉U҉R҉E҈S҉࿇
99 ጥሩ ነገር ሰርተህ 1 መጥፎ ስራ ብትሰራ በሰዎች ዘንድ አንተ መጥፎ ሰዉ ነህ” “99 መጥፎ ስራ ሰርተህ 1 ጥሩ ስራ ብትሰራ በ ክርስቶስ ዘንድ መጥፎ ስራዎችህን ይቅር ይልሃል

“ መልካም በዓል ይሁንላችሁ ”


Репост из: 🇱🇷 የኆኅተ ሰማይ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እና የሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም{ ካሊፎርንያ}
ውድ የቻናላችን ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ

የአብነት ትምህርት በነፃ ለመማር
ምርጫችሁን ያደረጋችሁ በመመዝገብ በብፁዕነታቸው አማካኝነት በነፃ አብነት መማር ትችላላችሁ

👉ቅኔ

👉አቋቋም

👉ጾመ ድጓ/ምዕራፍ ወይስ ሌላ...

ምን እከፍላለው ብለው ሳይጨነቁ ፣ ያለ ምንም ክፍያ ልናስተምሮት በonline ዝግጅታችንን ጨርሰናል !!! ምዝገባው የሚቆየው እስከ ዳግመ ትንሳኤ ሲሆን

ሰፊ ማብራርያ የምትፈልጉ
👇👇👇👇👇👇👇

@Kinfemikael12

ማነጋገር ትችላላችሁ
በተጨማሪ

👉 የፈለጉትን ትምህርት ቀለል ባለ መንገድ እና በአጭር ጊዜ ለማስጨረስ የራሳችን ማስተማሪያ መንገድ አዘጋጅተን እየጠበቅናችሁ ነው

👉 በእያንዳንዱ ጉባኤም ከ50 በላይ ተማሪ ስለማንቀበል ሳይሞላብዎት በፍጥነት ይመዝገቡ🙏 የቀረን ጥቂት ቦታ ስለሆነ ቶሎ ይመዝገቡ 🙏

ቻናሉ 👇👇👇👇👇

https://t.me/Abnetschoolcalifornia


Репост из: 🙏 ማርያም እምነ 🙏
ዮም ፍስሐ ኮነ በሰንበተ ክርስቲያን እስመ  ተንሥአ ክርስቶስ እም ሙታን ቀደሳ ወአክበራ እም ኵሎን መዋዕል አልዓላ አማን ተንሥአ እም ሙታን።🥰
🙏❤️❤️❤️🙏

https://t.me/weladite_amlaki
https://t.me/weladite_amlaki
https://t.me/weladite_amlaki


#ትርጉም፦


https://t.me/weladite_amlaki
https://t.me/weladite_amlaki
https://t.me/weladite_amlaki


በክርስቲያን ሰንበት ዛሬ ደስታ ሆነ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሥቷልና የክርስቲያን ሰንበትን ቀደሰ አከበረ ከሁሉ ዕለታትም ከፍ ከፍ አደረጋት በእውነት ከሙታን መካከል ተነሳ።🥰
🙏❤️❤️❤️🙏


Репост из: 🙏 ማርያም እምነ 🙏
ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፊቱ በወዝ ተሸፍኖ ባየችው ጊዜ በፍጥነት እየሮጠች በመጎናጸፊያዋ ፊቱን አበሰችለት፡፡ይህች ቅድስት እንስት ማን ትሰኛለች
Опрос
  •   ቅድስት ቬሮኒካ
  •   ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ
  •   ቅድስት አርሴማ
  •   ቅድስት እንባ መሪና
19 голосов


ከጀርባህ ላይ ያለው የጅራፍ ንቅሳት
እኛን የመውደድህ የዘላለም ምትራት
የፋሬስ የሳዶቅ ያለማመን ደባ
የጲላጦስ ግርፊያ የሄሮድስ ካባ
ከፊትህ የወጣው የደም ጎርፍ እና እንባ
ላንተ ስቃይ ናቸው ለኛ ግን ደስታ
መከራህ ነውና የመዳን አለኝታ
ጅራፍ እና ቡጢ ምራቅና ሃሞት
ለአይን ደስ የማይል የስቃይ ደምግባት
በደም የተረጩ ቅዱሳት አልባሳት
እኒህ ናቸው ውበት የጌታ ደምግባት
የመዳን አለኝታ የዘላለም ምትራት
ውዴን ያላያችሁ
እኔ ልንገራችሁ
ፍቅሩን ላሳያችሁ
ድምጹን ላሰማችሁ
ምራቅ ተቀብቷል
ቡጢ ተቀብሏል
ኃጢዓት ተሸክሟል
በቁንዳለው መሃል የደም ጎርፍ ይፈሳል
የፍቅር ንጉስ ነው የእሾህ አክሊል ደፍቷል
ውዴን ያላያችሁ
ድምጹን ያልሰማችሁ
ፍቅሩን ልንገራችሁ
ዐይኑ ፍቅር ያለቅሳል
ጎኑ ደም ይረጫል
ፅህሙ ተነጭቷል
ልብሱ ሜዳ ወድቋል
በቃሉ ቅዱስ ነው ይቅርታን ይሰዋል
ከፍቅር ትከሻው የዓለም ደዌን አዝሏል
ከጀርባው ላይ ያለው የጅራፍ ንቅሳት
እኛን የመውደዱ የዘላለም ምትራት
ለእሱ ስቃይ ናቸው ለኛ ግን ደስታ
መከራው ነውና የመዳን አለኝታ
ይህ ሁሉ ቢሆንም
ይህ ሁሉ ቢሆንም
የሰው ልጆች ድፍረት ክብሩን አይቀንስም
ስለሰው መድከሙም ኃይሉን አያወርድም
ስሙ እግዚአብሔር ነው
ስሙ ይቅርታ ነው
ስሙ መሀሪ ነው
የፈረሱን ብርታት ብቃቴ ነው የሚል
ብዛቱን ተማምኖ የሚታበይ ልዑል
በ'ሱ ስም ይወድቃል በስሙ ይጣላል
ስሙ ሁሉን ቻይ ነው ሁሉንም አድራጊ
ታላቁን የሚጥል ለታናሽ ተዋጊ
ውዴን ያላያችሁ
ድምጹን ላሰማችሁ
እኔ ልንገራችሁ
ፍቅሩን ላሳያችሁ
ከጀርባው ላይ ያለው የጅራፍ ንቅሳት
እኛን የመውደዱ የዘላለም ምትራት
ለርሱ ስቃይ ናቸው ለኛ ግን ደስታ
መከራው ነውና የመዳን አለኝታ
እናም ጌታችን ሆይ...
ያመኑት ይፅናኑ የወጉህም ይዩህ
በደም የተረጩ ልብሶችህን ለብሰህ
አሜን ጌታችን ሆይ ናልን ተመልሰህ


Репост из: *****ny
ከ17 ደቂቃ ቦኃላ ይጠፋል


የ 200 ብር ካርድ የሚያስሸልም ጥያቄ!

በኢትዮጵያ በጣም አስቸጋሪ የነበረዉ  ረሀብ መች አመተምህረት ነበረ


📌ስለ ጉልባን አንድ ምስጢር ልነግራችሁ ወደድኩ❗️

⭐️ጉልባን በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ትምህርት የሚሰራው ከስንዴ እና ከባቄላ ተዘጋጅቶ ነው።

👉የጉልባኑ ባቄላ ሲዘጋጅ ደግሞ፦
➩ባቄላው ይታመሳል፣
➩ባቄላው ይፈተጋል፣
➩ባቄላው ይከካል።

👉የጉልባኑ ስንዴው ሲዘጋጅ ግን፦
➩ስንዴው አይከካም፣
➩ስንዴው አይፈተግም፣
➩ስንዴው አይታመስም።

📌የሊቃውንቱ አስተምህሮ ምስጢር ምንድነው❓

⭐️ይገርማችኋል እንዲህ መሆኑ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት ድንቅ ምስጢር እና ምሳሌነት አለው።ይኸውም ምሳሌነቱ ስለ እኛ በተዋሕዶ ለከበረው አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መከራ መታሰቢያ ነው።ማለትም ባቄላው የሥጋ ስንዴው ደግሞ የመለኮት ምሳሌ ነው።ምንም እንኳን መለኮት ከሥጋው ያልተለየው አምላክ ቢሆንም ሕማሙ ግን መለኮትን አላገኘውም።

⭐️የተዋሕዶ መዶሻ የተባለ ቅዱስ ቄርሎስ እንዳስተማረው ነገረ ተዋሕዶን በጋለ ብረት እንዳስተማረው ብረትን ከእሳቱ ውስጥ ቢጨምሩት ብረቱ እሳቱን ይመስላል እሳቱም የብረቱን ቅርፅ ይይዛል ብረቱን ቢመቱት ይለዝባል የማይጨበጠው እሳትም ከብረት ስለተዋሐደ አንጥረኛው ይመተዋል እሳቱን ግን አያገኘውም።

⭐️መለኮት የተዋሐደው ሥጋ መከራን ተቀበለ በሥጋም ሞተ፤ ለመለኮት ግን ሕማም ድካም ሞት አይስማማውም፤ ይኸውም መለኮት ከሥጋው አንደተዋሐደ በነፍስ ወደ ሲኦል ወርዶ ምርኮን ማረከ ነፍሳትን ነፃ አወጣ ገነትም አስገባቸው ፤መለኮት የተዋሐደው ሥጋ ወደ መቃብር ቢወርድም በሶስተኛውም ቀን በታላቅ ኃይል በሥልጣን ክርስቶስ ኢየሱስ ሞትን ድል አድርጎ ተነሳ።

👉ግሩም የነገረ ተዋሕዶ ምስጢር አለው!!!🤲🤲🤲🙏🙏


በሕማማት ሐሙስ አምላክ ምን አደረገልን? || መምህር ዘበነ ለማ


Репост из: የተዋሕዶ ፍሬዎች
Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
በሕማማት ሐሙስ አምላክ ምን አደረገልን? || መምህር ዘበነ ለማ


Репост из: የተዋሕዶ ፍሬዎች
የምሴተ ሐሙስ የጸሎት ፣ የቅዳሴ እና የሕጽበተ እግር ሥነ ሥርዓት !

         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬


Репост из: የተዋሕዶ ፍሬዎች
ዕለተ ሐሙስ ፣ ጸሎት ሐሙስ ፣ ኅጽበተ እግር ፣ የምሥጢር ቀን

ጸሎተ ሐሙስ ጸሎተ ቅዳሴ የተጀመረበት ጥንተ ዕለት፣ የሐዲስ ኪዳን ሥርዓተ ቁርባን የተመሠረተበት የተቀደሰ፣ የተመረጠና የከበረ ዕለት በመሆኑ እንዲሁም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የአይሁድ ጭፍሮች እስኪይዙት ድረስ በዚህ ዕለት በጌቴሴማኒ ሲጸልይ በማደሩ “ጸሎተ ሐሙስ” ፣ ደቀ መዛሙርቱን እግር ዝቅ ብሎ በማጠቡ ምክንያት “ኅጽበተ እግር” ፣ ጌታችን ኅብስቱንና ጽዋውን አንሥቶ "ይህ ስለ እናንተ በመስቀል ላይ የሚቈረሰው ሥጋዬ ነው፡፡ እንካችሁ ብሉ፡፡ ይህ ስለ እናንተ ነገ በመስቀል ላይ የሚፈስ ደሜ ነው ፤ ከእርሱም ጠጡ" በማለት እርሱ ከእኛ፤ እኛም ከእርሱ ጋር አንድ የምንሆንበትን ምሥጢር ከጠላት ዲያብሎስ ሰውሮ፣ ለደቀ መዛሙርቱ የገለጠበት ቀን በመሆኑና አማናዊውን ምሥጢረ ቁርባን የመሠረተበት ቀን ነውና “የምሥጢር ቀን” ይባላል። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለመጨረሻ ጊዜ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር የፋሲካን ራት የተመገበበት ዕለት ነውና “የመጨረሻ ራት” ይባላል።

ጌታችን በዚህ ዕለት "እናንተ ለወንድሞቻችሁ እንደዚህ አድርጉ" በማለት የደቀ መዛሙርቱን እግር ያጠበበት ነው። ይህም የሚያሳየው "እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለው፤ ባሪያ ከጌታው አይበልጥም፤ መልክተኛም ከላኪው አይበልጥም፤ ይህን ብታውቁ ብታደርጉትም ብፁዓን ናችሁ" በማለት ትሕትናውን አሳይቷል፡፡ [ዮሐ.፫፥፮-፯]

አባቶችንም በዚህ ዕለት ጌታችንን አብነት አድርገው በቤተ ክርስቲያን የምእመናኑን እግር ያጥባሉ፤ እኛም ከጌታችን ትሕትናን እንማራለን፤ በሕይወታችን ታዛዦች፣ ትሑትና ቅን ልሆንና ከእርሱ እንድንማር ባስተማረን መሠረት አርአያውን ልንከተል ይገባል፡፡

         †              †               †


Репост из: የተዋሕዶ ፍሬዎች
#ሕጽበተ_እግር

✍️በዚህ ዕለት ጌታችን በትሕትና፣ በፍቅር፣ በመታዘዝና በማገልገል አርአያ ለመሆን የደቀ መዛሙርቱን እግር በማጠቡ ሕጽበተ ሐሙስ በመባልም ይጠራል፡፡ ይህም ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለምን ዅሉ ኃጢአት ለማጠብ የመጣ የንጽሕና፣ የቅድስና አምላክ መኾኑን ያጠይቃል፡፡ ስለዚህም ዕለቱ ‹ሕጽበተ ሐሙስ› ይባላል፡፡ ይህ የሚያሳየው እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጠኋችሁ የተባለውን ነው። እውነት እውነት እላችኋለሁ ባሪያ ከጌታው አይበልጥም፣ መልእክተኛም ከላከው አይበልጥም፣ ይህን ብታውቁ ብታደርጉትም ብፁዓን ናችሁ (ዮሐ.፲፫፣፲፮-፲፯) በማለት ትሕትናውን አሳይቷል፡፡

ጌታ በዚህ ዕለት የደቀ መዛሙርቱን እግር ሲያጥብ እኔ መምህራችሁ ስሆን እግራችሁን ካጠብኳችሁ ምሳሌውን አሳየኋችሁ፡፡ ነገር ግን ከእናንተ አንዱ ለሞት አሳልፎ ይሰጠኛል አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም  እኔ እሆን? እኔ እሆን? ተባባሉ፡፡ ጌታም ኅብስት ቆርሼ፣ ከወጡም አጥቅሼ የምሰጠው እርሱ ነው አላቸው፡፡ ይሁዳን ማመልከቱ ቢሆንም ስለማን እነደተናገረ አልገባቸውም።

እነሆ ይህንን ዕለት በማስታወስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሊቃነ ጳጳሳት ጀምሮ እስከ ቀሳውስት ያሉት አባቶች በየደብራቸው  በመዓርግ ከእነሱ በእውቀት፣ በእድሜ፣ በክብር፣ በስልጣል  የሚያንሱ የካህናትን፣ የዲያቆናትን እና የምእመናንን እግር በማጠብ ክርስቶስን በተግባር ይሰብካሉ። የሚያጥቡትም የወይራና የወይን ቅጠል በውኃ በመዘፍዘፍ ነው፡፡ 
 
ክርስቲያኖች ሆይ! ይህ ቀን ጌታችን ከሐዋርያት ጋር የነበረበት የመጨረሻ ቀን ነበር፡፡ ስለዚህም በየዕለቱ ያደረጋቸው ነገሮች ትዝታን የሚጥሉ ጌታም ለእኛ ያለውን ፍቅር የሚገልጹ ድርጊቶች ነበሩ፡፡ (ዮሐ 13÷1)
https://t.me/yetewahedofera


Репост из: የተዋሕዶ ፍሬዎች
#ፀሎተ ሀሙስ

#ሀሙስ ምሽት ጌታችን ያደረገልን ትህትና ዮሐንስ 13

እግራቸውንም አጥቦ ልብሱንም አንሥቶ ዳግመኛ ተቀመጠ
እንዲህም አላቸው፦ ያደረግሁላችሁን ታስተውላላችሁን?
እናንተ መምህርና ጌታ ትሉኛላችሁ እንዲሁ ነኝና መልካም
ትላላችሁ።

እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ
እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ
ይገባችኋል።

እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ
ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና።

እውነት እውነት እላችኋለሁ ባሪያ ከጌታው አይበልጥም።
መልእክተኛም ከላከው አይበልጥም። 17 ይህን ብታውቁ
ብታደርጉትም ብፁዓን ናችሁ።
ስለ ሁላችሁ አልናገርም እኔ የመረጥኋቸውን አውቃለሁ
ነገር ግን መጽሐፍ፦ እንጀራዬን የሚበላ በእኔ ላይ ተረከዙን
አነሣብኝ ያለው ይፈጸም ዘንድ ነው።

በሆነ ጊዜ እኔ እንደ ሆንሁ ታምኑ ዘንድ ከአሁን ጀምሬ
አስቀድሞ ሳይሆን እነግራችኋለሁ።

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ለዘላለም ትኑር በመጀመሪያነት ያጋሩት፦
በሰሞነ ህማማት የሚገኙ እለታትና ስያሚያቸው ........እለተ ሀሙስ -በዚህ እለት ጌታችን አምላካችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍፁም ሰው ፍፁም አምላክ መሆኑን ለመግለፅና ለአርያነት ፀሀፍት ፈሪሳውያን የአይሁድ ካህናት መጥተው እስኪይዙት ድረስ ሲፀልይ በማደሩ ምክንያት ፀሎተ ሀሙስ በመባል ይታወቃል ፡፡

ትህትና ፍቅር መታዘዝ እንድሁም የአገልግሎትም ትርጉም
ለማስረዳትና ለማስገንዘብ እርሱ ጌታ አምላክ ሆኖ ሳለ ዝቅ ብሎ የደቀመዛሙርቱን እግር በማጠቡ ህፅበተ እግር በመባልም እንደሚጠራም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ይናገራሉ ፡፡

ሀዋርያው ቅዱስ ዮሀንስም እግራቸውን አጥቦ ልብሱንም አንስቶ ዳግመኛ ተቀመጠ እንድህም አላቸው ያደረኩላችሁን
ታስተውላላችሁን እንግድህ ጌታ መምህር ስሆን እግራችሁን
ካጠብሁ እናንተ ደግሞ ለታናናሾቻችሁ እንድሁ ታደርጉ ዘንድ ይገባችኀል ሲል ተናግራል፡፡ ይኸውም ዮሀንስ ወንጌል 13 ፣12
- 20 በዝርዝር ይገኛል ፡፡

ይህ ለእናንተ በመስቀል ላይ የሚቆረሰው ስጋየ ነው እንካችሁ
ብሉ ይህ ፅዋ ለእናንተ የሚፈሰው የሀዲስ ኪዳን ደሜ ነው ከእርሱ ጠጡ በማለት ሚስጥረ ቁርባንን የመሰረተበት ወይንም
እራሱ ጌታችን አምላካችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ሚስጥረ ቁርባንን የጀመረበት እለት በመሆኑ የሚስጥር ቀን በመባል ይጠራል ፡፡

ይኸውም የሰው ልጆች ስጋውንና ደሙን ተቀብለው ከእርሱ ጋራ
አንድነትንና ህብረትን እንድኖረን ጥንተ ጠላት ዳቢሎስን ድል
ነስተን ሰማያዊዩን እርስት እንድንወርስ ሊያደርግ ነው፡፡ ይህም በማቴወስ 26 ፣ 26 - 29 በዝርዝር ይገኛል ፡፡

አይሁድ ጌታችንን ለመያዝ በእነርሱ ጥበብና ፍላጎት ቀስ ብለው
መጥተው የያዙበት ስለሆነ በዚህ እለት በለ ሆሳስ ወይም ብዙ
የጩኸት ድምፅ ሳይሰማ የቅዳሴ ስርአት ይፈፀማል ፡፡

ስለሆነም መላው ህዝበ ክርስቲያን በዚህ የህፅበተ ሚስጥር የፀሎት እለት በሆነው በዚህ እለት በንስሀ ታጥበው የጌታን ስጋና ደሙን እንድቀበሉ ቤተ ክርስቲያን በአፅኖት ታስተምራለች ፡፡

እኛም በንስሀ ታጥበን ወደ አምላካችን ቀርበን ስጋወ ደሙን
ልንቀበል ይገባናል የጌታችን ቸርነት ፍቅሩ የእመ አምላክ
የንፅሒተ ንፁሀን የድንግል ማርያም ምልጃ የመላክት ጥበቃ
የሠማአታት ፀጋ በረከታቸው በሁላችን ላይ ይደርብን አሜን
አሜን አሜን !!!

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
https://t.me/yetewahedofera


Репост из: የተዋሕዶ ፍሬዎች
የጸሎተ ሐሙስ ሥርዐተ ቅዳሴ፦

የጸሎተ ሐሙስ ቅዳሴ ከወትሮ የተለየ ነው።
ቅዳሴም ሲገባ ደወል ስለማይኖር ጽናጽልን እያቃጨሉ ይገባሉ።

በአጠቃላይ በደወል ፈንታ ጽናጽል በአገልግሎት ላይ ይውላል።

ቅዳሴውም የሚቀደሰው በተመጠነ ድምጽ / በለሖሳስ / ነው።

ምሥጢሩ ደግሞ ይሁዳ ጌታን በሠላሳ ብር ለመሸጥ ይፋዊ ባልሆነ ድምጽ / በሹክሸክታ / መነጋገሩን ለማመልከት ነው። 

አንድም ሰሙነ ሕማማት የዘመነ ብሉይ መታሰቢያ ነውና የዘመነ ብሉይ ጸሎትና አገልግሎት ደግሞ እስከ መንበረ ጸባኦት የሚሰማ ኃይል ያልነበረው ምድራዊ በረከት ቢያሰጥ እንጂ ሰማያዊ ሕይወት የዘለዓለም ተስፋ ማስገኘት ያልቻለ የድካም አገልግሎት እንደነበር ለማስታወስ ነው።

አንድም ጌታ ዐርብ በአራት ማዕዝን መንገድ / በአደባባይ / ለዓለም ሁሉ ቤዛ ሆኖ ከመስቀሉ አስቀድሞ ሐሙስ ምሽት በአልዓዛር ቤት ለደቀመዛሙርቱ ብቻ በምሥጢር ሥርዐተ ቁርባንን ያስተማረበትና የፈጸመበትን ለማስታወስ በቤተ መቅደሱ ተገኝተው ለሚያስቀድሱ ምእመናን ብቻ በሚሰማ በአነስተኛ ድምጽ ቅዳሴ ይከናወናል ማለት ነው።

በዚህ ባለንበት ዘምን ግን አንዳንድ የከተማ አድባራት በድምፅ ማጉያ ሲቀድሱ ይታያሉ ።


#የጸሎተ ሐሙስ ቅዳሴ ዓላማ፡- ሰሙነ ሕማማት ቅዳሴ አይኖርም ፡፡

ምክንያቱም ሳምንቱ የጌታን ነገረ መስቀል ለመዘከር ብቻ የተለየ ሳምንት በመሆኑ ነው።

ታዲያ የዚህ ዕለት ቅዳሴ ለምን አስፈለገ? ከተባለ፣ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የብሉይ ኪዳንን መሥዋት አሳልፎ አዲሱን ኪዳን የመሠረተበት ዕለት በመሆኑ ለዚህ መታሰቢያ ነው ፡፡

ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህች ዕለት በመጀመሪያ እስራኤላውያን በግ አርደው ፣ ደሙን አፍስሰው ሥጋውንም ጠብሰው ቂጣ ጋግረው ንፍሮ ቀቅለው የሚያከብሩትን በዓለ ፋሲካ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር አክብሯል።

በስተመጨረሻ ላይ ደግሞ ሕይወት የሚሰጥ እውነተኛ የፋስካ በግ እርሱ ራሱ መሆኑን ሲናገር “ እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው ፣ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፡ ” በማለት አዲሱን የሕይወት ቃል ኪዳን መሥርቷል።

የቃል ኪዳኑ ምልክትም ሥጋና ደሙ ሆኗል።  የዚህ ዕለት ቅዳሴም ያስፈለገው ይህን ለመዘከር ነው። ለምን ከመሰቀሉ በፊት ሥጋውና ደሙን ሰጠ የሚለውን ሊቃውንቱ ሲያብራሩ “ ዐርብ በመልዕልተ መስቀል ተሰቅዬ ብታዩኝ ሕያው ነኝ እንደ ዛሬው ነኝ ምውት ነው ብላችሁ አታስቡ እንደ ዛሬው ነኝ " ለማለት መሆኑን ያብራራሉ፡ ( የወንጌል አንድምታ )

የጸሎተ ሐሙስ የዕለቱ አገልግሎት ፍጻሜውን የሚያገኘው ከቅዳሴ በማስከተል ዕለቱን የሚመለከት ክብር ይዕቲ ፣ ዕጣነ ሞገርና ዝማሬ በዜማ ከደረሰ በኋላ ነው። አገልግሎቱ ሲጠናቀቅም ሕዝቡ ያለ ኑዛዜና ቡራኬ ይሰናበታል።  “ ቁርባን ሲፈጸም ካህን በአንብሮ እድ ሳይባርክ ያሰናብታል ኃዳፌ ነፍስ አይባልም ” እንዲል ፡፡
https://t.me/yetewahedofera
https://t.me/yetewahedofera
https://t.me/yetewahedofera


Репост из: የተዋሕዶ ፍሬዎች
🕊


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን፡፡
-----------------------------------------------

አንድ ጥያቄ አለኝ!

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

ጥያቄ ፦

፩ . በስሙነ ሕማማት ማማተብ ፣ ማዕድ መባረክ ፣ መልክዐ መልክ መድገም አይፈቀድምን?


፪ . ሰሙነ ሕማማት ከገባ ጊዜ ጀምሮ ማማተብ ፣ ማዕድም ሲቀርብ ባርኮ መቁረስና ስለ እነሱ ብሎ ቡራኬ መስጠት የተከለከለ ነው ይባላል፡፡ ትክክል ነውን? ለምን?

፫ . በተጨማሪም መልክዐመልኮች አይደገሙም ፣ የሃይማኖት ጸሎት ሲደገም "ስለኛ ተሰቀለ በጴንጤናዊው በጲላጦስ ዘመን እርሱ መከራን ተቀበለ ሞተ ተቀበረ  በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ..." እስከሚለው ድረስ ከሰኞ እስከ ሐሙስ አይደገምም ይዘለላል ምክንያቱ ምንድን ነው?

-----------------------------------------------

[      ምላሽ     ]

- ማማተብ !

ይህ የሚያመለክተው በጉባዔ ፣ በአደባባይ ፣ በይፋ የሚደረገውን ነው፡፡ በብዙኃን ፊት ቡራኬ መስጠት ፣ የሞተ መፍታት ፣ መስቀል ማሳለም አይፈቀድም፡፡ ይህም ፭ ሺህ ፭ መቶ ዘመን ዓለም በማእሠረ ሰይጣን እንዳለ ፣ በግዞት በመርገም ውስጥ እንደነበረ ለማስታወስ ነው እንጂ ማዕዳችሁን አትባርኩ የሚል ሥርዓት አልተደነገገም፡፡

በግሉ አንድ ሰው ፊቱን በትእምርተ መስቀል አማትቦ መጸለይ ይችላል፡፡ ምክንያቱም አንድ ሰው ካላማተበ የአጋንንትን ውጊያ ድል መንሣት አይችልም፡፡ ስለዚህ በግል ጸሎት አታማትብ አይባልም፡፡ አይከለከልም፡፡

-  ጸሎት !

የሃይማኖት ጸሎትም ሲደገም ፦ "ስለ እኛ ተሰቀለ ፣ በጴንጤናዊው በጲላጦስ ዘመን እርሱ መከራን ተቀበለ ፣ ሞተ ፣ ተቀበረ ፣ በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ" እስከሚለው ድረስ ከሰኞ እስከ ሐሙስ አይደገምም "ሐመ" ብለው ይተውታል፡፡ ይሄ ታሪኩን ለማስታወስ ነው፡፡ ጸሎቱ የሚከለከል ሆኖ አይደለም፡፡ ወቅቱን እየጠበቅን ድርጊቱን ለማስተማር ነው፡፡ ይኸውም ሰኞ ፣ ማክሰኞ ፣ ረቡዕ ፤ ሐሙስ መከሩ ከሐሙስ እስከ ዓርብ ሌሊት መከራውን ተቀበለ ፤ ዓርብ ስድስት ሰዓት ላይ ተሰቀለ እንላለን ፤ ከዘጠኝ ሰዓት ጀምሮ "ሞተ ተቀበረ" ይባላል፡፡ "ተነሣ" የምንለው ደግሞ ቅዳሜ በሌሊት ስድስት ሰዓት ነው፡፡ ያንን በየሰዓቱ የተደረገውን ታሪክ ለማስታወስ ፣ ለመግለጽ ፣ ለማስተማር ነው፡፡

መልክዐ መልኮች አለመደገማቸው ደግሞ ወደ ነገረ መስቀሉ ለማድላት ነው፡፡ ነገረ መስቀሉ ከሁሉ በላይ ነውና፡፡ ዓለም የዳነው በጌታችንና በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ ካሳነት ነው ፤ ይህንን የምናስታውስበት በስሙነ ሕማማት የእርሱን ካሳነት በፍጹም ተመስጦ እናስባለን እንጸልያለን፡፡ በዚህ ወቅት በቂ ጊዜ ስለማይኖር ወደ ቅዱሳን ገድል ትሩፋት ድጋም [ጸሎት ፣ ንባብ] አንሄድም፡፡

ነገር ግን ጊዜ ከተገኘ በሕማማት ቢሆን የቅዱሳንን ገድሎች እናነባቸዋለን፡፡ የሰዓት ቁጠባ ነው እንጂ ሌላ ምንም ምክንያት የለውም፡፡ ግብረ ሕማማቱ እራሱ በየሰዓቱ የተዘጋጀ የራሱ ጸሎት አለው፡፡ በእረፍት ሰዓት ግን ገድሎችንም ሆነ ስንክሳርን እናነባለን፡፡ ከሰዓት አንጻር የሚታይ ነው፡፡ ወደ ነገረ መስቀሉ ለማድላት ሕማሙን ሞቱን መከራውን ለእኛ ያደረገውን ካሳ በስሙነ ሕማማት በፍጹም ልቡና ለማሰብ ቅድሚያ ለእርሱ እንዲሰጥ ነው፡፡

[አንድ ጥያቄ አለኝ መለከት ቁጥር አንድ መጽሐፍ]

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፣ ወለወላዲቱ ድንግል ፡ ወለመስቀሉ ክቡር አሜን፡፡
ይቆየን !

         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬

Показано 20 последних публикаций.